ዘኍል 2 – NASV & NVI-PT

New Amharic Standard Version

ዘኍል 2:1-34

የየነገዱ አሰፋፈር

1እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴንና አሮንን እንዲህ አላቸው፤ 2“እስራኤላውያን ከምስክሩ ድንኳን ትይዩ ዙሪያውን ጥቂት ራቅ ብለው እያንዳንዱ ሰው በየዐርማውና በየቤተ ሰቡ ምልክት ሥር ይስፈር።”

3በምሥራቅ በኩል በፀሓይ መውጫ፤

የይሁዳ ምድብ፤ በየሰራዊቱና በዐርማቸው ሥር ይስፈር፤ የይሁዳ ሕዝብ አለቃ የአሚናዳብ ልጅ ነአሶን ነው፤ 4የሰራዊቱም ብዛት ሰባ አራት ሺሕ ስድስት መቶ ነው።

5ከእነዚህ ቀጥሎ የይሳኮር ነገድ ይሰፍራል፤ የይሳኮር ሕዝብ አለቃ የሶገር ልጅ ናትናኤል ሲሆን፣ 6የሰራዊቱም ብዛት አምሳ አራት ሺሕ አራት መቶ ነው።

7ከዚያም የዛብሎን ነገድ ይቀጥላል፤ የዛብሎን ሕዝብ አለቃ የኬሎን ልጅ ኤልያብ ሲሆን፣ 8የሰራዊቱም ብዛት አምሳ ሰባት ሺሕ አራት መቶ ነው።

9በየሰራዊታቸው ሆነው ከአይሁድ ምድብ የተመዘገቡ አንድ መቶ ሰማንያ ስድስት ሺሕ አራት መቶ ናቸው፤ እነዚህ አስቀድመው ይወጣሉ።

10በደቡብ በኩል፤

የሮቤል ምድብ ሰራዊት በዐርማቸው ሥር ይሆናል፤ የሮቤል ሕዝብ አለቃ የሰዲዮር ልጅ ኤሊሱር ሲሆን፣ 11የሰራዊቱም ብዛት አርባ ስድስት ሺሕ አምስት መቶ ነው።

12ከእነዚህ ቀጥሎ የስምዖን ነገድ ይሰፍራል፤ የስምዖን ሕዝብ አለቃ የሱሪሰዳይ ልጅ ሰለሚኤል ሲሆን፣ 13የሰራዊቱም ብዛት አምሳ ዘጠኝ ሺሕ ሦስት መቶ ነው።

14ከዚያም የጋድ ነገድ ይቀጥላል፤ የጋድ ሕዝብ አለቃ የራጉኤል2፥14 ብዙ የማሶሬቲክ፣ የኦሪት ሳምራውያንና የቩልጌት ቅጆች ጸዑኤል ይላሉ (ዘኍ 1፥14 ይመ)፤ አያሌ የማሶሬቲክ ቅጆች ግን ከዚህ ይስማማሉ። ልጅ ኤሊሳፍ ሲሆን፣ 15የሰራዊቱም ብዛት አርባ አምስት ሺሕ ስድስት መቶ አምሳ ነው።

16በየሰራዊታቸው ሆነው ከሮቤል ምድብ የተመዘገቡት ወንዶች በሙሉ አንድ መቶ አምሳ አንድ ሺሕ አራት መቶ አምሳ ናቸው፤ እነዚህ ቀጥለው ይመጣሉ።

17ከዚህ በኋላ የመገናኛው ድንኳንና የሌዋውያን ምድብ በመካከል ሆነው ይጓዛሉ፤ እያንዳንዳቸውም አሰፋፈራቸውን በመከተል ቦታቸውን ጠብቀው በዐርማቸው ሥር ይጓዛሉ።

18በምዕራብ በኩል፤

የኤፍሬም ምድብ ሰራዊት በዐርማቸው ሥር ይሆናል፤ የኤፍሬም ሕዝብ አለቃ የዓሚሁድ ልጅ ኤሊሳማ ሲሆን፣ 19የሰራዊቱም ብዛት አርባ ሺሕ አምስት መቶ ነው።

20ከእነዚህም የምናሴ ነገድ ይቀጥላል፣ የምናሴ ሕዝብ አለቃ የፍዳሱር ልጅ ገማልኤል ሲሆን፣ 21የሰራዊቱም ብዛት ሠላሳ ሁለት ሺሕ ሁለት መቶ ነው።

22ከዚያም የብንያም ነገድ ይቀጥላል፣ የብንያም ሕዝብ አለቃ የጋዴዮን ልጅ አቢዳን ሲሆን፣ 23የሰራዊቱም ብዛት ሠላሳ አምስት ሺሕ አራት መቶ ነው።

24በየሰራዊታቸው ሆነው ከኤፍሬም ምድብ የተመዘገቡት ወንዶች በሙሉ አንድ መቶ ስምንት ሺሕ አንድ መቶ ናቸው፤ እነዚህ ሦስተኛ ሆነው ይመጣሉ።

25በሰሜን በኩል፤

የዳን ምድብ ሰራዊት በዐርማው ሥር ይሆናል፤ የዳን ሕዝብ አለቃ የአሚሳዳይ ልጅ አኪዔዘር ሲሆን፣ 26የሰራዊቱም ብዛት ስድሳ ሁለት ሺሕ ሰባት መቶ ነው።

