ዘካርያስ 6 – NASV & NIV

New Amharic Standard Version

ዘካርያስ 6:1-15

አራቱ ሠረገሎች

1እንደ ገናም ወደ ላይ ተመለከትሁ፤ እነሆ አራት ሠረገሎች ከሁለት ተራራ መካከል ሲወጡ አየሁ፤ ተራሮቹም የናስ ተራሮች ነበሩ። 2የመጀመሪያው ሠረገላ መጋላ፣ ሁለተኛው ዱሪ፤ 3ሦስተኛው ዐምባላይ፤ አራተኛውም ዝጕርጕር ፈረሶች ነበሯቸው፤ ሁሉም ጠንካሮች ነበሩ። 4እኔም ከእኔ ጋር ይነጋገር የነበረውን መልአክ፣ “ጌታዬ ሆይ፤ እነዚህ ምንድን ናቸው?” አልሁት።

5መልአኩም እንዲህ አለኝ፤ “እነዚህ አራቱ ቆመው ከነበሩበት ከምድር ሁሉ ጌታ ፊት የወጡ የሰማይ መናፍስት6፥5 ወይም ነፋሳት ሊሆን ይችላል። ናቸው። 6የባለ ዱሪ ፈረሶች ወደ ሰሜን፤ የባለ አምባላይ ፈረሶች ወደ ምዕራብ6፥6 ወይም ከኋላቸው ፈረሶች እንደ ማለት ነው። አገር፣ የባለ ዝጕርጕር ፈረሶች ወደ ደቡብ አገር ይወጣል።” 7ጠንካሮቹ ፈረሶች ሲወጡ፣ በምድር ሁሉ ለመመላለስ አቈብቍበው ነበር። እርሱም፣ “ወደ ምድር ሁሉ ሂዱ” አላቸው፤ እነርሱም ወደ ምድር ሁሉ ሄዱ። 8ከዚያም ጮኾ እንዲህ አለኝ፤ “እነሆ፤ ወደ ሰሜን አገር የሚወጡት፣ መንፈሴን በሰሜን ምድር አሳርፈውታል።”

ለኢያሱ የተደረገለት አክሊል

9የእግዚአብሔር ቃል እንዲህ ሲል ወደ እኔ መጣ፤ 10“ከባቢሎን ከመጡት ምርኮኞች ከሔልዳይና ከጦብያ፣ ከዮዳኤም ወርቅና ብር ውሰድ፤ በዚያው ቀን ወደ ሶፎንያስ ልጅ ወደ ኢዮስያስ ቤት ሂድ። 11ወርቁንና ብሩን ወስደህ አክሊል ሥራ፤ በኢዮሴዴቅ ልጅ በሊቀ ካህኑ በኢያሱ ራስ ላይም አድርገው፤ 12ለእርሱም እግዚአብሔር ጸባኦት እንዲህ ይላል ብለህ ንገረው፤ ‘እነሆ፤ ስሙ ቅርንጫፍ የተባለው ሰው ይህ ነው፤ እርሱም በቦታው ይንሰራፋል፤ የእግዚአብሔርንም ቤተ መቅደስ ይሠራል። 13የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ የሚሠራው እርሱ ነው፤ ክብርን ይጐናጸፋል፤ በዙፋኑ ተቀምጦ ይገዛል፤ በዙፋኑም ላይ ካህን ይሆናል፤ በሁለቱም መካከል ስምምነት ይኖራል።’ 14አክሊሉም ለሔሌምና6፥14 ሲርያክ፤ ዕብራይስጡ ሔሌም ይላል። ለጦብያ፣ ለዮዳኤና ለሶፎንያስ ልጅ ለሔን6፥14 ወይም ርኅሩኁ እንደ ማለት ነው። በእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ውስጥ መታሰቢያ ይሆናል። 15እነዚያ በሩቅ ያሉት መጥተው የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ሲሠራ ያግዛሉ፤ እናንተም እግዚአብሔር ጸባኦት እንደ ላከኝ ታውቃላችሁ። ለአምላካችሁ ለእግዚአብሔር በጥንቃቄ ብትታዘዙ ይህ ይሆናል።”

New International Version

Zechariah 6:1-15

Four Chariots

1I looked up again, and there before me were four chariots coming out from between two mountains—mountains of bronze. 2The first chariot had red horses, the second black, 3the third white, and the fourth dappled—all of them powerful. 4I asked the angel who was speaking to me, “What are these, my lord?”

5The angel answered me, “These are the four spirits6:5 Or winds of heaven, going out from standing in the presence of the Lord of the whole world. 6The one with the black horses is going toward the north country, the one with the white horses toward the west,6:6 Or horses after them and the one with the dappled horses toward the south.”

7When the powerful horses went out, they were straining to go throughout the earth. And he said, “Go throughout the earth!” So they went throughout the earth.

8Then he called to me, “Look, those going toward the north country have given my Spirit6:8 Or spirit rest in the land of the north.”

A Crown for Joshua

9The word of the Lord came to me: 10“Take silver and gold from the exiles Heldai, Tobijah and Jedaiah, who have arrived from Babylon. Go the same day to the house of Josiah son of Zephaniah. 11Take the silver and gold and make a crown, and set it on the head of the high priest, Joshua son of Jozadak.6:11 Hebrew Jehozadak, a variant of Jozadak 12Tell him this is what the Lord Almighty says: ‘Here is the man whose name is the Branch, and he will branch out from his place and build the temple of the Lord. 13It is he who will build the temple of the Lord, and he will be clothed with majesty and will sit and rule on his throne. And he6:13 Or there will be a priest on his throne. And there will be harmony between the two.’ 14The crown will be given to Heldai,6:14 Syriac; Hebrew Helem Tobijah, Jedaiah and Hen6:14 Or and the gracious one, the son of Zephaniah as a memorial in the temple of the Lord. 15Those who are far away will come and help to build the temple of the Lord, and you will know that the Lord Almighty has sent me to you. This will happen if you diligently obey the Lord your God.”