ኤርምያስ 6 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ኤርምያስ 6:1-30

የኢየሩሳሌም መከበብ

1“እናንት የብንያም ልጆች፤ ክፉ ነገር፣

ታላቅም ጥፋት ከሰሜን ድንገት ይመጣልና፣

ከኢየሩሳሌም ሸሽታችሁ አምልጡ፤

በቴቁሔ መለከትን ንፉ፤

በቤትሐካሪም ላይ ምልክት ከፍ

አድርጋችሁ አሳዩ።

2ውብና ሽሙንሙን የሆነችዋን፣

የጽዮንን ሴት ልጅ አጠፋታለሁ።

3እረኞች መንጎቻቸውን ይዘው ይመጡባታል፤

ድንኳናቸውን በዙሪያዋ ይተክላሉ፤

እያንዳንዳቸውም በየአቅጣጫቸው መንጋቸውን ያሰማራሉ።

4“በእርሷ ላይ ጦርነት ዐውጁ፤

ተነሡ በቀትር አደጋ እንጣልባት፤

ወይ ጉድ! ቀኑ እኮ መሸብን!

ጥላው ረዘመ።

5እንግዲህ ተነሡ በሌሊት እናጥቃት፤

ምሽጎቿንም እንደምስስ!”

6የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ዛፎቹን ቍረጡ፤

በኢየሩሳሌም ዙሪያ የዐፈር ድልድል ሥሩ።

ይህች ከተማ ቅጣት ይገባታል፤

ግፍን ተሞልታለችና።

7የውሃ ጕድጓድ ውሃ እንደሚያመነጭ፣

እርሷም እንዲሁ ክፋቷን ታፈልቃለች።

ዐመፅና ጥፋት በውስጧ ይስተጋባል፤

ሕመሟና ቍስሏ ዘወትር ይታየኛል።

8ኢየሩሳሌም ሆይ፤ ተጠንቀቂ፤

አለዚያ ከአንቺ ዘወር እላለሁ፤

ማንም ሊኖርባት እስከማይችል ድረስ፣

ምድርሽን ባዶ አደርጋለሁ።”

9የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“የወይን ፍሬ ተሟጦ እንደሚቃረም፣

ከእስራኤል የተረፉትን እንዲሁ ይቃርሟቸው።

ወይን ለቃሚ እንደሚለቅም፣

እጅህን ወደ ቅርንጫፎቹ ደጋግመህ ዘርጋ።”

10ለማን ልናገር? ማንን ላስጠንቅቅ?

ማንስ ይሰማኛል?

እነሆ፣ ጆሮዎቻቸው አልተገረዙምና፣6፥10 ወይም ጆሮዎቻቸው ተደፍነዋል

መስማት አይችሉም።

በእግዚአብሔር ቃል ይሣለቃሉ፤

ደስም አይሰኙበትም።

11በእነርሱ ላይ በእግዚአብሔር ቍጣ ተሞልቻለሁ፤

በውስጤም ልይዘው አልቻልሁም።

“መንገድ ላይ በሚገኙ ሕፃናት፣

በተሰበሰቡ ወጣቶችም ላይ አፍስሰው፤

ባልም ሚስትም፣

ያረጁና የጃጁም አያመልጡም።

12በምድሪቱ በሚኖሩት ላይ

እጄን በምዘረጋበት ጊዜ፣

ዕርሻቸውና ሚስቶቻቸው ሳይቀሩ፣

ቤቶቻቸው ለሌሎች ይሆናሉ፤”

ይላል እግዚአብሔር

13“ከትንሹ እስከ ትልቁ ሰው፣

ሁሉም ለጥቅም የሚስገበገቡ ናቸው፤

ነቢያቱም ካህናቱም ሳይቀሩ፣

ሁሉም ያጭበረብራሉ።

14የሕዝቤን ቍስል እንደ ቀላል ቈጠሩ፣

እንዲፈወስም ተገቢውን እንክብካቤ አላደረጉለትም፤

ሰላምም ሳይኖር፣

‘ሰላም፣ ሰላም’ ይላሉ።

15ስለ ጸያፉ ተግባራቸው ዐፍረዋል እንዴ?

ኧረ ጨርሶ ዕፍረት የላቸውም!

