ዘኍል 2 – NASV & PCB

New Amharic Standard Version

ዘኍል 2:1-34

የየነገዱ አሰፋፈር

1እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴንና አሮንን እንዲህ አላቸው፤ 2“እስራኤላውያን ከምስክሩ ድንኳን ትይዩ ዙሪያውን ጥቂት ራቅ ብለው እያንዳንዱ ሰው በየዐርማውና በየቤተ ሰቡ ምልክት ሥር ይስፈር።”

3በምሥራቅ በኩል በፀሓይ መውጫ፤

የይሁዳ ምድብ፤ በየሰራዊቱና በዐርማቸው ሥር ይስፈር፤ የይሁዳ ሕዝብ አለቃ የአሚናዳብ ልጅ ነአሶን ነው፤ 4የሰራዊቱም ብዛት ሰባ አራት ሺሕ ስድስት መቶ ነው።

5ከእነዚህ ቀጥሎ የይሳኮር ነገድ ይሰፍራል፤ የይሳኮር ሕዝብ አለቃ የሶገር ልጅ ናትናኤል ሲሆን፣ 6የሰራዊቱም ብዛት አምሳ አራት ሺሕ አራት መቶ ነው።

7ከዚያም የዛብሎን ነገድ ይቀጥላል፤ የዛብሎን ሕዝብ አለቃ የኬሎን ልጅ ኤልያብ ሲሆን፣ 8የሰራዊቱም ብዛት አምሳ ሰባት ሺሕ አራት መቶ ነው።

9በየሰራዊታቸው ሆነው ከአይሁድ ምድብ የተመዘገቡ አንድ መቶ ሰማንያ ስድስት ሺሕ አራት መቶ ናቸው፤ እነዚህ አስቀድመው ይወጣሉ።

10በደቡብ በኩል፤

የሮቤል ምድብ ሰራዊት በዐርማቸው ሥር ይሆናል፤ የሮቤል ሕዝብ አለቃ የሰዲዮር ልጅ ኤሊሱር ሲሆን፣ 11የሰራዊቱም ብዛት አርባ ስድስት ሺሕ አምስት መቶ ነው።

12ከእነዚህ ቀጥሎ የስምዖን ነገድ ይሰፍራል፤ የስምዖን ሕዝብ አለቃ የሱሪሰዳይ ልጅ ሰለሚኤል ሲሆን፣ 13የሰራዊቱም ብዛት አምሳ ዘጠኝ ሺሕ ሦስት መቶ ነው።

14ከዚያም የጋድ ነገድ ይቀጥላል፤ የጋድ ሕዝብ አለቃ የራጉኤል2፥14 ብዙ የማሶሬቲክ፣ የኦሪት ሳምራውያንና የቩልጌት ቅጆች ጸዑኤል ይላሉ (ዘኍ 1፥14 ይመ)፤ አያሌ የማሶሬቲክ ቅጆች ግን ከዚህ ይስማማሉ። ልጅ ኤሊሳፍ ሲሆን፣ 15የሰራዊቱም ብዛት አርባ አምስት ሺሕ ስድስት መቶ አምሳ ነው።

16በየሰራዊታቸው ሆነው ከሮቤል ምድብ የተመዘገቡት ወንዶች በሙሉ አንድ መቶ አምሳ አንድ ሺሕ አራት መቶ አምሳ ናቸው፤ እነዚህ ቀጥለው ይመጣሉ።

17ከዚህ በኋላ የመገናኛው ድንኳንና የሌዋውያን ምድብ በመካከል ሆነው ይጓዛሉ፤ እያንዳንዳቸውም አሰፋፈራቸውን በመከተል ቦታቸውን ጠብቀው በዐርማቸው ሥር ይጓዛሉ።

18በምዕራብ በኩል፤

የኤፍሬም ምድብ ሰራዊት በዐርማቸው ሥር ይሆናል፤ የኤፍሬም ሕዝብ አለቃ የዓሚሁድ ልጅ ኤሊሳማ ሲሆን፣ 19የሰራዊቱም ብዛት አርባ ሺሕ አምስት መቶ ነው።

20ከእነዚህም የምናሴ ነገድ ይቀጥላል፣ የምናሴ ሕዝብ አለቃ የፍዳሱር ልጅ ገማልኤል ሲሆን፣ 21የሰራዊቱም ብዛት ሠላሳ ሁለት ሺሕ ሁለት መቶ ነው።

22ከዚያም የብንያም ነገድ ይቀጥላል፣ የብንያም ሕዝብ አለቃ የጋዴዮን ልጅ አቢዳን ሲሆን፣ 23የሰራዊቱም ብዛት ሠላሳ አምስት ሺሕ አራት መቶ ነው።

24በየሰራዊታቸው ሆነው ከኤፍሬም ምድብ የተመዘገቡት ወንዶች በሙሉ አንድ መቶ ስምንት ሺሕ አንድ መቶ ናቸው፤ እነዚህ ሦስተኛ ሆነው ይመጣሉ።

25በሰሜን በኩል፤

የዳን ምድብ ሰራዊት በዐርማው ሥር ይሆናል፤ የዳን ሕዝብ አለቃ የአሚሳዳይ ልጅ አኪዔዘር ሲሆን፣ 26የሰራዊቱም ብዛት ስድሳ ሁለት ሺሕ ሰባት መቶ ነው።

