ኤርምያስ 49 – NASV & NIVUK

New Amharic Standard Version

ኤርምያስ 49:1-39

ስለ አሞን የተነገረ መልእክት

1ስለ አሞናውያን፤

እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“እስራኤል ወንዶች ልጆች አልወለደምን?

ወራሾችስ የሉትምን?

ታዲያ፣ ሚልኮምሸ49፥1 ወይም ንጉሣቸው፤ ዕብራይስጡ መልካም ይላል፤ 3 ይመ። ጋድን ለምን ወረሰ?

የእርሱ ሰዎች ለምን በከተሞቿ ይኖራሉ?

2ስለዚህ በአሞናውያን ከተማ በረባት ላይ፣

የጦርነት ውካታ ድምፅ

የሚሰማበት ጊዜ ይመጣል፤”

ይላል እግዚአብሔር

“እርሷም የፍርስራሽ ክምር ትሆናለች፤

በዙሪያዋ ያሉት መንደሮችም ይቃጠላሉ፤

እስራኤልም ከአገሯ ያስወጧትን፣

ከአገሯ ታስወጣለች፤”

ይላል እግዚአብሔር

3“ሐሴቦን ሆይ፤ ጋይ ጠፍታለችና ዋይ በይ፤

የራባት ሴቶች ልጆች ሆይ ጩኹ፤

ማቅ ለብሳችሁ አልቅሱ፤

ሚልኮም ከካህናቱና ከመኳንንቱ ጋር፣

ተማርኮ ይወሰዳልና፣

በቅጥር ውስጥ ወዲያ ወዲህ ተሯሯጡ።

4አንቺ ከዳተኛ ልጅ ሆይ፤

በሸለቆችሽ ለምን ትመኪያለሽ?

ለምንስ በፍሬያማ ሸለቆሽ ትኵራሪያለሽ?

በብልጽግናሽ ተማምነሽ፣

‘ማን ሊነካኝ ይችላል?’ ትያለሽ።

5በዙሪያሽ ካሉት ሁሉ ዘንድ፣

ሽብር አመጣብሻለሁ፤”

ይላል የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር

“እያንዳንዳችሁ ትሰደዳላችሁ፤

በሽሽት ላይ ያሉትንም የሚሰበስብ አይገኝም።

6“ከዚያ በኋላ ግን፣ የአሞናውያንን ምርኮ እመልሳለሁ”

ይላል እግዚአብሔር

ስለ ኤዶም የተነገረ መልእክት

49፥9-10 ተጓ ምብ – አብ 5-6

49፥14-16 ተጓ ምብ – አብ 1-4

7ስለ ኤዶም፤

የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ጥበብ ከቴማን ጠፍቷልን?

ምክር ከአስተዋዮች ርቋልን?

ጥበባቸውስ ተሟጧልን?

8ዔሳውን በምቀጣ ጊዜ፣

ጥፋት ስለማመጣበት፣

እናንተ በድዳን የምትኖሩ ሆይ፤

ወደ ኋላ ተመልሳችሁ ሽሹ፤ ጥልቅ ጕድጓድ ውስጥ ተደበቁ።

9ወይን ለቃሚዎች ወደ አንተ ቢመጡ፣

ጥቂት ወይን አያስቀሩምን?

ሌቦችስ በሌሊት ቢመጡ፣

የሚሰርቁት የሚፈልጉትን ብቻ አይደለምን?

10እኔ ግን ዔሳውን አራቍተዋለሁ፤

መደበቅም እንዳይችል፣

መሸሸጊያ ስፍራዎቹን እገልጣለሁ፤

ልጆቹ፣ ዘመዶቹና ጎረቤቶቹ ይጠፋሉ፤

እርሱም ራሱ አይኖርም።

11ወላጆች የሌላቸውን ልጆችህን ተዋቸው፤ እኔ ለሕይወታቸው እጠነቀቃለሁ፤ መበለቶቻችሁም በእኔ ይታመኑ።”

12እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ “ከጽዋው መጠጣት የማይገባቸው ሊጠጡ ግድ ከሆነ፣ አንተ እንዴት ሳትቀጣ ትቀራለህ? መቀጣትህ አይቀርም፤ መጠጣት ይገባሃል። 13ባሶራ ፈራርሳ የድንጋጤ፣ የመዘባበቻና የርግማን ምልክት እንደምትሆን በራሴ ምያለሁ” ይላል እግዚአብሔር፤ “ከተሞቿም ሁሉ ለዘላለም ባድማ ይሆናሉ።”

14ከእግዚአብሔር ዘንድ መልእክት ሰምቻለሁ፤

“እርሷን ለመውጋት ተሰብሰቡ፤

ለጦርነትም ውጡ”

የሚል መልእክተኛ ወደ ሕዝቦች ተልኳል።

15“እነሆ፤ በሕዝቦች መካከል ታናሽ፣

በሰዎችም ዘንድ የተናቅህ አደርግሃለሁ።

16አንተ በዐለት ንቃቃት ውስጥ የምትኖር፣

የተራራውንም ከፍታ የያዝህ ሆይ፤

የምትነዛው ሽብር፣

የልብህም ኵራት አታልሎሃል፤

መኖሪያህን እንደ ንስር በከፍታ ቦታ ብትሠራም፣

ከዚያ ወደ ታች እጥልሃለሁ፤”

ይላል እግዚአብሔር

17“ኤዶም የድንጋጤ ምልክት ትሆናለች፤

ከቍስሎቿም ሁሉ የተነሣ፣

በዚያ የሚያልፍ ሁሉ በመደነቅ ያላግጥባታል።

18በዙሪያቸው ካሉት ከተሞች ጋር፣

ሰዶምና ገሞራ እንደ ተገለበጡ፣”

ይላል እግዚአብሔር

እንዲሁ ማንም በዚያ አይኖርም፤

አንድም ሰው አይቀመጥባትም።

19“አንበሳ ከዮርዳኖስ ደኖች፣

ወደ ግጦሽ ሜዳ ብቅ እንደሚል፣

እኔም በኤዶም ላይ ድንገት እወጣለሁ፤ ከምድሩም አባርረዋለሁ።

የመረጥሁትን በእርሱ ላይ እሾማለሁ፤

እንደ እኔ ያለ ማን ነው? ማንስ ሊገዳደረኝ ይችላል?

የትኛውስ እረኛ ሊቋቋመኝ ይችላል?”

20ስለዚህ እግዚአብሔር በኤዶም ላይ ያለውን ዕቅድ፣

በቴማን በሚኖሩትም ላይ ያሰበውን ሐሳብ ስሙ፤

ታናናሹ መንጋ ተጐትቶ ይወሰዳል፤

በእነርሱም ምክንያት መሰማሪያቸውን ፈጽሞ ያጠፋል።

21በውድቀታቸው ድምፅ ምድር ትናወጣለች፤

ጩኸታቸውም እስከ ቀይ ባሕር49፥21 ዕብራይስጡ ያም ሱፍ ይላል፤ ትርጕሙ የሸንበቆ ባሕር ማለት ነው። ያስተጋባል።

22እነሆ፤ እንደ ንስር ተወርውሮ ይወርድባታል፤

ክንፎቹንም በባሶራ ላይ ይዘረጋል፤

በዚያን ቀን የኤዶም ጦረኞች ልብ፣

በምጥ እንደ ተያዘች ሴት ልብ ይሆናል።

ስለ ደማስቆ የተነገረ መልእክት

23ስለ ደማስቆ፣

“ክፉ ወሬ ሰምተዋልና፣

ሐማትና አርፋድ ደንግጠዋል፤

እንደ49፥23 ዕብራይስጡ በተናወጠ ይላል። ተናወጠ ባሕርም ታውከዋል፤

ልባቸውም ቀልጧል።

24ደማስቆ ተዳከመች፤

ትሸሽም ዘንድ ወደ ኋላ ተመለሰች፤

ብርክ ያዛት፣

ምጥ እንደ ያዛት ሴት፣

ጭንቅና መከራ ዋጣት።

25ደስ የምሰኝባት፣

የታወቀችው ከተማ እንዴት ተተወች?

