ዘኍል 2 – NASV & OL

New Amharic Standard Version

ዘኍል 2:1-34

የየነገዱ አሰፋፈር

1እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴንና አሮንን እንዲህ አላቸው፤ 2“እስራኤላውያን ከምስክሩ ድንኳን ትይዩ ዙሪያውን ጥቂት ራቅ ብለው እያንዳንዱ ሰው በየዐርማውና በየቤተ ሰቡ ምልክት ሥር ይስፈር።”

3በምሥራቅ በኩል በፀሓይ መውጫ፤

የይሁዳ ምድብ፤ በየሰራዊቱና በዐርማቸው ሥር ይስፈር፤ የይሁዳ ሕዝብ አለቃ የአሚናዳብ ልጅ ነአሶን ነው፤ 4የሰራዊቱም ብዛት ሰባ አራት ሺሕ ስድስት መቶ ነው።

5ከእነዚህ ቀጥሎ የይሳኮር ነገድ ይሰፍራል፤ የይሳኮር ሕዝብ አለቃ የሶገር ልጅ ናትናኤል ሲሆን፣ 6የሰራዊቱም ብዛት አምሳ አራት ሺሕ አራት መቶ ነው።

7ከዚያም የዛብሎን ነገድ ይቀጥላል፤ የዛብሎን ሕዝብ አለቃ የኬሎን ልጅ ኤልያብ ሲሆን፣ 8የሰራዊቱም ብዛት አምሳ ሰባት ሺሕ አራት መቶ ነው።

9በየሰራዊታቸው ሆነው ከአይሁድ ምድብ የተመዘገቡ አንድ መቶ ሰማንያ ስድስት ሺሕ አራት መቶ ናቸው፤ እነዚህ አስቀድመው ይወጣሉ።

10በደቡብ በኩል፤

የሮቤል ምድብ ሰራዊት በዐርማቸው ሥር ይሆናል፤ የሮቤል ሕዝብ አለቃ የሰዲዮር ልጅ ኤሊሱር ሲሆን፣ 11የሰራዊቱም ብዛት አርባ ስድስት ሺሕ አምስት መቶ ነው።

12ከእነዚህ ቀጥሎ የስምዖን ነገድ ይሰፍራል፤ የስምዖን ሕዝብ አለቃ የሱሪሰዳይ ልጅ ሰለሚኤል ሲሆን፣ 13የሰራዊቱም ብዛት አምሳ ዘጠኝ ሺሕ ሦስት መቶ ነው።

14ከዚያም የጋድ ነገድ ይቀጥላል፤ የጋድ ሕዝብ አለቃ የራጉኤል2፥14 ብዙ የማሶሬቲክ፣ የኦሪት ሳምራውያንና የቩልጌት ቅጆች ጸዑኤል ይላሉ (ዘኍ 1፥14 ይመ)፤ አያሌ የማሶሬቲክ ቅጆች ግን ከዚህ ይስማማሉ። ልጅ ኤሊሳፍ ሲሆን፣ 15የሰራዊቱም ብዛት አርባ አምስት ሺሕ ስድስት መቶ አምሳ ነው።

16በየሰራዊታቸው ሆነው ከሮቤል ምድብ የተመዘገቡት ወንዶች በሙሉ አንድ መቶ አምሳ አንድ ሺሕ አራት መቶ አምሳ ናቸው፤ እነዚህ ቀጥለው ይመጣሉ።

17ከዚህ በኋላ የመገናኛው ድንኳንና የሌዋውያን ምድብ በመካከል ሆነው ይጓዛሉ፤ እያንዳንዳቸውም አሰፋፈራቸውን በመከተል ቦታቸውን ጠብቀው በዐርማቸው ሥር ይጓዛሉ።

18በምዕራብ በኩል፤

የኤፍሬም ምድብ ሰራዊት በዐርማቸው ሥር ይሆናል፤ የኤፍሬም ሕዝብ አለቃ የዓሚሁድ ልጅ ኤሊሳማ ሲሆን፣ 19የሰራዊቱም ብዛት አርባ ሺሕ አምስት መቶ ነው።

20ከእነዚህም የምናሴ ነገድ ይቀጥላል፣ የምናሴ ሕዝብ አለቃ የፍዳሱር ልጅ ገማልኤል ሲሆን፣ 21የሰራዊቱም ብዛት ሠላሳ ሁለት ሺሕ ሁለት መቶ ነው።

22ከዚያም የብንያም ነገድ ይቀጥላል፣ የብንያም ሕዝብ አለቃ የጋዴዮን ልጅ አቢዳን ሲሆን፣ 23የሰራዊቱም ብዛት ሠላሳ አምስት ሺሕ አራት መቶ ነው።

