ዘካርያስ 1 – NASV & BDS

New Amharic Standard Version

ዘካርያስ 1:1-21

ሕዝቡ ወደ እግዚአብሔር እንዲመለስ የቀረበ ጥሪ

1ዳርዮስ በነገሠ በሁለተኛው ዓመት በስምንተኛው ወር የእግዚአብሔር ቃል ወደ አዶ ልጅ ወደ በራክዩ ልጅ ወደ ነቢዩ ዘካርያስ እንዲህ ሲል መጣ፤

2እግዚአብሔር በአባቶቻችሁ ላይ እጅግ ተቈጥቶ ነበር፤ 3ስለዚህ ለሕዝቡ ንገር፤ እግዚአብሔር ጸባኦት እንዲህ ይላል፤ ‘ወደ እኔ ተመለሱ፤’ ይላል እግዚአብሔር ጸባኦት፤ ‘እኔም ወደ እናንተ እመለሳለሁ፤’ ይላል እግዚአብሔር ጸባኦት። 4የቀደሙት ነቢያት፣ ‘እግዚአብሔር ጸባኦት፣ “ከክፉ መንገዳችሁና ከክፉ ሥራችሁ ተመለሱ” ይላል በማለት ለአባቶቻችሁ ሰብከው ነበር፤ እነርሱ ግን አልሰሙም፤ እኔንም አላደመጡም፤ እንደ እነርሱ አትሁኑ፤’ ይላል እግዚአብሔር5አባቶቻችሁ አሁን የት አሉ? ነቢያትስ ለዘላለም በሕይወት ይኖራሉን? 6ለባሪያዎቼ ለነቢያት ያዘዝኋቸው ቃልና ሥርዐት በአባቶቻችሁ ላይ አልደረሰምን?

“እነርሱም ንስሓ ገብተው እንዲህ አሉ፤ ‘እግዚአብሔር ጸባኦት በወሰነው መሠረት፣ ለሥራችንና ለመንገዳችን የሚገባውን አድርጎብናል።’ ”

በባርሰነት ዛፎች መካከል የቆመው ሰው

7ዳርዮስ በነገሠ በሁለተኛው ዓመት፣ ሳባጥ በሚባለው በዐሥራ አንደኛው ወር በሃያ አራተኛው ቀን፣ የእግዚአብሔር ቃል ወደ አዶ ልጅ ወደ በራክዩ ልጅ ወደ ነቢዩ ዘካርያስ እንዲህ ሲል መጣ፤

8በምሽት ራእይ አየሁ፤ እዚያም በፊቴ አንድ ሰው በመጋላ ፈረስ ላይ ተቀምጧል፤ እርሱም በሸለቆ ውስጥ በባርሰነት ዛፎች መካከልም ቆሞ ነበር፤ ከበስተ ኋላውም መጋላ፣ ሐመርና አንባላይ ፈረሶች ነበሩ።

9እኔም፣ “ጌታዬ ሆይ፤ እነዚህ ምንድን ናቸው?” አልሁ።

ከእኔ ጋር ይነጋገር የነበረው መልአክም፣ “እነዚህ ምን እንደ ሆኑ አሳይሃለሁ” አለኝ።

10ከዚያም በባርሰነት ዛፎች መካከል የቆመው ሰው፣ “እነዚህ በምድር ሁሉ እንዲመላለሱ እግዚአብሔር የላካቸው ናቸው” ሲል መለሰ። 11እነርሱም በባርሰነት ዛፎች መካከል ቆሞ ለነበረው የእግዚአብሔር መልአክ፣ “በምድር ሁሉ ተመላለስን፤ መላዋ ምድርም ዐርፋ በሰላም ተቀምጣለች” ብለው መለሱለት።

12ከዚያም የእግዚአብሔር መልአክ፣ “እግዚአብሔር ጸባኦት ሆይ፤ በእነዚህ ሰባ ዓመታት ውስጥ የተቈጣሃቸውን ኢየሩሳሌምንና የይሁዳን ከተሞች የማትምራቸው እስከ መቼ ነው?” አለ። 13እግዚአብሔርም ከእኔ ጋር ይነጋገር ለነበረው መልአክ ደስ በሚያሰኝና በሚያጽናና ቃል መለሰለት።

14ከዚያም ከእኔ ጋር ይነጋገር የነበረው መልአክ እንዲህ አለኝ፤ “ይህን ቃል ተናገር፤ እግዚአብሔር ጸባኦት እንዲህ ይላል፤ ‘ስለ ጽዮንና ስለ ኢየሩሳሌም እጅግ ቀንቻለሁ፤ 15ሰላም አለ በሚሉ አሕዛብ ላይ ግን በጣም ተቈጥቻለሁ፤ በመጠኑ ተቈጥቼ ሳለሁ፣ እነርሱ ግን ጥፋቱ እንዲብስ አደረጉ።’

16“ስለዚህ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ ‘በምሕረት ወደ ኢየሩሳሌም እመለሳለሁ፤ በዚያም ቤቴ እንደ ገና ይሠራል፤ መለኪያ ገመድም በኢየሩሳሌም ላይ ይዘረጋል’ ይላል እግዚአብሔር ጸባኦት።

17“ቀጥለህም እንዲህ እያልህ ስበክ፤ እግዚአብሔር ጸባኦት እንዲህ ይላል፤ ‘ከተሞቼ እንደ ገና ብልጽግና ይትረፈረፍባቸዋል፤ እግዚአብሔርም እንደ ገና ጽዮንን ያጽናናል፤ ኢየሩሳሌምንም ይመርጣል።’ ”