26በርግጥ ወንዶች ወጣቶቿ በየአደባባዩ ይረግፋሉ፤

በዚያ ቀን ወታደሮቿ ሁሉ ይወድቃሉ፤”

ይላል የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር

27“በደማስቆ ቅጥር ላይ እሳት እለኵሳለሁ፤

የወልደ አዴርንም ዐምባ ይበላል።”

ስለ ቄዳርና ስለ ሐጾር የተነገረ መልእክት

28የባቢሎን ንጉሥ ናቡከደነፆር ስለ ወጋቸው ስለ ቄዳርና ስለ ሐጾር መንግሥታት የተነገረ፤ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ተነሡ፣ ቄዳርን ውጉ፤

የምሥራቅንም ሕዝብ ደምስሱ።

29ድንኳኖቻቸውና መንጎቻቸው ይወሰዳሉ፤

መጠለያቸውና ግመሎቻቸው ሳይቀሩ፣

ከነዕቃዎቻቸው ይነጠቃሉ፤

ሰዎች፣ ‘ሽብር በሽብር ላይ መጥቶባቸዋል፤’

እያሉ ይጮኹባቸዋል።

30በሐጾር የምትኖሩ ሆይ፣

በጥድፊያ ሽሹ፤ በጥልቅ ጕድጓድ ተሸሸጉ፤”

ይላል እግዚአብሔር

የባቢሎን ንጉሥ ናቡከደነፆር በእናንተ ላይ ጠንክሯልና፣

ወረራም ዶልቶባችኋል።

31“ተነሡ፣ ተዘልሎ የተቀመጠውን፣

በራሱ ተማምኖ የሚኖረውን ሕዝብ ውጉ፤”

ይላል እግዚአብሔር

“መዝጊያና መቀርቀሪያ በሌለው፤

ለብቻው በሚኖረው ሕዝብ ላይ ዝመቱ።

32ግመሎቻቸው ይዘረፋሉ፤

ከብቶቻቸውንም አንጋግተው ይነዱባቸዋል፤

ጠጕሩን የሚቀነብበውን ወገን49፥32 ወይም በሩቅ ስፍራ ያለውን

እበትናለሁ፤ ከየአቅጣጫው መዓት አመጣባችኋለው።”

ይላል እግዚአብሔር

33“ሐጾር የቀበሮዎች መፈንጫ፣

ለዘላለም ባድማ ትሆናለች፤

ማንም በዚያ አይኖርም፤

የሚቀመጥባትም አይገኝም።”

ስለ ኤላም የተነገረ መልእክት

34በይሁዳ ንጉሥ በሴዴቅያስ ዘመነ መንግሥት መጀመሪያ ላይ ወደ ነቢዩ ወደ ኤርምያስ የመጣው የእግዚአብሔር ቃል ይህ ነው፤

35የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“እነሆ፤ የኀያልነቷን መሠረት፣

የኤላምን ቀስት እሰብራለሁ።

36ከአራቱ የሰማይ ማእዘናት፣

በኤላም ላይ አራቱን ነፋሳት አመጣለሁ፤

ወደ አራቱም ነፋሳት እበትናቸዋለሁ፤

ከኤላም የሚማረኩት የማይደርሱበት፣

አገር አይገኝም።

37ነፍሳቸውን በሚሹ ጠላቶቻቸው ፊት፣

ኤላምን አርበደብዳለሁ፤

በላያቸው ላይ መዓትን፣

ይኸውም ቍጣዬን አመጣባቸዋለሁ፤”

ይላል እግዚአብሔር

“ፈጽሜ አስካጠፋቸውም ድረስ፣

በሰይፍ አሳድዳቸዋለሁ።

38ዙፋኔን በኤላም እዘረጋለሁ፤

ነገሥታቷንና መኳንንቷን አጠፋለሁ፤”

ይላል እግዚአብሔር

39“ነገር ግን የኋላ ኋላ፣

የኤላምን ምርኮ እመልሳለሁ፤”

ይላል እግዚአብሔር

New International Version – UK

Jeremiah 49:1-39

A message about Ammon

1Concerning the Ammonites:

This is what the Lord says:

‘Has Israel no sons?

Has Israel no heir?

Why then has Molek49:1 Or their king; also in verse 3 taken possession of Gad?

Why do his people live in its towns?

