ዘዳግም 16 – NASV & CCBT

New Amharic Standard Version

ዘዳግም 16:1-22

ፋሲካ

16፥1-8 ተጓ ምብ – ዘፀ 12፥14-20ዘሌ 23፥4-8ዘኍ 28፥16-25

1አምላክህ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) በአቢብ ወር ከግብፅ በሌሊት ስላወጣህ፣ የአቢብን ወር ጠብቅ፤ የአምላክህን የእግዚአብሔርን (ኤሎሂም ያህዌ) ፋሲካ አክብርበት። 2እግዚአብሔር (ያህዌ) ለስሙ ማደሪያ ይሆን ዘንድ በሚመርጠው ስፍራ ከበግና ከፍየል ወይም ከመንጋህ አንዱን እንስሳ ለአምላክህ ለእግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) ፋሲካ አድርገህ ሠዋው። 3ከቦካ ቂጣ ጋር አትብላው፤ ከግብፅ የወጣኸው በችኰላ ነውና ከግብፅ የወጣህበትን ጊዜ በሕይወትህ ዘመን ሁሉ ታስብ ዘንድ የመከራ ቂጣ ሰባት ቀን ብላ። 4በምድርህ ሁሉ ላይ በአንተ ዘንድ ለሰባት ቀን እርሾ አይገኝ፤ በመጀመሪያው ዕለት ምሽት ከምትሠዋውም ላይ ማናቸውንም ሥጋ ጧት ድረስ እንዲቈይ አታድርግ። 5አምላክህ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) በሚሰጥህ በማናቸውም ከተማ ፋሲካን መሠዋት አይገባህም፤ 6ነገር ግን ለስሙ ማደሪያ ይሆን ዘንድ አምላክህ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) በሚመርጠው ስፍራ፣ ፀሓይ ስትጠልቅ ምሽቱ16፥6 ወይም፣ ፀሓይ ስትወጣ ንጋቱ ላይ ላይ ከግብፅ በወጣህበት ሰዓት16፥6 ወይም ዓመታዊ መታሰቢያ እንዲሆን፣ በዚያ ፋሲካን ሠዋ። 7ሥጋውንም ጠብሰህ አምላክህ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) በሚመርጠው ስፍራ ብላ፤ ሲነጋም ወደ ድንኳንህ ተመልሰህ ሂድ።

8ስድስት ቀን ያልቦካ ቂጣ ብላ፤ በሰባተኛው ቀን ለአምላክህ ለእግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) የተቀደሰ ጉባኤ አድርግ፤ ሥራም አትሥራበት።

የመከር በዓል

16፥9-12 ተጓ ምብ – ዘሌ 23፥15-22ዘኍ 28፥26-31

9እህልህን ማጨድ ከምትጀምርበት ዕለት አንሥቶ ሰባት ሳምንት ቍጠር። 10ከዚያም በኋላ አምላክህ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) በባረከህ መጠን፣ በፈቃድህ የምታመጣውን ስጦታ በማቅረብ በመከሩ በዓል አምላክህን እግዚአብሔርን (ኤሎሂም ያህዌ) አክብር። 11አንተ፣ ወንዶችና ሴቶች ልጆችህ፣ ወንዶችና ሴቶች አገልጋዮችህ፣ በከተሞችህ ያለ ሌዋዊና መጻተኛ፣ በመካከልህ የሚኖሩ አባት የሌላቸውና መበለቶች አምላክህ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) ለስሙ ማደሪያ እንዲሆን በሚመርጠው ስፍራ በአምላክህ በእግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) ፊት ደስ ይበላችሁ። 12አንተም በግብፅ ባሪያ እንደ ነበርህ አስታውስ፤ ይህንም በጥንቃቄ ጠብቅ።

የዳስ በዓል

16፥13-17 ተጓ ምብ – ዘሌ 23፥33-43ዘኍ 29፥12-39

13የእህልህን ምርት ከዐውድማህ፣ ወይንህንም ከመጭመቂያህ ከሰበሰብህ በኋላ፣ የዳስን በዓል ሰባት ቀን አክብር። 14በበዓልህ አንተ፣ ወንድና ሴት ልጅህ፣ ወንድና ሴት አገልጋይህ፣ በከተማው ያለ ሌዋዊ፣ መጻተኛ፣ አባት አልባውና መበለቲቱ ደስ ይበላችሁ። 15እግዚአብሔር (ያህዌ) በመረጠው ስፍራ ለአምላክህ ለእግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) በዓሉን ሰባት ቀን አክብር፤ አምላክህ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) በእህል ምርትህና በእጅህ ሥራ ሁሉ ይባርክሃል፤ ደስታህም ፍጹም ይሆናል።

