ዘካርያስ 6 – NASV & NVI-PT

New Amharic Standard Version

ዘካርያስ 6:1-15

አራቱ ሠረገሎች

1እንደ ገናም ወደ ላይ ተመለከትሁ፤ እነሆ አራት ሠረገሎች ከሁለት ተራራ መካከል ሲወጡ አየሁ፤ ተራሮቹም የናስ ተራሮች ነበሩ። 2የመጀመሪያው ሠረገላ መጋላ፣ ሁለተኛው ዱሪ፤ 3ሦስተኛው ዐምባላይ፤ አራተኛውም ዝጕርጕር ፈረሶች ነበሯቸው፤ ሁሉም ጠንካሮች ነበሩ። 4እኔም ከእኔ ጋር ይነጋገር የነበረውን መልአክ፣ “ጌታዬ ሆይ፤ እነዚህ ምንድን ናቸው?” አልሁት።

5መልአኩም እንዲህ አለኝ፤ “እነዚህ አራቱ ቆመው ከነበሩበት ከምድር ሁሉ ጌታ ፊት የወጡ የሰማይ መናፍስት6፥5 ወይም ነፋሳት ሊሆን ይችላል። ናቸው። 6የባለ ዱሪ ፈረሶች ወደ ሰሜን፤ የባለ አምባላይ ፈረሶች ወደ ምዕራብ6፥6 ወይም ከኋላቸው ፈረሶች እንደ ማለት ነው። አገር፣ የባለ ዝጕርጕር ፈረሶች ወደ ደቡብ አገር ይወጣል።” 7ጠንካሮቹ ፈረሶች ሲወጡ፣ በምድር ሁሉ ለመመላለስ አቈብቍበው ነበር። እርሱም፣ “ወደ ምድር ሁሉ ሂዱ” አላቸው፤ እነርሱም ወደ ምድር ሁሉ ሄዱ። 8ከዚያም ጮኾ እንዲህ አለኝ፤ “እነሆ፤ ወደ ሰሜን አገር የሚወጡት፣ መንፈሴን በሰሜን ምድር አሳርፈውታል።”

ለኢያሱ የተደረገለት አክሊል

9የእግዚአብሔር ቃል እንዲህ ሲል ወደ እኔ መጣ፤ 10“ከባቢሎን ከመጡት ምርኮኞች ከሔልዳይና ከጦብያ፣ ከዮዳኤም ወርቅና ብር ውሰድ፤ በዚያው ቀን ወደ ሶፎንያስ ልጅ ወደ ኢዮስያስ ቤት ሂድ። 11ወርቁንና ብሩን ወስደህ አክሊል ሥራ፤ በኢዮሴዴቅ ልጅ በሊቀ ካህኑ በኢያሱ ራስ ላይም አድርገው፤ 12ለእርሱም እግዚአብሔር ጸባኦት እንዲህ ይላል ብለህ ንገረው፤ ‘እነሆ፤ ስሙ ቅርንጫፍ የተባለው ሰው ይህ ነው፤ እርሱም በቦታው ይንሰራፋል፤ የእግዚአብሔርንም ቤተ መቅደስ ይሠራል። 13የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ የሚሠራው እርሱ ነው፤ ክብርን ይጐናጸፋል፤ በዙፋኑ ተቀምጦ ይገዛል፤ በዙፋኑም ላይ ካህን ይሆናል፤ በሁለቱም መካከል ስምምነት ይኖራል።’ 14አክሊሉም ለሔሌምና6፥14 ሲርያክ፤ ዕብራይስጡ ሔሌም ይላል። ለጦብያ፣ ለዮዳኤና ለሶፎንያስ ልጅ ለሔን6፥14 ወይም ርኅሩኁ እንደ ማለት ነው። በእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ውስጥ መታሰቢያ ይሆናል። 15እነዚያ በሩቅ ያሉት መጥተው የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ሲሠራ ያግዛሉ፤ እናንተም እግዚአብሔር ጸባኦት እንደ ላከኝ ታውቃላችሁ። ለአምላካችሁ ለእግዚአብሔር በጥንቃቄ ብትታዘዙ ይህ ይሆናል።”

Nova Versão Internacional

Zacarias 6:1-15

Quatro Carruagens

1Olhei novamente e vi diante de mim quatro carruagens que vinham saindo do meio de duas montanhas de bronze. 2À primeira estavam atrelados cavalos vermelhos; à segunda, cavalos pretos; 3à terceira, cavalos brancos; e à quarta, cavalos malhados. Todos eram vigorosos. 4Perguntei ao anjo que falava comigo: Que representam estes cavalos atrelados, meu senhor?

5O anjo me respondeu: “Estes são os quatro espíritos6.5 Ou ventos dos céus, que acabam de sair da presença do Soberano de toda a terra. 6A carruagem puxada pelos cavalos pretos vai em direção à terra do norte, a que tem cavalos brancos vai em direção ao ocidente6.6 Hebraico: vai atrás deles., e a que tem cavalos malhados vai para a terra do sul”.

7Os vigorosos cavalos avançavam, impacientes por percorrer a terra. E o anjo lhes disse: “Percorram toda a terra!” E eles foram.

8Então ele me chamou e disse: “Veja, os que foram para a terra do norte deram repouso ao meu Espírito6.8 Ou espírito naquela terra”.

A Coroa de Josué

9E o Senhor me ordenou: 10“Tome prata e ouro dos exilados Heldai, Tobias e Jedaías, que chegaram da Babilônia. No mesmo dia, vá à casa de Josias, filho de Sofonias. 11Pegue a prata e o ouro, faça uma coroa, e coloque-a na cabeça do sumo sacerdote Josué, filho de Jeozadaque. 12Diga-lhe que assim diz o Senhor dos Exércitos: Aqui está o homem cujo nome é Renovo, e ele sairá do seu lugar e construirá o templo do Senhor. 13Ele construirá o templo do Senhor, será revestido de majestade e se assentará em seu trono para governar. Ele será sacerdote no trono. E haverá harmonia entre os dois. 14A coroa será para Heldai6.14 Conforme a Versão Siríaca. O Texto Massorético diz Helém., Tobias, Jedaías e Hem6.14 Ou o bondoso, filho de Sofonias, como um memorial no templo do Senhor. 15Gente de longe virá ajudar a construir o templo do Senhor. Então vocês saberão que o Senhor dos Exércitos me enviou a vocês. Isso só acontecerá se obedecerem fielmente à voz do Senhor, o seu Deus”.