ዘኍል 2 – NASV & NEN

New Amharic Standard Version

ዘኍል 2:1-34

የየነገዱ አሰፋፈር

1እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴንና አሮንን እንዲህ አላቸው፤ 2“እስራኤላውያን ከምስክሩ ድንኳን ትይዩ ዙሪያውን ጥቂት ራቅ ብለው እያንዳንዱ ሰው በየዐርማውና በየቤተ ሰቡ ምልክት ሥር ይስፈር።”

3በምሥራቅ በኩል በፀሓይ መውጫ፤

የይሁዳ ምድብ፤ በየሰራዊቱና በዐርማቸው ሥር ይስፈር፤ የይሁዳ ሕዝብ አለቃ የአሚናዳብ ልጅ ነአሶን ነው፤ 4የሰራዊቱም ብዛት ሰባ አራት ሺሕ ስድስት መቶ ነው።

5ከእነዚህ ቀጥሎ የይሳኮር ነገድ ይሰፍራል፤ የይሳኮር ሕዝብ አለቃ የሶገር ልጅ ናትናኤል ሲሆን፣ 6የሰራዊቱም ብዛት አምሳ አራት ሺሕ አራት መቶ ነው።

7ከዚያም የዛብሎን ነገድ ይቀጥላል፤ የዛብሎን ሕዝብ አለቃ የኬሎን ልጅ ኤልያብ ሲሆን፣ 8የሰራዊቱም ብዛት አምሳ ሰባት ሺሕ አራት መቶ ነው።

9በየሰራዊታቸው ሆነው ከአይሁድ ምድብ የተመዘገቡ አንድ መቶ ሰማንያ ስድስት ሺሕ አራት መቶ ናቸው፤ እነዚህ አስቀድመው ይወጣሉ።

10በደቡብ በኩል፤

የሮቤል ምድብ ሰራዊት በዐርማቸው ሥር ይሆናል፤ የሮቤል ሕዝብ አለቃ የሰዲዮር ልጅ ኤሊሱር ሲሆን፣ 11የሰራዊቱም ብዛት አርባ ስድስት ሺሕ አምስት መቶ ነው።

12ከእነዚህ ቀጥሎ የስምዖን ነገድ ይሰፍራል፤ የስምዖን ሕዝብ አለቃ የሱሪሰዳይ ልጅ ሰለሚኤል ሲሆን፣ 13የሰራዊቱም ብዛት አምሳ ዘጠኝ ሺሕ ሦስት መቶ ነው።

14ከዚያም የጋድ ነገድ ይቀጥላል፤ የጋድ ሕዝብ አለቃ የራጉኤል2፥14 ብዙ የማሶሬቲክ፣ የኦሪት ሳምራውያንና የቩልጌት ቅጆች ጸዑኤል ይላሉ (ዘኍ 1፥14 ይመ)፤ አያሌ የማሶሬቲክ ቅጆች ግን ከዚህ ይስማማሉ። ልጅ ኤሊሳፍ ሲሆን፣ 15የሰራዊቱም ብዛት አርባ አምስት ሺሕ ስድስት መቶ አምሳ ነው።

16በየሰራዊታቸው ሆነው ከሮቤል ምድብ የተመዘገቡት ወንዶች በሙሉ አንድ መቶ አምሳ አንድ ሺሕ አራት መቶ አምሳ ናቸው፤ እነዚህ ቀጥለው ይመጣሉ።

17ከዚህ በኋላ የመገናኛው ድንኳንና የሌዋውያን ምድብ በመካከል ሆነው ይጓዛሉ፤ እያንዳንዳቸውም አሰፋፈራቸውን በመከተል ቦታቸውን ጠብቀው በዐርማቸው ሥር ይጓዛሉ።

18በምዕራብ በኩል፤

የኤፍሬም ምድብ ሰራዊት በዐርማቸው ሥር ይሆናል፤ የኤፍሬም ሕዝብ አለቃ የዓሚሁድ ልጅ ኤሊሳማ ሲሆን፣ 19የሰራዊቱም ብዛት አርባ ሺሕ አምስት መቶ ነው።

