ኤፌሶን 5 – NASV & HHH

New Amharic Standard Version

ኤፌሶን 5:1-33

1እንግዲህ እንደ ተወደዱ ልጆች እግዚአብሔርን ምሰሉ፤ 2ክርስቶስ እንደ ወደደን ራሱንም ስለ እኛ መልካም መዐዛ ያለው መባና መሥዋዕት አድርጎ ለእግዚአብሔር እንደ ሰጠ እናንተም በፍቅር ተመላለሱ።

3ማንኛውም የዝሙት ወይም የርኩሰት ወይም የሥሥት ነገር ከቶ በመካከላችሁ አይነሣ፤ ይህ ቅዱስ ለሆነው ለእግዚአብሔር ሕዝብ አይገባምና። 4የሚያሳፍርና ተራ የሆነ ንግግር፣ ዋዛ ፈዛዛም ለእናንተ ስለማይገባ በመካከላችሁ አይኑር፤ ይልቁንስ የምታመሰግኑ ሁኑ። 5ደግሞም ይህን ዕወቁ፤ ማንም አመንዝራ ወይም ርኩስ ወይም ስግብግብ፣ ይኸውም ጣዖት አምላኪ በክርስቶስና በእግዚአብሔር መንግሥት5፥5 ወይም የክርስቶስና የእግዚአብሔር መንግሥት በሆነው ርስት የለውም። 6ማንም በከንቱ ንግግር አያታልላችሁ፤ ምክንያቱም የእግዚአብሔር ቍጣ በማይታዘዙ ልጆች ላይ የሚመጣው በእንደዚህ ዐይነት ነገር ነው። 7ስለዚህ እንዲህ ካሉ ጋር አትተባበሩ።

8ቀድሞ ጨለማ ነበራችሁ፤ አሁን ግን በጌታ ብርሃን ናችሁ። እንደ ብርሃን ልጆች ኑሩ፤ 9የብርሃኑ ፍሬ በበጎነት፣ በጽድቅና በእውነት ሁሉ ዘንድ ነውና። 10እንዲሁም ጌታን ደስ የሚያሰኘውን ፈልጉ። 11ፍሬ ከሌለው ከጨለማ ሥራ ጋር ምንም ዐይነት ግንኙነት አይኑራችሁ፤ ይልቁን ግለጡት፤ 12በድብቅ የሚሠሩትን ነገር መናገር ራሱ አሳፋሪ ነውና። 13ብርሃን የበራበት ነገር ሁሉ ግልጽ ሆኖ ይታያል፤ 14ምክንያቱም ሁሉን ነገር እንዲታይ የሚያደርገው ብርሃን ነውና፤ ስለዚህም፣

“አንተ የተኛህ ንቃ፤

ከሙታን ተነሣ፤

ክርስቶስም ያበራልሃል” ተብሏል።

15እንግዲህ ጥበብ እንደሌላቸው ሳይሆን እንደ ጥበበኞች እንዴት እንደምትኖሩ ተጠንቀቁ። 16ቀኖቹ ክፉ ናቸውና ዘመኑን በሚገባ ዋጁ። 17ስለዚህ ሞኞች አትሁኑ፤ የጌታ ፈቃድ ምን እንደ ሆነ አስተውሉ እንጂ። 18በመንፈስ ተሞሉ እንጂ በወይን ጠጅ አትስከሩ፤ ይህ ብክነት ነውና። 19በመዝሙርና በውዳሴ፣ በመንፈሳዊም ዝማሬ እርስ በርሳችሁ ተነጋገሩ፤ በልባችሁ ለጌታ ተቀኙ፤ አዚሙም። 20በዚህም እግዚአብሔር አብን በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ስለ ሁሉ ነገር ሁልጊዜ አመስግኑ።

21ለክርስቶስ ካላችሁ አክብሮታዊ ፍርሀት የተነሣ አንዳችሁ ለአንዳችሁ ተገዙ።

ባልና ሚስት

5፥22–6፥9 ተጓ ምብ – ቈላ 3፥18–4፥1

22ሚስቶች ሆይ፤ ለጌታ እንደምትገዙ ለባሎቻችሁም ተገዙ 23ክርስቶስ፣ አካሉ ለሆነችውና አዳኟ ለሆናት ቤተ ክርስቲያን ራስ እንደ ሆነ ሁሉ፣ ባልም የሚስቱ ራስ ነውና። 24እንግዲህ ቤተ ክርስቲያን ለክርስቶስ እንደምትገዛ፣ ሚስቶችም ለባሎቻቸው በማንኛውም ነገር እንደዚሁ መገዛት ይገባቸዋል።

25ባሎች ሆይ፤ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያንን እንደ ወደዳትና ራሱንም ስለ እርሷ አሳልፎ እንደ ሰጠ፣ እናንተም ሚስቶቻችሁን ውደዱ፤ 26በቃሉ አማካይነት በውሃ ዐጥቦ በማንጻት እንድትቀደስ፣ 27እንዲሁም ጕድፍ ወይም የፊት መጨማደድ ወይም አንዳች እንከን ሳይገኝባት ቅድስትና ነውር አልባ የሆነች ክብርት ቤተ ክርስቲያን አድርጎ ለራሱ ሊያቀርባት ነው። 28ባሎችም እንደዚሁ ሚስቶቻቸውን እንደ ገዛ ሥጋቸው መውደድ ይገባቸዋል። ሚስቱን የሚወድድ ራሱን ይወድዳል። 29የገዛ ሥጋውን የሚጠላ ማንም የለም፤ ይመግበዋል፤ ይንከባከበዋል፤ ክርስቶስም ለቤተ ክርስቲያን ያደረገው ልክ እንደዚሁ ነው፤ 30እኛ የክርስቶስ አካል ብልቶች ነንና። 31“ስለዚህም ሰው አባቱንና እናቱን ይተዋል፤ ከሚስቱም ጋር አንድ ይሆናል፤ ሁለቱም አንድ ሥጋ ይሆናሉ”። 32ይህ ጥልቅ ምስጢር ነው፤ እኔም ይህን ስለ ክርስቶስና ስለ ቤተ ክርስቲያን እናገራለሁ። 33ሆኖም ከእናንተ እያንዳንዱ ሚስቱን እንደ ራሱ አድርጎ ይውደድ፤ ሚስትም ባሏን ታክብር።