16ወንዶችህ ሁሉ በዓመት ሦስት ጊዜ፣ በቂጣ በዓል፣ በመከር በዓልና በዳስ በዓል ላይ እርሱ በሚመርጠው ስፍራ በአምላክህ በእግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) ፊት ይቅረቡ፤ ማንም ሰው በእግዚአብሔር (ያህዌ) ፊት ባዶ እጁን አይቅረብ። 17አምላክህ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) በባረከህ መጠን እያንዳንዱ እንደ ችሎታው ይስጥ።

ስለ ፍርድ አሰጣጥ

18አምላክህ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) በሚሰጥህ ከተሞች ሁሉ ለየነገዶችህ ዳኞችንና አለቆችን ሹም፤ እነርሱም ሕዝቡን በቅን ፍርድ ይዳኙ። 19ፍርድ አታዛባ፤ አድልዎ አታድርግ፤ ጕቦም አትቀበል፤ ጕቦ የጠቢባንን ዐይን ያሳውራል፤ የጻድቃንንም ቃል ያጣምማልና። 20በሕይወት እንድትኖርና አምላክህ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) የሚሰጥህን ምድር እንድትወርስ፣ ቅን ፍርድን ብቻ ተከተል።

ሌሎችን አማልክት ስለ ማምለክ

21ለአምላክህ ለእግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) በምትሠራው መሠዊያ አጠገብ የአሼራን ምስል የዕንጨት ዐምድ አታቁም16፥21 ወይም፣ ለአሼራ ብለህ ምንም ዐይነት ዛፍ አትትከል22አምላክህ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) የሚጠላውን ማምለኪያ ዐምድ ለአንተ አታቁም።

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

申命記 16:1-22

逾越節

1「你們要在亞筆月16·1 亞筆月是猶太曆的第一個月,約在陽曆三月中旬到四月中旬,相當於中國的春分時節。為你們的上帝耶和華守逾越節,因為祂在這個月的一個晚上帶領你們離開了埃及2你們要在你們的上帝耶和華選定的敬拜場所,把牛羊作為逾越節的祭牲獻給祂。 3吃祭牲的時候,不可吃有酵的餅,七天之內要吃無酵餅,即憶苦餅,以便你們一生謹記離開埃及的日子,因為當時你們離開得很倉促。 4那七天之內,你們境內不可有酵母。第一天傍晚獻的祭肉不可留到第二天早晨。 5在你們的上帝耶和華將要賜給你們的各城中,你們不可隨便獻逾越節的祭牲, 6而是要在傍晚日落時分,即你們離開埃及的時候,到你們的上帝耶和華選定的敬拜場所獻逾越節的祭牲。 7你們要在那裡煮祭肉吃,第二天早晨可以返回自己的帳篷。 8在隨後的六天之內,你們要吃無酵餅。第七天,要舉行莊嚴的聚會,敬拜你們的上帝耶和華。那一天你們不可做工。

七七收穫節

9「從收割那天開始算起,你們要算出七週的時間。 10七週後,要為你們的上帝耶和華守七七收穫節16·10 七七收穫節」後稱為五旬節。。那時,你們要按照你們的上帝耶和華所賜的福分,甘心樂意地獻上祭物。 11你們要和兒女、僕婢、同城的利未人、寄居者及孤兒寡婦在你們的上帝耶和華選定的敬拜場所,在祂面前一起歡喜快樂。 12你們要記住自己曾在埃及做過奴隸,因此要謹遵這些律例。

住棚節

13「在收藏好穀物和新酒後,你們要守七天的住棚節。 14住棚節期間,你們要和兒女、僕婢、同城的利未人、寄居者及孤兒寡婦一起歡慶。 15要在你們的上帝耶和華選定的地方,為祂守住棚節七天;要滿心歡喜,因為你們的上帝耶和華賜福你們,使你們的出產豐富、凡事順利。

16「你們所有男子要每年三次,即在無酵節、七七收穫節和住棚節,在你們的上帝耶和華指定的地方朝見祂。你們不可空手朝見, 17各人要按祂賜的福分,盡自己的能力獻上禮物。

委任審判官

18「要在你們的上帝耶和華將要賜給你們的各城中,按支派委任審判官及其他官員。官員們要秉公審判, 19不可徇私枉法、偏心待人,收受賄賂,因為賄賂能蒙蔽智者的眼睛,使正直人顛倒是非。 20你們要追求公正公義,以便可以存活,承受你們的上帝耶和華將要賜給你們的土地。

不可拜偶像

21「在為你們的上帝耶和華建造的祭壇旁,你們不可豎立亞舍拉木神像, 22也不可豎立神柱,因為這些是你們的上帝耶和華所憎惡的。