24በየሰራዊታቸው ሆነው ከኤፍሬም ምድብ የተመዘገቡት ወንዶች በሙሉ አንድ መቶ ስምንት ሺሕ አንድ መቶ ናቸው፤ እነዚህ ሦስተኛ ሆነው ይመጣሉ።

25በሰሜን በኩል፤

የዳን ምድብ ሰራዊት በዐርማው ሥር ይሆናል፤ የዳን ሕዝብ አለቃ የአሚሳዳይ ልጅ አኪዔዘር ሲሆን፣ 26የሰራዊቱም ብዛት ስድሳ ሁለት ሺሕ ሰባት መቶ ነው።

27የአሴር ነገድ ከእነዚህ ቀጥሎ ይሰፍራል፤ የአሴር ሕዝብ አለቃ የኤክራን ልጅ ፋግኤል ሲሆን፣ 28የሰራዊቱም ብዛት አርባ አንድ ሺሕ አምስት መቶ ነው።

29ከዚያም የንፍታሌም ነገድ ይቀጥላል፤ የንፍታሌም ሕዝብ አለቃ የዔናን ልጅ አኪሬ ሲሆን፣ 30የሰራዊቱም ብዛት አምሳ ሦስት ሺሕ አራት መቶ ነው።

31በየሰራዊታቸው ሆነው ከዳን ምድብ የተመዘገቡት ወንዶች ሁሉ አንድ መቶ አምሳ ሰባት ሺሕ ስድስት መቶ ናቸው፤ እነርሱም በዐርማቸው ሥር በመጨረሻ ይመጣሉ።

32በየቤተ ሰባቸው፣ በየምድባቸውና በየሰራዊታቸው የተመዘገቡት እስራኤላውያን ስድስት መቶ ሦስት ሺሕ አምስት መቶ አምሳ ናቸው፤ 33ያም ሆኖ ግን እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን ባዘዘው መሠረት ሌዋውያኑ ከሌሎቹ እስራኤላውያን ጋር አልተቈጠሩም።

34ስለዚህ እስራኤላውያን እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን ያዘዘውን ሁሉ አደረጉ፤ በየዐርማውም ሥር የሰፈሩትና፣ እያንዳንዳቸው በየጐሣቸውና በየቤተ ሰባቸው የተጓዙት በዚህ ሁኔታ ነበር።

O Livro

Números 2:1-34

Disposição das tribos quando acampadas

1O Senhor deu mais as seguintes ordens a Moisés e a Aarão: 2“Cada tribo deverá ter o seu próprio espaço para instalar as tendas, cada uma sob o respetivo pendão e cada família com a respetiva insígnia, e hão de dispor-se de forma a que fiquem no meio da tenda do encontro.”

3-31Será assim a sua localização relativa:

Tribo Chefe Localização Membros recenseadosJudá Nassom, filho de Aminadabe A oriente 74 600Issacar Netanel, filho de Zuar Junto de Judá 54 400Zebulão Eliabe, filho de Helom Junto de Issacar 57 400

Portanto, o total de todos aqueles que acampavam do lado de Judá era de 186 400. Estas três tribos eram as que seguiam à frente, quando todo o povo tinha de se deslocar para se instalar noutro sítio.

Rúben Elizur, filho de Sedeur A sul 46 500Simeão Selumiel, filho de Zurisadai Junto de Rúben 59 300Gad Eliasafe, filho de Deuel Junto de Simeão 45 650

O total dos que ficavam do lado de Rúben foi pois de 151 450. E iam após o grupo anterior quando tinham que viajar. Só então vinha a tenda do encontro com os levitas. Sempre que se deslocavam, cada tribo mantinha-se sob a sua própria bandeira, tal como quando estavam acampados, separadas umas das outras.

Efraim Elisama, filho de Amiude A ocidente 40 500Manassés Gamaliel, filho de Pedazur Junto de Efraim 32 200Benjamim Abidã, filho de Gideoni Junto de Manassés 35 400

O total dos que faziam este conjunto com Efraim foi assim de 108 100; seguiam após os outros na linha de marcha.

Dan Aiezer, filho de Amisadai A norte 62 700Aser Pagiel, filho de Ocrã Junto de Dan41 500Naftali Airá, filho de Enã Junto de Aser 53 400

Era pois o total dos que estavam do lado de Dan 157 600, e fechavam a coluna de marcha nas deslocações do povo.

32Os exércitos de Israel totalizavam 603 550 indivíduos. 33Não incluía os levitas, que não eram tidos nessa contagem, conforme a indicação de Senhor a Moisés.

34Estabelecia assim o povo de Israel os seus acampamentos; cada tribo sob o seu estandarte, no local que o Senhor mostrava a Moisés.