ዘኍል 1 – NASV & BPH

New Amharic Standard Version

ዘኍል 1:1-54

የሕዝብ ቈጠራ

1እስራኤላውያን ከግብፅ በወጡ በሁለተኛው ዓመት፣ በሁለተኛው ወር፣ በመጀመሪያው ቀን በሲና ምድረ በዳ ሳሉ እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን በመገናኛው ድንኳን ውስጥ ተናገረው፤ እንዲህም አለው፤ 2“የወንዶቹን ስም አንድ በአንድ በመዘርዘር መላውን የእስራኤል ማኅበረ ሰብ በየጐሣቸውና በየቤተ ሰባቸው ቍጠሯቸው። 3በመላው እስራኤል ያሉትን ዕድሜያቸው ሃያና ከዚያም በላይ ሆኖ ለውጊያ ብቁ የሆኑትን ወንዶች ሁሉ አንተና አሮን በየምድባቸው ቍጠሯቸው። 4ከየነገዱ የአባቶች ቤት ተጠሪ የሆነ አንድ ሰው ከእናንተ ጋር ይሁን።

5“የሚረዷችሁም ሰዎች ስም የሚከተለው ነው፤

“ከሮቤል የሰዲዮር ልጅ ኤሊሱር፤

6ከስምዖን የሱሪሰዳይ ልጅ ሰለሚኤል፤

7ከይሁዳ የአሚናዳብ ልጅ ነአሶን፤

8ከይሳኮር የሶገር ልጅ ናትናኤል፤

9ከዛብሎን የኬሎን ልጅ ኤልያብ፤

10ከዮሴፍ ልጆች ከኤፍሬም የዓሚሁድ ልጅ ኤሊሳማ፤

ከምናሴ የፍዳሱር ልጅ ገማልኤል፤

11ከብንያም የጋዴዮን ልጅ አቢዳን፤

12ከዳን የአሚሳዳይ ልጅ አኪዔዘር፤

13ከአሴር የኤክራን ልጅ ፋግኤል፤

14ከጋድ የራጉኤል ልጅ ኤሊሳፍ፤

15ከንፍታሌም የዔናን ልጅ አኪሬ።”

16እነዚህ ከማኅበረ ሰቡ የተመረጡ የየነገዱ አለቆች ሲሆኑ እነርሱም የእስራኤል ጐሣዎች መሪዎች ነበሩ።

17ሙሴና አሮን ስማቸው የተጠቀሰውን እነዚህን ሰዎች ወሰዱ፤ 18ከዚያም በሁለተኛው ወር በመጀመሪያው ቀን ማኅበረ ሰቡን በሙሉ በአንድነት ሰበሰቧቸው። የተሰበሰቡትም በየጐሣቸውና በየቤተ ሰባቸው የትውልድ ሐረጋቸውን ተናገሩ፤ 19እግዚአብሔር ሙሴን ባዘዘው መሠረት ዕድሜያቸው ሃያ ዓመትና ከዚያም በላይ የሆነ ወንዶች ስማቸው አንድ በአንድ ተመዘገበ። እንዲህ አድርጎም በሲና ምድረ በዳ ቈጠራቸው።

20ከእስራኤል የበኵር ልጅ ከሮቤል ዝርያ፦

ዕድሜያቸው ሃያ ዓመትና ከዚያ በላይ ሆኖ በሰራዊቱ ውስጥ ለማገልገል ብቁ የሆኑት ወንዶች ሁሉ በየጐሣቸውና፣ በየቤተ ሰባቸው መዝገብ መሠረት ስማቸው አንድ በአንድ ተጻፈ። 21ከሮቤል ነገድ የተቈጠሩት አርባ ስድስት ሺሕ አምስት መቶ ነበሩ።

22ከስምዖን ዝርያ፦

ዕድሜያቸው ሃያ ዓመትና ከዚያም በላይ ሆኖ ለመዋጋት ብቁ የሆኑት ወንዶች ሁሉ በየጐሣቸውና በየቤተ ሰባቸው መዝገብ መሠረት ስማቸው አንድ በአንድ ተጻፈ። 23ከስምዖን ነገድ የተቈጠሩት አምሳ ዘጠኝ ሺሕ ሦስት መቶ ነበሩ።

24ከጋድ ዝርያ፦

ዕድሜያቸው ሃያ ዓመትና ከዚያም በላይ ሆኖ ለመዋጋት ብቁ የሆኑት ወንዶች ሁሉ በየጐሣቸውና፣ በየቤተ ሰባቸው መዝገብ መሠረት ስማቸው አንድ በአንድ ተጻፈ። 25ከጋድ ነገድ የተቈጠሩትም አርባ አምስት ሺሕ ስድስት መቶ አምሳ ነበሩ።

26ከይሁዳ ዝርያ፦

ዕድሜያቸው ሃያ ዓመትና ከዚያም በላይ ሆኖ ለመዋጋት ብቁ የሆኑት ወንዶች ሁሉ በየጐሣቸውና፣ በየቤተ ሰባቸው መዝገብ መሠረት ስማቸው አንድ በአንድ ተጻፈ። 27ከይሁዳ ነገድ የተቈጠሩትም ሰባ አራት ሺሕ ስድስት መቶ ነበሩ።

