ዘካርያስ 1 – NASV & PCB

New Amharic Standard Version

ዘካርያስ 1:1-21

ሕዝቡ ወደ እግዚአብሔር እንዲመለስ የቀረበ ጥሪ

1ዳርዮስ በነገሠ በሁለተኛው ዓመት በስምንተኛው ወር የእግዚአብሔር ቃል ወደ አዶ ልጅ ወደ በራክዩ ልጅ ወደ ነቢዩ ዘካርያስ እንዲህ ሲል መጣ፤

2እግዚአብሔር በአባቶቻችሁ ላይ እጅግ ተቈጥቶ ነበር፤ 3ስለዚህ ለሕዝቡ ንገር፤ እግዚአብሔር ጸባኦት እንዲህ ይላል፤ ‘ወደ እኔ ተመለሱ፤’ ይላል እግዚአብሔር ጸባኦት፤ ‘እኔም ወደ እናንተ እመለሳለሁ፤’ ይላል እግዚአብሔር ጸባኦት። 4የቀደሙት ነቢያት፣ ‘እግዚአብሔር ጸባኦት፣ “ከክፉ መንገዳችሁና ከክፉ ሥራችሁ ተመለሱ” ይላል በማለት ለአባቶቻችሁ ሰብከው ነበር፤ እነርሱ ግን አልሰሙም፤ እኔንም አላደመጡም፤ እንደ እነርሱ አትሁኑ፤’ ይላል እግዚአብሔር5አባቶቻችሁ አሁን የት አሉ? ነቢያትስ ለዘላለም በሕይወት ይኖራሉን? 6ለባሪያዎቼ ለነቢያት ያዘዝኋቸው ቃልና ሥርዐት በአባቶቻችሁ ላይ አልደረሰምን?

“እነርሱም ንስሓ ገብተው እንዲህ አሉ፤ ‘እግዚአብሔር ጸባኦት በወሰነው መሠረት፣ ለሥራችንና ለመንገዳችን የሚገባውን አድርጎብናል።’ ”

በባርሰነት ዛፎች መካከል የቆመው ሰው

7ዳርዮስ በነገሠ በሁለተኛው ዓመት፣ ሳባጥ በሚባለው በዐሥራ አንደኛው ወር በሃያ አራተኛው ቀን፣ የእግዚአብሔር ቃል ወደ አዶ ልጅ ወደ በራክዩ ልጅ ወደ ነቢዩ ዘካርያስ እንዲህ ሲል መጣ፤

8በምሽት ራእይ አየሁ፤ እዚያም በፊቴ አንድ ሰው በመጋላ ፈረስ ላይ ተቀምጧል፤ እርሱም በሸለቆ ውስጥ በባርሰነት ዛፎች መካከልም ቆሞ ነበር፤ ከበስተ ኋላውም መጋላ፣ ሐመርና አንባላይ ፈረሶች ነበሩ።

9እኔም፣ “ጌታዬ ሆይ፤ እነዚህ ምንድን ናቸው?” አልሁ።

ከእኔ ጋር ይነጋገር የነበረው መልአክም፣ “እነዚህ ምን እንደ ሆኑ አሳይሃለሁ” አለኝ።

10ከዚያም በባርሰነት ዛፎች መካከል የቆመው ሰው፣ “እነዚህ በምድር ሁሉ እንዲመላለሱ እግዚአብሔር የላካቸው ናቸው” ሲል መለሰ። 11እነርሱም በባርሰነት ዛፎች መካከል ቆሞ ለነበረው የእግዚአብሔር መልአክ፣ “በምድር ሁሉ ተመላለስን፤ መላዋ ምድርም ዐርፋ በሰላም ተቀምጣለች” ብለው መለሱለት።

12ከዚያም የእግዚአብሔር መልአክ፣ “እግዚአብሔር ጸባኦት ሆይ፤ በእነዚህ ሰባ ዓመታት ውስጥ የተቈጣሃቸውን ኢየሩሳሌምንና የይሁዳን ከተሞች የማትምራቸው እስከ መቼ ነው?” አለ። 13እግዚአብሔርም ከእኔ ጋር ይነጋገር ለነበረው መልአክ ደስ በሚያሰኝና በሚያጽናና ቃል መለሰለት።

14ከዚያም ከእኔ ጋር ይነጋገር የነበረው መልአክ እንዲህ አለኝ፤ “ይህን ቃል ተናገር፤ እግዚአብሔር ጸባኦት እንዲህ ይላል፤ ‘ስለ ጽዮንና ስለ ኢየሩሳሌም እጅግ ቀንቻለሁ፤ 15ሰላም አለ በሚሉ አሕዛብ ላይ ግን በጣም ተቈጥቻለሁ፤ በመጠኑ ተቈጥቼ ሳለሁ፣ እነርሱ ግን ጥፋቱ እንዲብስ አደረጉ።’

16“ስለዚህ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ ‘በምሕረት ወደ ኢየሩሳሌም እመለሳለሁ፤ በዚያም ቤቴ እንደ ገና ይሠራል፤ መለኪያ ገመድም በኢየሩሳሌም ላይ ይዘረጋል’ ይላል እግዚአብሔር ጸባኦት።

17“ቀጥለህም እንዲህ እያልህ ስበክ፤ እግዚአብሔር ጸባኦት እንዲህ ይላል፤ ‘ከተሞቼ እንደ ገና ብልጽግና ይትረፈረፍባቸዋል፤ እግዚአብሔርም እንደ ገና ጽዮንን ያጽናናል፤ ኢየሩሳሌምንም ይመርጣል።’ ”

