ዘኍል 2 – NASV & CARSA

New Amharic Standard Version

ዘኍል 2:1-34

የየነገዱ አሰፋፈር

1እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴንና አሮንን እንዲህ አላቸው፤ 2“እስራኤላውያን ከምስክሩ ድንኳን ትይዩ ዙሪያውን ጥቂት ራቅ ብለው እያንዳንዱ ሰው በየዐርማውና በየቤተ ሰቡ ምልክት ሥር ይስፈር።”

3በምሥራቅ በኩል በፀሓይ መውጫ፤

የይሁዳ ምድብ፤ በየሰራዊቱና በዐርማቸው ሥር ይስፈር፤ የይሁዳ ሕዝብ አለቃ የአሚናዳብ ልጅ ነአሶን ነው፤ 4የሰራዊቱም ብዛት ሰባ አራት ሺሕ ስድስት መቶ ነው።

5ከእነዚህ ቀጥሎ የይሳኮር ነገድ ይሰፍራል፤ የይሳኮር ሕዝብ አለቃ የሶገር ልጅ ናትናኤል ሲሆን፣ 6የሰራዊቱም ብዛት አምሳ አራት ሺሕ አራት መቶ ነው።

7ከዚያም የዛብሎን ነገድ ይቀጥላል፤ የዛብሎን ሕዝብ አለቃ የኬሎን ልጅ ኤልያብ ሲሆን፣ 8የሰራዊቱም ብዛት አምሳ ሰባት ሺሕ አራት መቶ ነው።

9በየሰራዊታቸው ሆነው ከአይሁድ ምድብ የተመዘገቡ አንድ መቶ ሰማንያ ስድስት ሺሕ አራት መቶ ናቸው፤ እነዚህ አስቀድመው ይወጣሉ።

10በደቡብ በኩል፤

የሮቤል ምድብ ሰራዊት በዐርማቸው ሥር ይሆናል፤ የሮቤል ሕዝብ አለቃ የሰዲዮር ልጅ ኤሊሱር ሲሆን፣ 11የሰራዊቱም ብዛት አርባ ስድስት ሺሕ አምስት መቶ ነው።

12ከእነዚህ ቀጥሎ የስምዖን ነገድ ይሰፍራል፤ የስምዖን ሕዝብ አለቃ የሱሪሰዳይ ልጅ ሰለሚኤል ሲሆን፣ 13የሰራዊቱም ብዛት አምሳ ዘጠኝ ሺሕ ሦስት መቶ ነው።

14ከዚያም የጋድ ነገድ ይቀጥላል፤ የጋድ ሕዝብ አለቃ የራጉኤል2፥14 ብዙ የማሶሬቲክ፣ የኦሪት ሳምራውያንና የቩልጌት ቅጆች ጸዑኤል ይላሉ (ዘኍ 1፥14 ይመ)፤ አያሌ የማሶሬቲክ ቅጆች ግን ከዚህ ይስማማሉ። ልጅ ኤሊሳፍ ሲሆን፣ 15የሰራዊቱም ብዛት አርባ አምስት ሺሕ ስድስት መቶ አምሳ ነው።

16በየሰራዊታቸው ሆነው ከሮቤል ምድብ የተመዘገቡት ወንዶች በሙሉ አንድ መቶ አምሳ አንድ ሺሕ አራት መቶ አምሳ ናቸው፤ እነዚህ ቀጥለው ይመጣሉ።

17ከዚህ በኋላ የመገናኛው ድንኳንና የሌዋውያን ምድብ በመካከል ሆነው ይጓዛሉ፤ እያንዳንዳቸውም አሰፋፈራቸውን በመከተል ቦታቸውን ጠብቀው በዐርማቸው ሥር ይጓዛሉ።

18በምዕራብ በኩል፤

የኤፍሬም ምድብ ሰራዊት በዐርማቸው ሥር ይሆናል፤ የኤፍሬም ሕዝብ አለቃ የዓሚሁድ ልጅ ኤሊሳማ ሲሆን፣ 19የሰራዊቱም ብዛት አርባ ሺሕ አምስት መቶ ነው።

20ከእነዚህም የምናሴ ነገድ ይቀጥላል፣ የምናሴ ሕዝብ አለቃ የፍዳሱር ልጅ ገማልኤል ሲሆን፣ 21የሰራዊቱም ብዛት ሠላሳ ሁለት ሺሕ ሁለት መቶ ነው።

22ከዚያም የብንያም ነገድ ይቀጥላል፣ የብንያም ሕዝብ አለቃ የጋዴዮን ልጅ አቢዳን ሲሆን፣ 23የሰራዊቱም ብዛት ሠላሳ አምስት ሺሕ አራት መቶ ነው።

24በየሰራዊታቸው ሆነው ከኤፍሬም ምድብ የተመዘገቡት ወንዶች በሙሉ አንድ መቶ ስምንት ሺሕ አንድ መቶ ናቸው፤ እነዚህ ሦስተኛ ሆነው ይመጣሉ።

