ኤርምያስ 5 – NASV & CCBT

New Amharic Standard Version

ኤርምያስ 5:1-31

ቅን ሰው አለመገኘቱ

1“በኢየሩሳሌም መንገዶች እስቲ ውጡ፤ ወደ ላይ ወደ ታችም ውረዱ፤

ዙሪያውን ተመልከቱ ቃኙ፤

በአደባባይዋም ፈልጉ፤

እውነትን የሚሻና በቅንነት የሚሄድ፣

አንድ ሰው እንኳ ብታገኙ፣

እኔ ይህችን ከተማ እምራታለሁ።

2‘ሕያው እግዚአብሔርን!’ ቢሉም፣

የሚምሉት በሐሰት ነው።”

3እግዚአብሔር ሆይ፤ ዐይኖችህ እውነትን አይመለከቱምን?

አንተ መታሃቸው፤ እነርሱ ግን አልተሰማቸውም፤

አደቀቅሃቸው፤ እነርሱ ግን አልታረሙም፤

ፊታቸውን ከድንጋይ ይልቅ አጠነከሩ

በንስሓ ለመመለስም አልፈለጉም።

4እኔም በልቤ እንዲህ አልሁ፤ “እነዚህ ድኾች ናቸው፤

ሞኞች ናቸው፤

የእግዚአብሔርን መንገድ፣

የአምላካቸውን ሕግ አላወቁምና።

5ስለዚህ ወደ ታላላቆቹ እሄዳለሁ፤

ለእነርሱም እናገራለሁ፤

በርግጥ እነርሱ የእግዚአብሔርን መንገድ፣

የአምላካቸውንም ሕግ ያውቃሉና።”

ነገር ግን እነርሱም ቢሆኑ ያው እንደዚያው ቀንበሩን ሰብረዋል፤

እስራቱንም በጥሰዋል።

6ስለዚህ አንበሳ ከዱር ወጥቶ ይሰባብራቸዋል፣

የበረሓ ተኵላም ይቦጫጭቃቸዋል፤

ብቅ የሚለውን ሰው ሁሉ ለመገነጣጠል፣

ነብር በከተሞቻቸው ዙሪያ ያደባል፤

ዐመፃቸው ታላቅ፣

ክሕደታቸው ብዙ ነውና።

7“ታዲያ፣ እንዴት ይቅር ልልሽ እችላለሁ?

ልጆችሽ ትተውኛል፤

እውነተኛውን አምላክ ትተው አማልክት ባልሆኑት ምለዋል፤

እስኪጠግቡ ድረስ መገብኋቸው፤

እነርሱ ግን አመነዘሩ፤

ወደ ጋለሞቶችም ቤት ተንጋጉ።

8እንደ ተቀለበ ብርቱ ድንጉላ ፈረስ ሆኑ፤

እያንዳንዱም የሌላውን ሚስት ተከትሎ አሽካካ።

9ስለ እነዚህ ነገሮች አልቀጣቸውምን?”

ይላል እግዚአብሔር

“እኔ ራሴ እንደዚህ ዐይነቱን ሕዝብ

አልበቀልምን?

10“ወደ ወይን አትክልቷ ስፍራ ገብታችሁ አበላሹት፤

ነገር ግን ፈጽማችሁ አታጥፉት፤

ቅርንጫፎቿን ገነጣጥሉ፤

የእግዚአብሔር አይደሉምና፤

11የእስራኤል ቤትና የይሁዳ ቤት፣

ፈጽመው ከድተውኛል፤”

ይላል እግዚአብሔር

12በእግዚአብሔር ላይ ሐሰትን ተናገሩ፤

እንዲህም አሉ፤ “እሱ ምንም አያደርግም!