ዕፍረት ምን እንደ ሆነ እንኳ አያውቁም፤

ስለዚህ ከሚወድቁት ጋር ይወድቃሉ፤

በምቀጣቸውም ጊዜ ይዋረዳሉ፤”

ይላል እግዚአብሔር

16እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“መንታ መንገድ ላይ ቁሙ፣ ተመልከቱም፤

መልካሟን፣ የጥንቷን መንገድ ጠይቁ፤

በእርሷም ላይ ሂዱ።

ለነፍሳችሁ ዕረፍት ታገኛላችሁ፤

እናንተ ግን፣ ‘በእርሷ አንሄድም’ አላችሁ።

17ጠባቂዎችን አቆምሁላችሁ፤

‘የመለከትንም ድምፅ ስሙ’ አልኋችሁ፤

እናንተ ግን፣ ‘አንሰማም’ አላችሁ።

18እንግዲህ ሕዝቦች ሆይ ስሙ፤

እናንተም ምስክሮች ምን

እንደሚገጥማቸው አስተውሉ።

19ምድር ሆይ፤ ስሚ፤

ቃሌን ስላላደመጡ፣

ሕጌንም ስለ ናቁ፣

በዚህ ሕዝብ ላይ የሐሳባቸውን ውጤት፣

ጥፋትን አመጣባቸዋለሁ።

20ዕጣን ከሳባ ምድር፣

ጣፋጩ ቅመም ከሩቅ አገር ቢመጣ ምን ይጠቅመኛል?

የሚቃጠል መሥዋዕታችሁን አልቀበልም፤

ሌላውም መሥዋዕታችሁ ደስ አያሰኙኝም።”

21ስለዚህ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“በዚህ ሕዝብ ፊት መሰናክልን አስቀምጣለሁ፤

አባቶችና ወንዶች ልጆች በአንድነት ይደናቀፉበታል፤

ጎረቤቶችና ባልንጀሮችም ይጠፋሉ።”

22እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“እነሆ፤ ሰራዊት፣

ከሰሜን ምድር እየመጣ ነው፤

ከምድር ዳርቻም፣

ታላቅ ሕዝብ እየተነሣሣ ነው።

23ቀስትና ጦር ይዘዋል፤

ጨካኞችና ምሕረት የለሽ ናቸው፤

ፈረሶቻቸውን ሲጋልቡ፣

ድምፃቸው እንደ ተናወጠ ባሕር ነው፤

የጽዮን ልጅ ሆይ፤ ለሰልፍ የታጠቁ ሆነው፣

ሊወጉሽ ይመጣሉ።”

24ስለ እነርሱ ወሬ ደርሶናል፤

ክንዶቻችንም ዝለዋል፤

ጭንቀት ይዞናል፤ እንደምታምጥም

ሴት ሆነናል።

25ጠላት ሰይፍ ታጥቋል፤

በየቦታውም ሽብር ሞልቷል፤

ስለዚህ ወደ ውጭ አትውጡ፤

በየመንገዱ አትዘዋወሩ።

26የሕዝቤ ልጅ ሆይ፤ ማቅ ልበሺ፤

በዐመድም ላይ ተንከባለዪ፤

አንድያ ልጁን እንዳጣ ሰው፣

ምርር ብለሽ አልቅሺ፤

አጥፊው በድንገት፣

በላያችን ይመጣልና።

27“ብረት እንደሚፈተን፣

የሕዝቤን መንገድ፣

አካሄዳቸውንም እንድትፈትን፣

አንተን ፈታኝ አድርጌሃለሁ።

28ሁሉም ለማማት የሚዞሩ፣

ድድር ዐመፀኞች፣

ናስና ብረት የሆኑ፣

ምግባረ ብልሹዎች ናቸው።

29ርሳሱን ለማቅለጥ፣

ወናፉ በብርቱ አናፋ፤

ግን ምን ይሆናል፣ ከንቱ ልፋት ነው፤

ክፉዎች ጠርገው አልወጡምና።

30እግዚአብሔር ንቋቸዋልና፣

የተናቀ ብር ተብለው ይጠራሉ።”

Thai New Contemporary Bible

เยเรมีย์ 6:1-30

เยรูซาเล็มถูกล้อม

1“วิ่งหนีเอาชีวิตรอดเถิด ชาวเบนยามินเอ๋ย!

จงหนีจากเยรูซาเล็ม!

จงเป่าแตรในเทโคอา!

ส่งสัญญาณขึ้นเหนือเบธฮัคเคเรม!