25በሰሜን በኩል፤

የዳን ምድብ ሰራዊት በዐርማው ሥር ይሆናል፤ የዳን ሕዝብ አለቃ የአሚሳዳይ ልጅ አኪዔዘር ሲሆን፣ 26የሰራዊቱም ብዛት ስድሳ ሁለት ሺሕ ሰባት መቶ ነው።

27የአሴር ነገድ ከእነዚህ ቀጥሎ ይሰፍራል፤ የአሴር ሕዝብ አለቃ የኤክራን ልጅ ፋግኤል ሲሆን፣ 28የሰራዊቱም ብዛት አርባ አንድ ሺሕ አምስት መቶ ነው።

29ከዚያም የንፍታሌም ነገድ ይቀጥላል፤ የንፍታሌም ሕዝብ አለቃ የዔናን ልጅ አኪሬ ሲሆን፣ 30የሰራዊቱም ብዛት አምሳ ሦስት ሺሕ አራት መቶ ነው።

31በየሰራዊታቸው ሆነው ከዳን ምድብ የተመዘገቡት ወንዶች ሁሉ አንድ መቶ አምሳ ሰባት ሺሕ ስድስት መቶ ናቸው፤ እነርሱም በዐርማቸው ሥር በመጨረሻ ይመጣሉ።

32በየቤተ ሰባቸው፣ በየምድባቸውና በየሰራዊታቸው የተመዘገቡት እስራኤላውያን ስድስት መቶ ሦስት ሺሕ አምስት መቶ አምሳ ናቸው፤ 33ያም ሆኖ ግን እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን ባዘዘው መሠረት ሌዋውያኑ ከሌሎቹ እስራኤላውያን ጋር አልተቈጠሩም።

34ስለዚህ እስራኤላውያን እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን ያዘዘውን ሁሉ አደረጉ፤ በየዐርማውም ሥር የሰፈሩትና፣ እያንዳንዳቸው በየጐሣቸውና በየቤተ ሰባቸው የተጓዙት በዚህ ሁኔታ ነበር።

Священное Писание (Восточный перевод), версия с «Аллахом»

Числа 2:1-34

Расположение родов в станах

1Вечный сказал Мусе и Харуну:

2– Пусть исраильтяне разбивают стан вокруг шатра встречи, поодаль от него, каждый под своим знаменем, под знаками своей семьи.

3Пусть стан Иуды будет под своим знаменем на востоке, к восходу. Вождь рода Иуды – Нахшон, сын Аминадава. 4В его войске 74 600 мужчин.

5Род Иссахара пусть ставит стан рядом с ними. Вождь рода Иссахара – Нетанил, сын Цуара. 6В его войске 54 400 мужчин.

7Рядом будет род Завулона. Вождь рода Завулона – Элиав, сын Хелона. 8В его войске 57 400 мужчин.

9Всего мужчин в стане Иуды по их войскам 186 400. Они будут отправляться в путь первыми.

10Пусть на юге будет стан Рувима под своим знаменем. Вождь рода Рувима – Элицур, сын Шедеура. 11В его войске 46 500 мужчин.

12Род Шимона пусть ставит стан рядом с ними. Вождь рода Шимона – Шелумиил, сын Цуришаддая. 13В его войске 59 300 мужчин.

14Рядом – род Гада. Вождь рода Гада – Элиасаф, сын Деуила. 15В его войске 45 650 мужчин.

16Всего мужчин в стане Рувима по их войскам 151 450. Они будут отправляться в путь вторыми.

17Затем, пусть в середине станов отправляется в путь шатёр встречи и стан левитов. Они будут отправляться в путь в том порядке, в каком ставят стан, каждый на своём месте, под своим знаменем.

18Пусть на западе будет стан Ефраима под своим знаменем. Вождь рода Ефраима – Элишама, сын Аммихуда. 19В его войске 40 500 мужчин.

20После них будет род Манассы. Вождь рода Манассы – Гамалиил, сын Педацура. 21В его войске 32 200 мужчин.

22Потом будет род Вениамина. Вождь рода Вениамина – Авидан, сын Гидеони. 23В его войске 35 400 мужчин.

24Всего мужчин в стане Ефраима по их войскам 108 100. Они будут отправляться в путь третьими.

25Пусть на севере будет стан Дана под своим знаменем. Вождь рода Дана – Ахиезер, сын Аммишаддая. 26В его войске 62 700 мужчин.

27Род Ашира будет ставить стан возле них. Вождь рода Ашира – Пагиил, сын Охрана. 28В его войске 41 500 мужчин.

29Потом будет род Неффалима. Вождь рода Неффалим – это Ахира, сын Енана. 30В его войске 53 400 мужчин.

31Всего мужчин в стане Дана 157 600. Они будут отправляться в путь последними под своими знамёнами.

32Это исраильтяне, исчисленные по их семьям. Всего в станах – по ополчениям – 603 550 человек. 33Лишь левиты не были исчислены с остальными исраильтянами – так повелел Мусе Вечный.

34Исраильтяне сделали всё, что повелел Мусе Вечный. Они вставали станом под своими знамёнами и также отправлялись в путь – каждый со своим кланом и семьёй.