20ከእነዚህም የምናሴ ነገድ ይቀጥላል፣ የምናሴ ሕዝብ አለቃ የፍዳሱር ልጅ ገማልኤል ሲሆን፣ 21የሰራዊቱም ብዛት ሠላሳ ሁለት ሺሕ ሁለት መቶ ነው።

22ከዚያም የብንያም ነገድ ይቀጥላል፣ የብንያም ሕዝብ አለቃ የጋዴዮን ልጅ አቢዳን ሲሆን፣ 23የሰራዊቱም ብዛት ሠላሳ አምስት ሺሕ አራት መቶ ነው።

24በየሰራዊታቸው ሆነው ከኤፍሬም ምድብ የተመዘገቡት ወንዶች በሙሉ አንድ መቶ ስምንት ሺሕ አንድ መቶ ናቸው፤ እነዚህ ሦስተኛ ሆነው ይመጣሉ።

25በሰሜን በኩል፤

የዳን ምድብ ሰራዊት በዐርማው ሥር ይሆናል፤ የዳን ሕዝብ አለቃ የአሚሳዳይ ልጅ አኪዔዘር ሲሆን፣ 26የሰራዊቱም ብዛት ስድሳ ሁለት ሺሕ ሰባት መቶ ነው።

27የአሴር ነገድ ከእነዚህ ቀጥሎ ይሰፍራል፤ የአሴር ሕዝብ አለቃ የኤክራን ልጅ ፋግኤል ሲሆን፣ 28የሰራዊቱም ብዛት አርባ አንድ ሺሕ አምስት መቶ ነው።

29ከዚያም የንፍታሌም ነገድ ይቀጥላል፤ የንፍታሌም ሕዝብ አለቃ የዔናን ልጅ አኪሬ ሲሆን፣ 30የሰራዊቱም ብዛት አምሳ ሦስት ሺሕ አራት መቶ ነው።

31በየሰራዊታቸው ሆነው ከዳን ምድብ የተመዘገቡት ወንዶች ሁሉ አንድ መቶ አምሳ ሰባት ሺሕ ስድስት መቶ ናቸው፤ እነርሱም በዐርማቸው ሥር በመጨረሻ ይመጣሉ።

32በየቤተ ሰባቸው፣ በየምድባቸውና በየሰራዊታቸው የተመዘገቡት እስራኤላውያን ስድስት መቶ ሦስት ሺሕ አምስት መቶ አምሳ ናቸው፤ 33ያም ሆኖ ግን እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን ባዘዘው መሠረት ሌዋውያኑ ከሌሎቹ እስራኤላውያን ጋር አልተቈጠሩም።

34ስለዚህ እስራኤላውያን እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን ያዘዘውን ሁሉ አደረጉ፤ በየዐርማውም ሥር የሰፈሩትና፣ እያንዳንዳቸው በየጐሣቸውና በየቤተ ሰባቸው የተጓዙት በዚህ ሁኔታ ነበር።

Kiswahili Contemporary Version (Neno: Bibilia Takatifu)

Hesabu 2:1-34

Mpangilio Wa Kambi Za Makabila

1Bwana aliwaambia Mose na Aroni: 22:2 Za 74:4; Isa 31:9; Yer 4:21“Waisraeli watapiga kambi zao kuzunguka Hema la Kukutania kwa umbali fulani kutoka kwenye hema, kila mwanaume chini ya alama yake pamoja na bendera ya jamaa yake.”

32:3 Hes 6:23; Rut 4:20; 1Nya 2:10; Lk 3:32-33; Hes 10:14Kwa upande wa mashariki kuelekea mawio ya jua, kambi ya makundi ya Yuda watapiga kambi chini ya alama yao. Kiongozi wa watu wa Yuda ni Nashoni mwana wa Aminadabu. 4Kundi lake lina watu 74,600.

52:5 Hes 1:8; 10:15Kabila la Isakari watapiga kambi karibu na Yuda. Kiongozi wa watu wa Isakari ni Nethaneli mwana wa Suari. 62:6 Hes 26:25Kundi lake lina watu 54,400.

72:7 Hes 1:9; 10:16; Mwa 49:13; Kum 33:18Kabila la Zabuloni litafuata. Kiongozi wa watu wa Zabuloni ni Eliabu mwana wa Heloni. 8Kundi lake lina watu 57,400.