28ከይሳኮር ዝርያ፦

ዕድሜያቸው ሃያ ዓመትና ከዚያም በላይ ሆኖ ለመዋጋት ብቁ የሆኑት ወንዶች ሁሉ በየጐሣቸውና፣ በየቤተ ሰባቸው መዝገብ መሠረት ስማቸው አንድ በአንድ ተጻፈ። 29ከይሳኮር ነገድ የተቈጠሩትም አምሳ አራት ሺሕ አራት መቶ ነበሩ።

30ከዛብሎን ዝርያ፦

ዕድሜያቸው ሃያ ዓመትና ከዚያም በላይ ሆኖ ለመዋጋት ብቁ የሆኑት ወንዶች ሁሉ በየጐሣቸውና፣ በየቤተ ሰባቸው መዝገብ መሠረት ስማቸው አንድ በአንድ ተጻፈ። 31ከዛብሎን ነገድ የተቈጠሩትም አምሳ ሰባት ሺሕ አራት መቶ ነበሩ።

32ከዮሴፍ ልጆች፦

ከኤፍሬም ዝርያ ዕድሜያቸው ሃያ ዓመትና ከዚያም በላይ ሆኖ ለመዋጋት ብቁ የሆኑት ወንዶች ሁሉ በየጐሣቸውና በየቤተ ሰባቸው መዝገብ መሠረት ስማቸው አንድ በአንድ ተጻፈ። 33ከኤፍሬም ነገድ የተቈጠሩትም አርባ ሺሕ አምስት መቶ ነበሩ።

34ከምናሴ ዝርያዎች፦

ዕድሜያቸው ሃያ ዓመትና ከዚያም በላይ ሆኖ ለመዋጋት ብቁ የሆኑት ወንዶች ሁሉ በየጐሣቸውና በየቤተ ሰባቸው መዝገብ መሠረት ስማቸው አንድ በአንድ ተጻፈ። 35ከምናሴ ነገድ የተቈጠሩትም ሠላሳ ሁለት ሺሕ ሁለት መቶ ነበሩ።

36ከብንያም ዝርያ፦

ዕድሜያቸው ሃያ ዓመትና ከዚያም በላይ ሆኖ ለመዋጋት ብቁ የሆኑት ወንዶች ሁሉ በየጐሣቸውና፣ በየቤተ ሰባቸው መዝገብ መሠረት ስማቸው አንድ በአንድ ተጻፈ፤ 37ከብንያም ነገድ የተቈጠሩትም ሠላሳ አምስት ሺሕ አራት መቶ ነበሩ።

38ከዳን ዝርያ፦

ዕድሜያቸው ሃያ ዓመትና ከዚያም በላይ ሆኖ ለመዋጋት ብቁ የሆኑት ወንዶች ሁሉ በየጐሣቸውና፣ በየቤተ ሰባቸው መዝገብ መሠረት ስማቸው አንድ በአንድ ተጻፈ። 39ከዳን ነገድ የተቈጠሩትም ስድሳ ሁለት ሺሕ ሰባት መቶ ነበሩ።

40ከአሴር ዝርያ፦

ዕድሜያቸው ሃያ ዓመትና ከዚያም በላይ ሆኖ ለመዋጋት ብቁ የሆኑት ወንዶች ሁሉ በየጐሣቸውና፣ በየቤተ ሰባቸው መዝገብ መሠረት ስማቸው አንድ በአንድ ተጻፈ። 41ከአሴር ነገድ የተቈጠሩት አርባ አንድ ሺሕ አምስት መቶ ነበሩ።

42ከንፍታሌም ዝርያ፦

ዕድሜያቸው ሃያ ዓመትና ከዚያም በላይ ሆኖ ለመዋጋት ብቁ የሆኑት ወንዶች ሁሉ በየጐሣቸውና፣ በየቤተ ሰባቸው መዝገብ መሠረት ስማቸው አንድ በአንድ ተጻፈ። 43ከንፍታሌም ነገድ የተቈጠሩትም አምሳ ሦስት ሺሕ አራት መቶ ነበሩ።

44በሙሴና በአሮን፣ እያንዳንዳቸውም ቤተ ሰባቸውን በወከሉት በዐሥራ ሁለቱ የእስራኤል አለቆች የተቈጠሩት ወንዶች እነዚህ ናቸው። 45ስለዚህ እስራኤላውያን ሁሉ ዕድሜያቸው ሃያ ዓመትና ከዚያም በላይ ሆኖ በእስራኤል ሰራዊት ውስጥ ለመዋጋት ብቁ የሆኑት በየቤተ ሰባቸው ተቈጠሩ፤ 46ጠቅላላ ቍጥራቸውም ስድስት መቶ ሦስት ሺሕ አምስት መቶ አምሳ ነበር።