ክፉ ነገር አይደርስብንም፤

ሰይፍም ራብም አናይም፤

13ነቢያቱ ነፋስ እንጂ ሌላ ነገር አይደሉም፤

ቃሉም በውስጣቸው የለም፤

ያሉት ሁሉ በእነርሱ ላይ ይመለስ።”

14ስለዚህ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ሕዝቡ ይህን ቃል ስለ ተናገረ፣

ቃሌን በአፍህ ውስጥ የሚፋጅ እሳት፣

ይህንም ሕዝብ ማገዶ አደርጋለሁ፤

እሳቱም ይበላቸዋል፤

15የእስራኤል ቤት ሆይ፤” ይላል እግዚአብሔር

“ከሩቅ ሕዝብን አመጣባችኋለሁ፤

ጥንታዊና ብርቱ፣

ቋንቋውን የማታውቁት፣ ንግግሩንም

የማትረዱት ሕዝብ ነው።

16የፍላጻቸው ሰገባ እንደ ተከፈተ መቃብር ነው፤

ሁሉም ብርቱ ተዋጊዎች ናቸው።

17ሰብልህንና ምግብህን ጠራርገው ይበሉብሃል፤

ወንዶችና ሴቶች ልጆችህን ይውጣሉ፤

በጎችህንና ከብቶችህን ይፈጃሉ፤

የወይን ተክሎችህንና የበለስ ዛፎችህን ያወድማሉ፤

የታመንህባቸውንም የተመሸጉ ከተሞች

በሰይፍ ያጠፏቸዋል።

18“ይሁን እንጂ፣ በዚያን ዘመን እንኳ” ይላል እግዚአብሔር፤ “ፈጽሜ አላጠፋችሁም። 19ሕዝቡ፣ ‘እግዚአብሔር አምላካችን ይህን ሁሉ ነገር ለምን አደረገብን?’ ብለው ቢጠይቁ፣ ‘እኔን፣ እንደ ተዋችሁኝና በራሳችሁ ምድር ባዕዳን አማልክትን እንዳገለገላችሁ፣ እንደዚሁ የእናንተ ባልሆነ ምድር ባዕዳንን ታገለግላላችሁ’ ትላቸዋለህ።

20“በያዕቆብ ቤት ይህን አሰሙ፤

በይሁዳም እንዲህ ብላችሁ ዐውጁ፤

21እናንት ዐይን እያላችሁ የማታዩ፣

ጆሮ እያላችሁ የማትሰሙ፣

ሞኞችና የማታስተውሉ ሰዎች ይህን ስሙ፤

22ልትፈሩኝ አይገባችሁምን?” ይላል እግዚአብሔር

“በእኔ ፊት ልትንቀጠቀጡስ አይገባምን?

ለዘላለም ዐልፎት መሄድ እንዳይችል፣

አሸዋን ለባሕር ድንበር አደረግሁ፤

ማዕበሉ እየጋለበ ቢመጣ ከዚያ አያልፍም፤

ሞገዱ ቢጮኽም ሊያቋርጠው አይችልም።

23ይህ ሕዝብ ግን የሸፈተና እልኸኛ ልብ አለው፤

መንገድ ለቆ ሄዷል፤

24በልባቸውም፣

‘የፊተኛውንና የኋለኛውን ዝናብ በጊዜው የሚያዘንበውን፣

መከርን በወቅቱ የሚያመጣልንን፣

አምላካችንን እግዚአብሔርን እንፍራ’ አላሉም።

25በደላችሁ እነዚህን አስቀርቶባችኋል።

ኀጢአታችሁ መልካሙን ነገር ከልክሏችኋል።

26“በሕዝቤ መካከል ክፉ ሰዎች አሉና፤

ወፍ እንደሚያጠምዱ ሰዎች፣

ወጥመድ ዘርግተው ሰው እንደሚይዙ ሰዎችም ያደባሉ።

27ወፎች እንደ ሞሉት ጐጆ፣

ቤታቸው በማጭበርበር የተሞላ ነው፤

ባለጠጎችና ኀያላን ሆነዋል፤

28ወፍረዋል፤ ሠብተዋልም።

ክፋታቸው ገደብ የለውም፤

ወላጅ የሌላቸው ፍትሕ እንዲያገኙ

አልቆሙላቸውም፤

ለድኾችም መብት አልተከራከሩም።

29ስለ እነዚህ ነገሮች ልቀጣቸው አይገባኝምን?”

ይላል እግዚአብሔር

እንዲህ ዐይነቶቹን ሕዝብ፣

እኔ ራሴ ልበቀላቸው አይገባኝምን?

30“የሚያስፈራና የሚያስደነግጥ ነገር

በምድሪቱ ላይ ሆኗል፤

31ነቢያት በሐሰት ትንቢት ይናገራሉ፤

ካህናት በነቢያቱ ምክር ያስተዳድራሉ፤

ሕዝቤም እንዲህ ያለውን ይወድዳሉ፤

ፍጻሜው ሲደርስ ግን ምን ታደርጉ ይሆን?”