92:9 Hes 10:14; Amu 1:1; 1Nya 5:2; Za 78:52Wanaume wote walio katika kambi ya Yuda, kufuatana na makundi yao, ni 186,400. Wao watatangulia kuondoka.

102:10 Hes 1:5, 53; Kum 33:6Kwa upande wa kusini kutakuwa kambi ya makundi ya Reubeni chini ya alama yao. Kiongozi wa watu wa Reubeni ni Elisuri mwana wa Shedeuri. 11Kundi lake lina watu 46,500.

122:12 Hes 10:19; 1:6Kabila la Simeoni watapiga kambi karibu na Reubeni. Kiongozi wa watu wa Simeoni ni Shelumieli mwana wa Surishadai. 13Kundi lake lina watu 59,300.

142:14 Hes 10:20; 1:14Kabila la Gadi litafuata. Kiongozi wa watu wa Gadi ni Eliasafu mwana wa Deueli. 15Kundi lake lina watu 45,650.

162:16 Hes 10:18; Mwa 49:3Wanaume wote walio katika kambi ya Reubeni, kufuatana na makundi yao, ni 151,450. Nao watakuwa nafasi ya pili kuondoka.

172:17 Hes 1:50; 10:21; Mdo 4:4; Ebr 8:2; 1Kor 14:40Kisha Hema la Kukutania na kambi ya Walawi vitakuwa katikati ya kambi zote. Wao watasafiri kwa utaratibu ule ule kama walivyopiga kambi, kila mmoja mahali pake mwenyewe chini ya alama yake.

182:18 Hes 1:10, 53; Mwa 48:20; Yer 31:18-20; Za 80:1; Hos 11:3Upande wa magharibi kutakuwepo na kambi ya makundi ya Efraimu chini ya alama yao. Kiongozi wa watu wa Efraimu ni Elishama mwana wa Amihudi. 19Kundi lake lina watu 40,500.

202:20 Mwa 48:20; Hes 1:10Kabila la Manase litafuata baada ya Efraimu. Kiongozi wa watu wa Manase ni Gamalieli mwana wa Pedasuri. 21Kundi lake lina watu 32,200.

222:22 Hes 10:24; 1:11; Za 68:27Kabila la Benyamini litafuata baada ya Manase. Kiongozi wa watu wa Benyamini ni Abidani mwana wa Gideoni. 23Kundi lake lina watu 35,400.

242:24 Hes 10:22; Za 80:2Wanaume wote walio katika kambi ya Efraimu kufuatana na makundi yao ni 108,100. Nao watakuwa nafasi ya tatu kuondoka.

252:25 Hes 1:22, 53; 10:25; Kum 32:22Upande wa kaskazini kutakuwa na makundi ya kambi ya Dani, chini ya alama yao. Kiongozi wa watu wa Dani ni Ahiezeri mwana wa Amishadai. 26Kundi lake lina watu 62,700.

272:27 Hes 1:13; 10:26Kabila la Asheri watapiga kambi karibu na Dani. Kiongozi wa watu wa Asheri ni Pagieli mwana wa Okrani. 28Kundi lake lina watu 41,500.

292:29 Hes 1:15; 10:27; Mwa 30:8; 49:21; 2Fal 15:29Kabila la Naftali litafuata. Kiongozi wa watu wa Naftali ni Ahira mwana wa Enani. 30Kundi lake lina watu 53,400.

312:31 Hes 10:25; Yos 6:9Wanaume wote walio katika kambi ya Dani ni 157,600. Wao watakuwa wa mwisho kuondoka chini ya alama yao.

322:32 Hes 1:45; Kut 12:35-37; 38:26Hawa ndio Waisraeli, wakiwa wamehesabiwa kufuatana na jamaa zao. Wote walio kambini kwa makundi yao ni watu 603,550. 332:33 Hes 1:47; 26:57-62Hata hivyo, Walawi hawakuhesabiwa pamoja na Waisraeli wengine, kama Bwana alivyomwagiza Mose.

342:34 Kut 12:37; Hes 24:2, 9; Isa 45:12Kwa hiyo Waisraeli wakafanya kila kitu Bwana alichomwamuru Mose. Hivyo ndivyo walivyopiga kambi chini ya alama zao, pia hivyo ndivyo walivyoondoka, kila mmoja akiwa na ukoo wake na jamaa yake.