27የአሴር ነገድ ከእነዚህ ቀጥሎ ይሰፍራል፤ የአሴር ሕዝብ አለቃ የኤክራን ልጅ ፋግኤል ሲሆን፣ 28የሰራዊቱም ብዛት አርባ አንድ ሺሕ አምስት መቶ ነው።

29ከዚያም የንፍታሌም ነገድ ይቀጥላል፤ የንፍታሌም ሕዝብ አለቃ የዔናን ልጅ አኪሬ ሲሆን፣ 30የሰራዊቱም ብዛት አምሳ ሦስት ሺሕ አራት መቶ ነው።

31በየሰራዊታቸው ሆነው ከዳን ምድብ የተመዘገቡት ወንዶች ሁሉ አንድ መቶ አምሳ ሰባት ሺሕ ስድስት መቶ ናቸው፤ እነርሱም በዐርማቸው ሥር በመጨረሻ ይመጣሉ።

32በየቤተ ሰባቸው፣ በየምድባቸውና በየሰራዊታቸው የተመዘገቡት እስራኤላውያን ስድስት መቶ ሦስት ሺሕ አምስት መቶ አምሳ ናቸው፤ 33ያም ሆኖ ግን እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን ባዘዘው መሠረት ሌዋውያኑ ከሌሎቹ እስራኤላውያን ጋር አልተቈጠሩም።

34ስለዚህ እስራኤላውያን እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን ያዘዘውን ሁሉ አደረጉ፤ በየዐርማውም ሥር የሰፈሩትና፣ እያንዳንዳቸው በየጐሣቸውና በየቤተ ሰባቸው የተጓዙት በዚህ ሁኔታ ነበር።

Nova Versão Internacional

Números 2:1-34

A Disposição das Tribos no Acampamento

1O Senhor disse a Moisés e a Arão: 2“Os israelitas acamparão ao redor da Tenda do Encontro, a certa distância, cada homem junto à sua bandeira com os emblemas da sua família”.

3A leste, os exércitos de Judá acamparão junto à sua bandeira.

O líder de Judá será Naassom, filho de Aminadabe. 4Seu exército é de 74.600 homens.

5A tribo de Issacar acampará ao lado de Judá. O líder de Issacar será Natanael, filho de Zuar. 6Seu exército é de 54.400 homens.

7A tribo de Zebulom virá em seguida. O líder de Zebulom será Eliabe, filho de Helom. 8Seu exército é de 57.400 homens.

9O número total dos homens recenseados do acampamento de Judá, de acordo com os seus exércitos, foi 186.400. Esses marcharão primeiro.

10Ao sul estarão os exércitos do acampamento de Rúben, junto à sua bandeira.

O líder de Rúben será Elizur, filho de Sedeur. 11Seu exército é de 46.500 homens.

12A tribo de Simeão acampará ao lado de Rúben. O líder de Simeão será Selumiel, filho de Zurisadai. 13Seu exército é de 59.300 homens.

14A tribo de Gade virá em seguida. O líder de Gade será Eliasafe, filho de Deuel2.14 Alguns manuscritos dizem Reuel.. 15Seu exército é de 45.650 homens.

16O número total dos homens recenseados do acampamento de Rúben, de acordo com os seus exércitos, foi 151.450. Esses marcharão em segundo lugar.

17Em seguida, os levitas marcharão levando a Tenda do Encontro no meio dos outros acampamentos, na mesma ordem em que acamparem, cada um em seu próprio lugar, junto à sua bandeira.

18A oeste estarão os exércitos do acampamento de Efraim, junto à sua bandeira.

O líder de Efraim será Elisama, filho de Amiúde. 19Seu exército é de 40.500 homens.

20A tribo de Manassés acampará ao lado de Efraim. O líder de Manassés será Gamaliel, filho de Pedazur. 21Seu exército é de 32.200 homens.

22A tribo de Benjamim virá em seguida. O líder de Benjamim será Abidã, filho de Gideoni. 23Seu exército é de 35.400 homens.

24O número total dos homens recenseados do acampamento de Efraim, de acordo com os seus exércitos, foi 108.100. Esses marcharão em terceiro lugar.

25Ao norte estarão os exércitos do acampamento de Dã, junto à sua bandeira.

O líder de Dã será Aieser, filho de Amisadai. 26Seu exército é de 62.700 homens.

27A tribo de Aser acampará ao lado de Dã. O líder de Aser será Pagiel, filho de Ocrã. 28Seu exército é de 41.500 homens.

29A tribo de Naftali virá em seguida. O líder de Naftali será Aira, filho de Enã. 30Seu exército é de 53.400 homens.

31O número total dos homens recenseados do acampamento de Dã, de acordo com os seus exércitos, foi 157.600. Esses marcharão por último, junto às suas bandeiras.

32Foram esses os israelitas contados de acordo com as suas famílias. O número total dos que foram contados nos acampamentos, de acordo com os seus exércitos, foi 603.550. 33Os levitas, contudo, não foram contados com os outros israelitas, conforme o Senhor tinha ordenado a Moisés.

34Assim os israelitas fizeram tudo o que o Senhor tinha ordenado a Moisés; eles acampavam junto às suas bandeiras e depois partiam, cada um com o seu clã e com a sua família.