አራቱ ቀንዶችና አራቱ የእጅ ሙያተኞች

18ከዚያም ወደ ላይ ተመለከትሁ፤ ከፊቴም አራት ቀንዶችን አየሁ፤ 19ከእኔ ጋር ይነጋገር የነበረውንም መልአክ፣ “እነዚህ ምንድን ናቸው?” አልሁት።

እርሱም፣ “እነዚህ ይሁዳን፣ እስራኤልንና ኢየሩሳሌምን የበታተኑ ቀንዶች ናቸው” አለኝ።

20ከዚያም እግዚአብሔር አራት የእጅ ሙያተኞችን አሳየኝ። 21እኔም፣ “እነዚህስ ምን ሊያደርጉ መጡ?” አልሁ።

እርሱም፣ “እነዚህ ቀንዶች ማንም ራሱን ቀና ማድረግ እንዳይችል ይሁዳን የበታተኑ ናቸው፤ እነዚህ የእጅ ሙያተኞች ግን የመጡት እነርሱን ሊያስደነግጧቸው፣ ሕዝቡን ለመበታተን በይሁዳ ምድር ላይ ቀንዳቸውን ያነሡትን የእነዚህን የአሕዛብ ቀንዶች ሰብሮ ለመጣል ነው” አለኝ።

La Bible du Semeur

Zacharie 1:1-17

Le livre des visions

L’alliance reste établie : Revenez à moi

1Au huitième mois de la deuxième année du règne de Darius1.1 En octobre-novembre 520 av. J.-C., deux mois après qu’Aggée a commencé à prophétiser (voir Ag 1.1). Sur Darius, voir Ag 1.1 et note., l’Eternel adressa la parole à Zacharie, le prophète1.1 Sur Zacharie, voir Esd 5.1 ; 6.14 ; Né 12.4, 16., fils de Barachie et petit-fils d’Iddo, en ces termes :

2L’Eternel s’est violemment irrité contre vos pères. 3Dis à ce peuple : Voici ce que déclare le Seigneur des armées célestes : Revenez à moi, dit le Seigneur des armées célestes, et je reviendrai à vous, a dit le Seigneur des armées célestes. 4Ne faites pas comme vos ancêtres, que les prophètes d’autrefois ont exhortés en leur disant : « Voici ce que déclare le Seigneur des armées célestes : Abandonnez votre mauvaise conduite et renoncez à vos mauvaises actions. » Mais vos ancêtres n’ont pas écouté, ils n’ont pas prêté attention à mes paroles, l’Eternel le déclare.

5Vos ancêtres où sont-ils à présent ? Et les prophètes, sont-ils toujours en vie ? 6Or mes paroles et mes lois que j’avais ordonné à mes serviteurs les prophètes de leur transmettre, n’ont-elles pas été suivies d’effet pour vos pères ? Alors ils ont changé d’attitude et ils ont reconnu : « Oui, le Seigneur des armées célestes nous a traités comme il avait résolu de le faire, comme le méritaient notre conduite et nos actes. »

Les huit visions nocturnes

Les quatre cavaliers

7La deuxième année du règne de Darius, au vingt-quatrième jour du onzième mois, le mois de Shebath1.7 Le 15 février 519 av. J.-C. Shebath est un nom de mois babylonien., la parole de l’Eternel fut adressée à Zacharie le prophète, fils de Barachie et petit-fils d’Iddo.

8Cette nuit j’ai vu, dans une vision, un cavalier monté sur un cheval roux. Il se tenait parmi les myrtes1.8 Arbustes qui restent toujours verts, croissant dans les régions méditerranéennes surtout dans les fonds de vallées (voir Es 41.19 ; 55.13). dans les profondeurs, et derrière lui, il y avait d’autres chevaux : des roux, des gris-verts et des blancs1.8 Pour les v. 8-11, voir Ap 6.1-8.. 9Je demandai alors : Mon seigneur, que représentent-ils ?

L’ange qui me parlait répondit : Je vais te montrer ce qu’ils représentent.

10Et l’individu qui se tenait parmi les myrtes intervint en disant : Ce sont les coursiers que l’Eternel a envoyés pour parcourir la terre.

11Alors les cavaliers s’adressèrent à l’ange de l’Eternel qui se tenait parmi les myrtes, et lui firent ce rapport : Nous venons de parcourir la terre et nous avons constaté qu’elle est toute tranquille et calme.

12Là-dessus, l’ange de l’Eternel s’exclama : Seigneur des armées célestes, voilà soixante-dix ans1.12 Voir Jr 25.11 ; 29.10. que tu es irrité contre Jérusalem et contre les villes de Juda. Jusques à quand tarderas-tu à les prendre en pitié1.12 Réminiscence en Ap 6.10. ?

13Alors l’Eternel répondit à l’ange qui me parlait par des paroles bienveillantes et des paroles de consolation.

14L’ange qui me parlait me dit : Proclame ces paroles : Voici ce que déclare le Seigneur des armées célestes : J’éprouve pour Jérusalem et pour Sion un amour passionné. 15Et je suis saisi d’une violente indignation contre les peuples ennemis qui vivent dans la tranquillité. Car je n’étais qu’un peu irrité contre mon peuple, mais eux, ils ont accru son malheur. 16C’est pourquoi voici ce que dit l’Eternel : Je me tourne vers Jérusalem avec compassion. Mon temple y sera rebâti – le Seigneur des armées célestes le déclare – et l’on étendra le cordeau d’arpenteur sur Jérusalem.

17Proclame encore ce message : Voici ce que déclare le Seigneur des armées célestes : Mes villes déborderont de nouveau de prospérité, l’Eternel consolera de nouveau Sion et choisira de nouveau Jérusalem.