เพราะภัยพิบัติโผล่ขึ้นมาจากทางเหนือ

เป็นหายนะร้ายแรง

2เราจะทำลายธิดาแห่งศิโยน6:2 คือ ชาวเยรูซาเล็ม เช่นเดียวกับข้อ 23

ผู้งดงามและบอบบางเหลือเกิน

3คนเลี้ยงแกะและฝูงสัตว์ของเขาจะมาต่อสู้เธอ

พวกเขาจะตั้งเต็นท์ล้อมเมือง

แต่ละคนเลี้ยงสัตว์ของเขา”

4“จงเตรียมทำศึกกับศิโยน!

จงลุกขึ้น ให้เราบุกโจมตียามเที่ยงวัน!

แต่อนิจจา กลางวันคล้อยลงแล้ว

และร่มเงาของยามเย็นทอดยาว

5ดังนั้นจงลุกขึ้น ให้เราโจมตีตอนกลางคืน

และทำลายป้อมปราการต่างๆ เสีย!”

6พระยาห์เวห์ผู้ทรงฤทธิ์ตรัสว่า

“จงโค่นต้นไม้

แล้วก่อเชิงเทินเพื่อสู้กับเยรูซาเล็ม

กรุงนี้ต้องถูกลงโทษ

เพราะเต็มไปด้วยการกดขี่ข่มเหง

7ดั่งบ่อน้ำปล่อยน้ำไหลออกมา

กรุงนี้ก็ได้ปล่อยความชั่วร้ายออกมา

ความทารุณอำมหิตและการทำลายล้างดังกระหึ่มในเมืองนี้

ความเจ็บป่วยและบาดแผลของมันมีอยู่ต่อหน้าเราเสมอ

8เยรูซาเล็มเอ๋ย จงรับการเตือน

มิฉะนั้นเราจะเบือนหน้าหนีจากเจ้า

และทำให้ดินแดนของเจ้าถูกทิ้งร้าง

จนไม่มีใครอยู่อาศัยได้”

9พระยาห์เวห์ผู้ทรงฤทธิ์ตรัสว่า

“แม้แต่ชนอิสราเอลที่เหลืออยู่เพียงหยิบมือก็ต้องถูกทำลายซ้ำ

เหมือนคนเก็บองุ่น

ตรวจดูองุ่นแต่ละเถา

เพื่อเก็บพวกที่คลาดสายตาไป”

10จะให้ข้าพเจ้าพูดและเตือนใครได้?

ใครจะฟังข้าพเจ้า?

หูของพวกเขาถูกอุด6:10 ภาษาฮีบรูว่าไม่ได้เข้าสุหนัต

พวกเขาจึงไม่ได้ยิน

พระวจนะขององค์พระผู้เป็นเจ้าระคายหูของพวกเขา

พวกเขาจึงไม่อยากฟัง

11แต่พระพิโรธขององค์พระผู้เป็นเจ้าก็สุมอยู่ที่ข้าพเจ้า

สุดที่ข้าพเจ้าจะอัดอั้นไว้

“จงระบายออกมาเหนือเด็กๆ ตามท้องถนน

เหนือกลุ่มคนหนุ่มที่มาชุมนุมกัน

ทั้งสามีและภรรยาก็ไม่เว้น

รวมถึงคนเฒ่าคนแก่ที่ร่วงโรยไป

12บ้านเรือนของเขาจะตกเป็นของคนอื่น

พร้อมทั้งที่นาและภรรยา

เมื่อเรายื่นมือออก

ต่อสู้ประชากรที่อาศัยอยู่ในแผ่นดินนี้”

องค์พระผู้เป็นเจ้าประกาศดังนี้

13“ตั้งแต่ผู้น้อยที่สุดจนถึงผู้ใหญ่ที่สุด

ล้วนโลภมุ่งกำไร

พวกผู้เผยพระวจนะและปุโรหิตก็ไม่ต่างกัน

ล้วนโกหกหลอกลวง

14พวกเขาทำแผลให้ประชากรของเรา

ราวกับว่าไม่สาหัสรุนแรงเท่าไร

พวกเขากล่าวว่า ‘สันติสุข สันติสุข’

ทั้งๆ ที่ไม่มีสันติสุข

15พวกเขาละอายใจในความประพฤติอันน่าขยะแขยงของตนบ้างหรือเปล่า?