47የሌዊ ነገድ ቤተ ሰቦች ግን ከሌሎች ጋር አብረው አልተቈጠሩም፤ 48እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን እንዲህ ብሎት ነበርና፤ 49“የሌዊን ነገድ አትቍጠር፤ በእስራኤላውያንም ቈጠራ ውስጥ አታስገባው፤ 50በዚህ ፈንታ ሌዋውያንን በምስክሩ ማደሪያ፣ በውስጡ ባሉት በመገልገያ ዕቃዎች ሁሉ እንዲሁም ከዚሁ ጋር በተያያዙ በማናቸውም ነገሮች ላይ ኀላፊዎች ይሁኑ፤ ማደሪያውንና በውስጡ ያሉትን የመገልገያ ዕቃዎች ይሸከሙ፤ በውስጡ ያገልግሉ፤ ድንኳናቸውንም በዙሪያው ይትከሉ። 51ማደሪያው በሚነሣበት ጊዜ ሌዋውያን ይንቀሉት፤ ማደሪያው በሚተከልበትም ጊዜ ሌዋውያን ያቁሙት፤ ሌላ ሰው ቢቀርብ ግን ይገደል። 52እስራኤላውያን በየምድባቸው ድንኳናቸውን ይትከሉ፤ እያንዳንዱም ሰው በየሰፈሩና በየዐርማው ሥር ይስፈር። 53ሌዋውያን ግን በእስራኤላውያን ማኅበረ ሰብ ላይ ቍጣ እንዳይወርድ ድንኳኖቻቸውን በምስክሩ ማደሪያ ዙሪያ ይትከሉ፤ የምስክሩ ማደሪያ ድንኳን ኀላፊዎች ሌዋውያን ናቸው።”

54እስራኤላውያንም እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን ባዘዘው መሠረት ይህን ሁሉ አደረጉ።

Bibelen på hverdagsdansk

4. Mosebog 1:1-54

Israels første folketælling

1På den første dag i den anden måned1,1 Den anden måned svarer til april-maj. året efter, at israelitterne havde forladt Egypten, talte Herren til Moses i åbenbaringsteltet, mens folket opholdt sig i Sinais ørken.

Herren sagde: 2-4„Lav en liste over alle våbenføre mænd over 20 år med deres stamme- og slægtsnavne. Du og Aron skal være ansvarlige for optællingen, som skal uddelegeres til en leder fra hver enkelt stamme. 5Følgende ledere skal hjælpe jer: fra Rubens stamme: Elitzur, Shedeurs søn; 6fra Simeons stamme: Shelumiel, Zurishaddajs søn; 7fra Judas stamme: Nahshon, Amminadabs søn; 8fra Issakars stamme: Netanel, Suars søn; 9fra Zebulons stamme: Eliab, Helons søn; 10fra Efraims, Josefs søns, stamme: Elishama, Ammihuds søn; fra Manasses, Josefs søns, stamme: Gamliel, Pedasurs søn; 11fra Benjamins stamme: Abidan, Gidonis søn; 12fra Dans stamme: Ahiezer, Ammishaddajs søn; 13fra Ashers stamme: Pagiel, Okrans søn; 14fra Gads stamme: Eljasaf, Deuels søn; 15fra Naftalis stamme: Ahira, Enans søn.” 16Disse mænd var ledere blandt folket, overhoveder for hver deres slægt.

17-46Samme dag sammenkaldte Moses, Aron og de ovennævnte ledere samtlige våbenføre mænd i Israel over 20 år. Hver person fik besked på at oplyse sit stamme- og slægtsnavn, sådan som Herren havde befalet Moses. Her følger den samlede opgørelse: Jakobs førstefødte søns, Rubens, stamme: 46.500; Simeons stamme: 59.300; Gads stamme: 45.650; Judas stamme: 74.600; Issakars stamme: 54.400; Zebulons stamme: 57.400; Efraims, Josefs søns, stamme: 40.500; Manasses, Josefs søns, stamme: 32.200; Benjamins stamme: 35.400; Dans stamme: 62.700; Ashers stamme: 41.500; Naftalis stamme: 53.400. Det samlede antal våbenføre mænd udgjorde 603.550 personer.

47-49Dette tal indbefatter dog ikke levitterne, for Herren havde sagt til Moses: „Du må ikke bruge levitterne som soldater, og du skal ikke tage dem med på listen. 50Jeg har nemlig givet dem ansvar for at tage sig af min bolig, det hellige telt, som indeholder pagtens ark. Derfor skal de altid have deres lejr i nærheden af boligen. 51Det er levitternes opgave at pakke teltet sammen og rejse det igen, og hvis nogen andre blander sig i den opgave eller blot rører ved teltet, skal de henrettes. 52Resten af Israels stammer skal tildeles hver deres lejrplads med hver deres banner, 53men levitterne skal slå lejr rundt om teltet med pagtens ark, så de udgør en mur mellem folket og Herren, for at ingen af de menige israelitter skal komme til at røre ved teltet og rammes af Herrens vrede.”

54Israels folk fulgte omhyggeligt de befalinger, som Herren havde givet Moses.