ዘሌዋውያን 3 – NASV & CCB

New Amharic Standard Version

ዘሌዋውያን 3:1-17

የኅብረት መሥዋዕት

1“ ‘ማንኛውም ሰው የሚያቀርበው ቍርባን ከላሞች መንጋ የሚቀርብ የኅብረት መሥዋዕት3፥1 በትውፊት የሰላም መሥዋዕት ይባላል፤ እንዲሁም 3፡6፡9 ይመ። ከሆነ፣ እንከን የሌለበትን ተባዕት ወይም እንስት በእግዚአብሔር (ያህዌ) ፊት ያቅርብ። 2በሚያቀርበው እንስሳ ራስ ላይ እጁን ይጫን፤ በመገናኛው ድንኳን ደጃፍ ላይ ይረደው፤ ካህናቱም የአሮን ልጆች ደሙን በመሠዊያው ላይ ዙሪያውን ይርጩት። 3ከኅብረት መሥዋዕቱ ለእግዚአብሔር (ያህዌ) በእሳት የሚቀርብ ቍርባን አድርጎ ያምጣ፤ የሆድ ዕቃውን የሚሸፍነውን ሥብ፣ በሆድ ዕቃው ላይ ያለውን ሥብ ሁሉ፣ 4ሁለቱን ኵላሊቶች፣ በኵላሊቶቹ ላይና በጐድኑ አጠገብ ያለውን ሥብ እንዲሁም የጕበቱን መሸፈኛ፣ ከኵላሊቶቹ ጋር አንድ ላይ አውጥቶ ያቅርብ። 5የአሮንም ልጆች በመሠዊያው በሚነድደው ዕንጨት ላይ ባለው በሚቃጠለው መሥዋዕት ላይ አድርገው ያቃጥሉት፤ ይህም በእሳት የሚቀርብ፣ ሽታውም እግዚአብሔርን (ያህዌ) ደስ የሚያሰኝ መሥዋዕት ይሆናል።

6“ ‘ከበግ ወይም ከፍየሉ መንጋ ለእግዚአብሔር (ያህዌ) የኅብረት መሥዋዕት የሚያቀርብ ከሆነ፣ እንከን የሌለበትን ተባዕት ወይም እንስት ያቅርብ። 7መሥዋዕቱ የበግ ጠቦት ከሆነም፣ በእግዚአብሔር (ያህዌ) ፊት ያምጣው፤ 8በጠቦቱ ራስ ላይ እጁን ይጫን፤ በመገናኛው ድንኳን ፊት ለፊት ይረደው፤ የአሮንም ልጆች ደሙን በመሠዊያው ላይ ዙሪያውን ይርጩት። 9ከኅብረት መሥዋዕቱ ለእግዚአብሔር (ያህዌ) በእሳት የሚቀርብ ቍርባን አድርጎ ያምጣ፤ ሥቡን፣ እስከ ጀርባ ዐጥንቱ ድረስ የተቈረጠ ላቱን በሙሉ፣ የሆድ ዕቃውን የሸፈነውን ሥብ፣ ከሆድ ዕቃው ጋር የተያያዘውን ሥብ ሁሉ፣ 10ሁለቱን ኵላሊቶች፣ ኵላሊቶቹ ላይና በጐድኑ አጠገብ ያለውን ሥብ እንዲሁም የጕበቱን መሸፈኛ ከኵላሊቶቹ ጋር አብሮ አውጥቶ ያቅርብ። 11ካህኑም ይህን ሁሉ ለእግዚአብሔር (ያህዌ) በእሳት የሚቀርብ የመብል ቍርባን አድርጎ በመሠዊያው ላይ ያቃጥል።

12“ ‘መሥዋዕቱ ፍየል ከሆነ፣ በእግዚአብሔር (ያህዌ) ፊት ያቅርብ፤ 13በራሱም ላይ እጁን ይጫንበት፤ በመገናኛው ድንኳን ፊት ለፊት ይረደው፤ የአሮንም ልጆች ደሙን በመሠዊያው ላይ ዙሪያውን ይርጩት። 14ከሚያቀርበውም መሥዋዕት ላይ ለእግዚአብሔር (ያህዌ) በእሳት የሚቀርብ ቍርባን አድርጎ ያቅርብ፤ የሆድ ዕቃውን የሚሸፍነውን ሥብ፣ ከሆድ ዕቃው ጋር የተያያዘውን ሥብ ሁሉ፣ 15ሁለቱን ኵላሊቶች፣ በኵላሊቶቹ ላይና በጐድኑ አጠገብ ያለውን ሥብ፣ እንዲሁም የጕበቱን መሸፈኛ ከኵላሊቶቹ ጋር አብሮ አውጥቶ ያቅርብ። 16ካህኑም ይህን ሁሉ በእሳት የሚቀርብና ሽታውም ደስ የሚያሰኝ የመብል ቍርባን አድርጎ በመሠዊያው ላይ ያቃጥል፤ ሥብ ሁሉ የእግዚአብሔር (ያህዌ) ነው።

17“ ‘በምትኖሩበት ስፍራ ሁሉ፣ ሥብ ወይም ደም ከቶ አትብሉ፤ ይህ ለመጪው ትውልድ ሁሉ የተሰጠ የዘላለም ሥርዐት ነው።’ ”

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

利未记 3:1-17

献平安祭的条例

1“如果有人用牛献作平安祭,必须在耶和华面前献上毫无残疾的公牛或母牛。 2献祭者要把手放在牛头上,在会幕门口宰牛。祭司——亚伦的子孙要把牛血洒在祭坛四周。 3献祭者要从平安祭中献上火祭给耶和华。他要取出遮盖内脏的脂肪和内脏上的脂肪、 4两个肾脏和肾脏上靠近腰部的脂肪以及肝叶。 5祭司要把这一切放在祭坛燃烧的木柴上和燔祭一起焚烧,作为蒙耶和华悦纳的馨香火祭。

6“如果用羊作祭物向耶和华献平安祭,必须献毫无残疾的公羊或母羊。 7如果献的是绵羊羔,献祭者要把羊羔带到耶和华面前, 8将手放在羊头上,在会幕前宰杀。亚伦的子孙要把羊羔的血洒在祭坛四周。 9献祭者要从平安祭中取出脂肪作为火祭献给耶和华。他要从靠近脊椎骨处取下整条肥尾巴、遮盖内脏的脂肪、 10两个肾脏和肾脏上靠近腰部的脂肪以及肝叶。 11祭司要把这一切放在祭坛上焚烧,作为献给耶和华的火祭。

12“如果献的是山羊,献祭者要把山羊带到耶和华面前, 13将手放在羊头上,在会幕门口宰杀。祭司要把羊血洒在祭坛四周。 14-15献祭者要取出遮盖内脏的脂肪和内脏上的脂肪、两个肾脏和肾脏上面靠近腰部的脂肪以及肝叶,作为火祭献给耶和华。 16祭司要把这一切放在祭坛上焚烧,作为蒙耶和华悦纳的馨香火祭。所有的脂肪都属于耶和华。 17你们无论住在哪里,都不可吃脂肪和血,这是你们世代永远要遵守的条例。”