27የአሴር ነገድ ከእነዚህ ቀጥሎ ይሰፍራል፤ የአሴር ሕዝብ አለቃ የኤክራን ልጅ ፋግኤል ሲሆን፣ 28የሰራዊቱም ብዛት አርባ አንድ ሺሕ አምስት መቶ ነው።

29ከዚያም የንፍታሌም ነገድ ይቀጥላል፤ የንፍታሌም ሕዝብ አለቃ የዔናን ልጅ አኪሬ ሲሆን፣ 30የሰራዊቱም ብዛት አምሳ ሦስት ሺሕ አራት መቶ ነው።

31በየሰራዊታቸው ሆነው ከዳን ምድብ የተመዘገቡት ወንዶች ሁሉ አንድ መቶ አምሳ ሰባት ሺሕ ስድስት መቶ ናቸው፤ እነርሱም በዐርማቸው ሥር በመጨረሻ ይመጣሉ።

32በየቤተ ሰባቸው፣ በየምድባቸውና በየሰራዊታቸው የተመዘገቡት እስራኤላውያን ስድስት መቶ ሦስት ሺሕ አምስት መቶ አምሳ ናቸው፤ 33ያም ሆኖ ግን እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን ባዘዘው መሠረት ሌዋውያኑ ከሌሎቹ እስራኤላውያን ጋር አልተቈጠሩም።

34ስለዚህ እስራኤላውያን እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን ያዘዘውን ሁሉ አደረጉ፤ በየዐርማውም ሥር የሰፈሩትና፣ እያንዳንዳቸው በየጐሣቸውና በየቤተ ሰባቸው የተጓዙት በዚህ ሁኔታ ነበር።

Persian Contemporary Bible

اعداد 2:1‏-34

جايگاه قبايل در اردوگاه

1‏-2خداوند اين دستورات را نيز به موسی و هارون داد: «قبايل بنی‌اسرائيل بايد گرداگرد خيمهٔ عبادت با فاصلهٔ معينی از آن اردو بزنند و هر يک عَلَم و نشان ويژهٔ خود را داشته باشند.»

3‏-31جايگاه قبيله‌ها به ترتيب زير بود:

قبيله رهبر تعداديهودا نحشون (پسر عميناداب) ۷۴,۶۰۰ نفريساكار نتنائيل (پسر صوغر) ۵۴,۴۰۰ نفرزبولون الی‌آب (پسر حيلون) ۵۷,۴۰۰ نفر

بنابراين، تعداد كل افراد ساكن در بخش يهودا كه در سمت شرقی اردوگاه قرار داشت، ۱۸۶,۴۰۰ نفر بود. هرگاه بنی‌اسرائيل به مكان تازه‌ای كوچ می‌كردند، اين سه قبيله به ترتيب، پيشاپيش حركت می‌كردند و راه را نشان می‌دادند.

قبيله رهبر تعدادرئوبين اليصور (پسر شدی‌ئور) ۴۶,۵۰۰ نفرشمعون شلومی‌ئيل (پسر صوريشدای) ۵۹,۳۰۰ نفرجاد الياساف (پسر دعوئيل) ۴۵,۶۵۰ نفر

بنابراين، تعداد كل افراد ساكن در بخش رئوبين كه در سمت جنوبی اردوگاه قرار داشت، ۱۵۱,۴۵۰ نفر بود. هر وقت بنی‌اسرائيل كوچ می‌كردند، اين سه قبيله به ترتيب در رديف بعدی قرار می‌گرفتند.

پشت سر اين دو رديف، لاویان با خيمهٔ عبادت حركت می‌كردند. هنگام كوچ، افراد هر قبيله زير علم خاص خود، دسته جمعی حركت می‌كردند، به همان ترتيبی كه در اردوگاه، هر قبيله از قبيلهٔ ديگر جدا بود.

قبيله رهبر تعدادافرايم اليشمع (پسر عميهود) ۴۰,۵۰۰ نفرمنسی جملی‌ئيل (پسر فدهصور) ۳۲,۲۰۰ نفربنيامين ابيدان (پسر جدعونی) ۳۵,۴۰۰ نفر

بنابراين، تعداد كل افراد ساكن در بخش افرايم كه در سمت غربی اردوگاه قرار داشت، ۱۰۸,۱۰۰ نفر بود. موقع كوچ كردن، اين سه قبيله به ترتيب در رديف بعدی قرار داشتند.

قبيله رهبر تعداددان اخيعزر (پسر عميشدای) ۶۲,۷۰۰ نفراشير فجعی‌ئيل (پسر عكران) ۴۱,۵۰۰ نفرنفتالی اخيرع (پسر عينان) ۵۳,۴۰۰ نفر

بنابراين، تعداد كل افراد ساكن در بخش دان كه در سمت شمالی اردوگاه قرار داشت، ۱۵۷,۶۰۰ نفر بود. هنگام كوچ، اين سه قبيله به ترتيب، پس از همه حركت می‌كردند. 32‏-33پس تعداد كل سپاهيان بنی‌اسرائيل، ۶۰۳,۵۵۰ نفر بود (غير از لاویان كه به دستور خداوند سرشماری نشدند). 34به اين ترتيب قوم اسرائيل طبق دستوری كه خداوند به موسی داده بود، هر يک با خاندان و خانوادهٔ خود كوچ می‌كرد و زير عَلَم قبيلهٔ خود اردو می‌زد.