เปล่าเลย พวกเขาไม่ละอายสักนิด

ไม่รู้เลยว่าการมียางอายนั้นเป็นอย่างไร

ฉะนั้นพวกเขาจะล้มลงในหมู่ผู้ที่ล้มลง

เขาจะตกต่ำลงเมื่อเราลงโทษเขา”

องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสดังนั้น

16องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสว่า

“จงยืนที่ทางแพร่งและมองดู

จงถามถึงหนทางโบราณ

จงถามหาหนทางที่ดีและดำเนินในทางนั้น

แล้วเจ้าจะพบการพักสงบสำหรับจิตใจของเจ้า

แต่เจ้าพูดว่า ‘เราจะไม่ยอมเดินทางสายนั้น’

17เราตั้งยามไว้เหนือเจ้าและกล่าวว่า

‘ฟังเสียงแตรเถิด!’

แต่เจ้าพูดว่า ‘เราจะไม่ฟัง’

18ฉะนั้นจงฟังให้ดี ประชาชาติทั้งหลาย

เหล่าพยานเอ๋ย

จงสังเกตสิ่งที่จะเกิดขึ้นกับเขา

19แผ่นดินโลกเอ๋ย จงฟังเถิด

เรากำลังนำภัยพิบัติมาเหนือชนชาตินี้

เป็นผลจากแผนชั่วของพวกเขาเอง

เพราะพวกเขาไม่ยอมฟังถ้อยคำของเรา

และได้ละทิ้งบทบัญญัติของเรา

20เราแยแสอะไรกับเครื่องหอมจากเชบา

หรือเครื่องเทศอันหอมหวลจากแดนไกล?

เครื่องเผาบูชาของเจ้าไม่เป็นที่ยอมรับ

เครื่องบูชาทั้งหลายของเจ้าไม่ได้ทำให้เราพอใจ”

21ด้วยเหตุนี้องค์พระผู้เป็นเจ้าจึงตรัสว่า

“เราจะตั้งเครื่องกีดขวางไว้ต่อหน้าชนชาตินี้

ซึ่งจะทำให้ทั้งผู้เป็นบิดาและผู้เป็นบุตรสะดุดล้ม

เพื่อนบ้านและมิตรสหายจะพินาศ”

22องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสว่า

“ดูเถิด กองทัพจะมา

จากดินแดนทางเหนือ

ชนชาติยิ่งใหญ่กำลังถูกเร่งเร้า

จากทุกมุมโลก

23พวกเขามีทั้งธนูและหอก

โหดเหี้ยมและไร้ความเมตตา

เสียงควบม้าของพวกเขา

เหมือนเสียงทะเลคำราม

พวกเขายกกระบวนทัพมา

เพื่อโจมตีเจ้า ธิดาแห่งศิโยนเอ๋ย”

24เราได้ยินกิตติศัพท์เลื่องลือเกี่ยวกับกองทัพ

ของเขา

แขนขาของเราก็หมดเรี่ยวหมดแรง

ความทุกข์ทรมานเกาะกุมเรา

เราเจ็บปวดเหมือนผู้หญิงที่กำลังคลอดลูก

25อย่าออกไปที่ทุ่งนา

หรือเดินตามถนน

เพราะศัตรูถือดาบพร้อมที่จะสังหาร

และไม่ว่าจะหันไปทางไหนก็มีแต่ความสยดสยอง

26พี่น้องร่วมชาติเอ๋ย จงสวมเสื้อผ้ากระสอบ

และเกลือกกลิ้งอยู่ในกองขี้เถ้าเถิด

จงร้องไห้คร่ำครวญอย่างรันทดขมขื่น

เหมือนสูญเสียลูกชายคนเดียวที่มีอยู่

เพราะในทันทีทันใด

ผู้ทำลายล้างจะยกมาโจมตีเรา

27“เราได้ทำให้เจ้าเป็นนักวิเคราะห์แร่

และประชากรของเราเป็นสินแร่

เพื่อเจ้าจะสังเกต

และทดสอบวิถีทางต่างๆ ของพวกเขา

28พวกเขาล้วนเป็นนักกบฏดื้อด้าน

เที่ยวนินทาว่าร้ายไปทั่ว

พวกเขาเป็นเหมือนทองสัมฤทธิ์และเหล็ก

ล้วนประพฤติตัวเสื่อมทราม

29สูบลมก็สูบอย่างดุเดือด

เพื่อให้ไฟเผาตะกั่วให้หมดไป

แต่การถลุงก็เปล่าประโยชน์

คนชั่วไม่ถูกหลอมชำระให้บริสุทธิ์ได้เลย

30พวกเขาจะได้ชื่อว่าเป็น ‘เงินที่ถูกทิ้งแล้ว’

เพราะองค์พระผู้เป็นเจ้าได้ทรงละทิ้งพวกเขาแล้ว”