አራቱ ቀንዶችና አራቱ የእጅ ሙያተኞች

18ከዚያም ወደ ላይ ተመለከትሁ፤ ከፊቴም አራት ቀንዶችን አየሁ፤ 19ከእኔ ጋር ይነጋገር የነበረውንም መልአክ፣ “እነዚህ ምንድን ናቸው?” አልሁት።

እርሱም፣ “እነዚህ ይሁዳን፣ እስራኤልንና ኢየሩሳሌምን የበታተኑ ቀንዶች ናቸው” አለኝ።

20ከዚያም እግዚአብሔር አራት የእጅ ሙያተኞችን አሳየኝ። 21እኔም፣ “እነዚህስ ምን ሊያደርጉ መጡ?” አልሁ።

እርሱም፣ “እነዚህ ቀንዶች ማንም ራሱን ቀና ማድረግ እንዳይችል ይሁዳን የበታተኑ ናቸው፤ እነዚህ የእጅ ሙያተኞች ግን የመጡት እነርሱን ሊያስደነግጧቸው፣ ሕዝቡን ለመበታተን በይሁዳ ምድር ላይ ቀንዳቸውን ያነሡትን የእነዚህን የአሕዛብ ቀንዶች ሰብሮ ለመጣል ነው” አለኝ።

Persian Contemporary Bible

زكريا 1:1-21

دعوت به سوی خداوند

1در سال دوم سلطنت داريوش پادشاه، در ماه هشتم، پيامی از جانب خداوند بر زكريا (پسر بركيا و نوهٔ عدوی نبی) نازل شد. خداوند قادر متعال به زكريا فرمود كه از قول او به مردم چنين بگويد: 2«من از اجداد شما بسيار خشمگين بودم. 3ولی اينک به شما می‌گويم كه اگر به سوی من بازگشت كنيد، من هم به سوی شما باز می‌گردم. 4مانند اجداد خود نباشيد كه انبيای گذشته هر چه سعی كردند آنها را از راههای زشتشان بازگردانند، توجهی به ايشان نكردند. من توسط انبيا به ايشان گفتم كه به سوی من بازگشت كنند، ولی آنها گوش ندادند.

5‏-6«اجداد شما و انبيای گذشته همگی مردند، ولی كلام من جاودانه است. كلام من گريبانگير اجداد شما شد و آنها را مجازات نمود. ايشان سرانجام بازگشت نموده گفتند: خداوند ما را به سزای اعمالمان رسانيده و آنچه را كه به ما اخطار نموده بود دقيقاً انجام داده است.»

رؤيای اسبها

7در روز بيست و چهارم، ماه يازدهم يعنی ماه شباط، از سال دوم سلطنت داريوش پادشاه، پيامی ديگر از جانب خداوند در رؤيای شب به من، زكريا رسيد. 8در كنار رودخانه‌ای، در ميان درختان آس، فرشته‌ای را سوار بر اسب سرخ ديدم. پشت سر او اسبانی به رنگهای سرخ، زرد و سفيد ايستاده بودند.

9پرسيدم: «ای سرورم، اين اسبها برای چه آنجا ايستاده‌اند؟»

فرشته جواب داد: «به تو خواهم گفت.»

10سپس به من گفت كه خداوند آنها را فرستاده است تا زمين را بررسی كنند.

11آنگاه سواران آن اسبها به فرشتهٔ خداوند گزارش داده گفتند: «در سراسر جهان گشتيم و همه جا صلح و آرامش برقرار بود.»

12فرشتهٔ خداوند چون اين را شنيد گفت: «ای خداوند قادر متعال، مدت هفتاد سال بر اورشليم و شهرهای يهودا خشمگين بودی. چقدر طول می‌كشد تا دوباره بر ايشان رحمت فرمايی؟»

13جواب خداوند به فرشته تسلی‌آميز و اطمينان‌بخش بود.

14آنگاه فرشته به من گفت: «اين پيام را از طرف خداوند قادر متعال با صدای بلند اعلام كن: من برای اورشليم و يهودا غيرت زيادی دارم. 15ولی از قومهايی كه در امنيت هستند به شدت خشمگينم، زيرا ايشان بيشتر از آنچه می‌خواستم قوم مرا آزار رساندند. 16پس من با رحمت بسيار به اورشليم باز خواهم گشت و خانهٔ من و تمام اورشليم از نو ساخته خواهد شد. 17شهرهای اسرائيل دوباره مملو از سعادت خواهند شد و من بار ديگر اورشليم را تسلی و بركت داده در آن ساكن خواهم گشت.»

رؤيای شاخها

18در رؤيايی ديگر، چهار شاخ حيوان ديدم!

19از فرشته پرسيدم: «اينها چه هستند؟»

جواب داد: «اينها نمايندهٔ آن چهار قدرت بزرگ جهانی هستند كه مردم يهودا، اسرائيل و اورشليم را پراكنده ساخته‌اند.»

20سپس فرشته، چهار آهنگر به من نشان داد.

21پرسيدم: «اين مردان برای انجام چه كاری آمده‌اند؟»

فرشته جواب داد: «آمده‌اند تا آن چهار شاخی را كه باعث پراكندگی مصيبت‌بار مردم يهودا شده‌اند، بگيرند و بر روی سندان خرد كنند و به دور اندازند.»