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

耶利米書 5:1-31

耶路撒冷的罪

1耶和華說:

「你們在耶路撒冷街頭四處看看,

在廣場找找,

如果你們能找到一個公正誠實的人,

我就赦免這城。

2雖然他們憑永活的耶和華起誓,

卻口是心非。」

3耶和華啊,你要的不是誠實嗎?

你責打他們,他們不感到疼痛;

你嚴懲他們,他們仍不受教。

他們屢教不改,

臉比石頭還硬。

4我想:「他們貧窮、愚昧,

不明白他們上帝耶和華的道,

也不知道祂的法令。

5我要找他們的首領說話,

因為這些首領明白耶和華的道,

知道他們上帝的法令。」

然而,他們卻一致違背耶和華的律法,

不服從祂的法令。

6因此,林中的獅子必襲擊他們,

荒野的豺狼必殘害他們,

豹子也蹲伏在他們的城外,

伺機撕裂出城的人,

因為他們罪大惡極,屢屢叛道。

7耶和華說:

耶路撒冷啊,我怎能赦免你呢?

你的兒女背棄我,

憑假神起誓。

我供應他們的一切需要,

他們卻縱情淫亂,

湧向娼妓的家。

8他們像吃得肥壯、發情的公馬,

垂涎鄰居的妻子。

9我怎能不懲罰他們呢?

我怎能不親自報應這樣的國民呢?

這是耶和華說的。

10你們要去毀壞她的葡萄園,

但不可徹底毀壞。

要砍掉枝子,

因為那些枝子不屬於耶和華。

11以色列人和猶大人根本不忠於我。

這是耶和華說的。

12「他們撒謊說,

『耶和華不會管我們,

我們必不會遇到災禍、戰爭和饑荒。

13先知的話不過是一陣風,

不是來自上帝,

他們預言的災禍必降臨到自己身上。』」

14因此,萬軍之上帝耶和華對我說:

「因為他們說了這話,

我要使我的話在你口中成為火,

使他們像柴一樣被燒毀。

15以色列人啊,我要使一個國家,

一個歷久不衰的古國從遠方來攻擊你們,

你們不明白他們的語言,

也聽不懂他們說的話。

這是耶和華說的。

16他們都是勇士,

他們的弓箭殺人無數。

17他們必吞噬你們的兒女、牛羊、

糧食、葡萄和無花果,

用刀劍摧毀你們所依靠的堅城。」

18耶和華說:「即使在那時,我也不會徹底毀滅你們。 19耶利米啊,如果有人問,『為什麼我們的上帝耶和華這樣待我們?』你可以對他們說,『你們怎樣背棄耶和華,在自己的土地上供奉外族的神明,也要怎樣在異地他鄉服侍外族人。』

20「要在猶大雅各家高聲宣佈,

21『聽著,你們這群愚昧無知的人啊,

你們視而不見,

聽而不聞。

22難道你們不敬畏我嗎?

這是耶和華說的。

難道你們在我面前不顫抖嗎?

我以沙石為海的界限,

使水永遠不能越過它。

洶湧的波濤不能逾越,

澎湃的海浪不能漫過。

23但你們這些人頑固不化,

悖逆成性。

你們離我而去。

24你們心中從未說,

我們要敬畏我們的上帝耶和華,

祂按時降下秋雨和春雨,

讓我們按時收割。

25你們的罪過使你們不再風調雨順,

你們的罪惡使你們失去祝福。』

26我的子民中有惡人,

他們像捕鳥人一樣埋伏等候,

設下網羅陷害人。

27他們的家裡充滿了詭詐,

就像籠子裝滿了鳥。

他們變得有財有勢,

28吃得肥胖紅潤,

壞事做盡,不為孤兒伸冤,

不為窮人主持公道。」

29耶和華說:「我怎能坐視不理呢?

我怎能不懲罰這樣的國家呢?

30這地方發生了一件令人震驚、恐懼的事,

31就是先知說假預言,

祭司濫用權力,

我的子民卻以此為樂。

但當最後的結局來臨時,

他們還能做什麼呢?