Habrit Hakhadasha/Haderekh

אגרת פולוס השליח אל האפסיים 5:1-33

1עליכם ללכת בעקבות אלוהים, כי אתם ילדיו והוא אוהב אתכם. 2אהבו איש את רעהו, כשם שהמשיח אהב אותנו וביטא אהבה זאת בהקריבו את עצמו למעננו, כדי לסלוח על חטאינו, וקורבנו היה רצוי לאלוהים.

3בכל הנוגע למעשי זנות למיניהם, מעשי טומאה ואהבת בצע – אפילו אל תזכירו אותם! נושאים אלה אינם הולמים שיחת מאמינים משיחיים. 4הימנעו גם מניבול־פה, דברי שטות וליצנות – אין הם הולמים אתכם! לעומת זאת, הזכירו איש לרעהו את טוב־לבו של אלוהים והיו אסירי תודה.

5דעו לכם כי הזונים ואוהבי הבצע, שאינם אלא עובדי אלילים, לעולם לא יירשו את מלכות האלוהים והמשיח, כי הם אוהבים את דברי העולם הזה יותר מאשר את אלוהים. 6אל תניחו לאיש להתעות אתכם בנושא זה, כי בגלל חטאים כאלה ישפוך אלוהים את זעמו על מי שמורד בו. 7אף אל תתחברו עם אנשים כאלה! 8פעם חייתם בחשכה ובחטא, אך כעת אתם חיים באור אדוננו, והתנהגותכם צריכה להוכיח זאת. 9שכן פרי הרוח והאור הוא כל דבר טוב, צודק ואמיתי.

10השתדלו ללמוד מה רצוי בעיני אדוננו. 11אל תשתתפו במעשים רעים למיניהם שאינם מביאים כל תועלת, אלא הוקיעו אותם! 12בושה וחרפה היא מה שעושים הרשעים בסתר. 13כשאתה חושף אותם לאור נראים חטאיהם בבירור, ובמקום שבו ניתן לראות בבירור יש אור. 14על כן נֶאֱמַר: ”התעורר, אתה הישן, קום מן המתים והמשיח יאיר עליך!“

15‏-16לפיכך התנהגו בזהירות, שכן אלה הם ימים קשים. אל תהיו שוטים, אלא חכמים, ונצלו היטב כל הזדמנות לעשות מעשים טובים. 17אל תתנהגו בחוסר מחשבה, אלא השתדלו להבין מה רוצה האדון שתעשו, ועשו זאת! 18אל תרבו בשתיית יין, כי שתייה מרובה גורמת למעשים רעים. לעומת זאת, מלאו עצמכם ברוח הקודש והניחו לו לשלוט בכם.

19בפגשכם זה את זה שוחחו על אודות האדון, צטטו מזמורי תהלים, שירו שירים רוחניים וזמרו לאלוהים בלבבכם. 20הודו תמיד על כל דבר לאלוהים אבינו בשם ישוע המשיח אדוננו.

21כבדו את המשיח על־ידי כניעתכם איש לרעהו. 22נשים, עליכן להיכנע ולציית לבעליכן, כשם שאתן נכנעות ומצייתות למשיח. 23כי הבעל הוא ראש האישה, כשם שהמשיח הוא ראש הקהילה, שהיא גופו ואשר למענה הקריב את חייו, כדי להושיעה ולדאוג לה. 24אם כן, עליכן, הנשים, להיכנע ברצון לבעליכן בכל דבר, כשם שהקהילה נכנעת למשיח.

25אתם, הבעלים, אהבו את נשותיכם באותה מידה שאהב המשיח את הקהילה, כשהקריב את חייו למענה 26כדי לזכותה ולקדשה, לרחצה בדבר אלוהים, 27למען יוכל להעמידה לפניו כקהילה יפה וקדושה, חסרת־דופי, כתם או פגם. 28על הבעלים לאהוב את נשותיהם כמו את עצמם, כי הבעל ואשתו אחד הם. 29‏-30הרי איש אינו שונא את גופו, אלא מזין אותו ודואג לו באהבה, כשם שהמשיח דואג לקהילתו, ואנו הרי איברי גופו, בשר מבשרו. 31כפי שאומר הכתוב:5‏.31 ה 31 בראשית ב 24 ”על כן יעזוב איש את אביו ואת אמו, ודבק באשתו והיו לבשר אחד.“ 32קשר הנשואים הוא דבר מופלא, אך יש בו הקבלה לקשר שבין המשיח והקהילה.

33אם כן, אני חוזר ואומר: הבעל חייב לאהוב את אשתו כמו את עצמו, והאישה חייבת לכבד את בעלה ולציית לו.