2But the days are coming,’ declares the Lord,

‘when I will sound the battle cry

against Rabbah of the Ammonites;

it will become a mound of ruins,

and its surrounding villages will be set on fire.

Then Israel will drive out

those who drove her out,’

says the Lord.

3‘Wail, Heshbon, for Ai is destroyed!

Cry out, you inhabitants of Rabbah!

Put on sackcloth and mourn;

rush here and there inside the walls,

for Molek will go into exile,

together with his priests and officials.

4Why do you boast of your valleys,

boast of your valleys so fruitful?

Unfaithful Daughter Ammon,

you trust in your riches and say,

“Who will attack me?”

5I will bring terror on you

from all those around you,’

declares the Lord, the Lord Almighty.

‘Every one of you will be driven away,

and no-one will gather the fugitives.

6‘Yet afterwards, I will restore the fortunes of the Ammonites,’

declares the Lord.

A message about Edom

7Concerning Edom:

This is what the Lord Almighty says:

‘Is there no longer wisdom in Teman?

Has counsel perished from the prudent?

Has their wisdom decayed?

8Turn and flee, hide in deep caves,

you who live in Dedan,

for I will bring disaster on Esau

at the time when I punish him.

9If grape pickers came to you,

would they not leave a few grapes?

If thieves came during the night,

would they not steal only as much as they wanted?

10But I will strip Esau bare;

I will uncover his hiding-places,

so that he cannot conceal himself.

His armed men are destroyed,

also his allies and neighbours,

so there is no-one to say,

11“Leave your fatherless children; I will keep them alive.

Your widows too can depend on me.” ’

12This is what the Lord says: ‘If those who do not deserve to drink the cup must drink it, why should you go unpunished? You will not go unpunished, but must drink it. 13I swear by myself,’ declares the Lord, ‘that Bozrah will become a ruin and a curse,49:13 That is, its name will be used in cursing (see 29:22); or, others will see that it is cursed. an object of horror and reproach; and all its towns will be in ruins for ever.’

14I have heard a message from the Lord;

an envoy was sent to the nations to say,

‘Assemble yourselves to attack it!

Rise up for battle!’

15‘Now I will make you small among the nations,

despised by mankind.

16The terror you inspire

and the pride of your heart have deceived you,

you who live in the clefts of the rocks,

who occupy the heights of the hill.

Though you build your nest as high as the eagle’s,

from there I will bring you down,’

declares the Lord.

17‘Edom will become an object of horror;

all who pass by will be appalled and will scoff

because of all its wounds.

18As Sodom and Gomorrah were overthrown,

along with their neighbouring towns,’ says the Lord,

‘so no-one will live there;

no people will dwell in it.

19‘Like a lion coming up from Jordan’s thickets

to a rich pasture-land,

I will chase Edom from its land in an instant.

Who is the chosen one I will appoint for this?

Who is like me and who can challenge me?

And what shepherd can stand against me?’

20Therefore, hear what the Lord has planned against Edom,

what he has purposed against those who live in Teman:

the young of the flock will be dragged away;

their pasture will be appalled at their fate.

21At the sound of their fall the earth will tremble;

their cry will resound to the Red Sea.49:21 Or the Sea of Reeds

22Look! An eagle will soar and swoop down,

spreading its wings over Bozrah.

In that day the hearts of Edom’s warriors

will be like the heart of a woman in labour.

A message about Damascus

23Concerning Damascus:

‘Hamath and Arpad are dismayed,

for they have heard bad news.

They are disheartened,

troubled like49:23 Hebrew on or by the restless sea.

24Damascus has become feeble,

she has turned to flee

and panic has gripped her;

anguish and pain have seized her,

pain like that of a woman in labour.

25Why has the city of renown not been abandoned,

the town in which I delight?

26Surely, her young men will fall in the streets;

all her soldiers will be silenced in that day,’

declares the Lord Almighty.

27‘I will set fire to the walls of Damascus;

it will consume the fortresses of Ben-Hadad.’

A message about Kedar and Hazor

28Concerning Kedar and the kingdoms of Hazor, which Nebuchadnezzar king of Babylon attacked:

This is what the Lord says:

‘Arise, and attack Kedar

and destroy the people of the East.

29Their tents and their flocks will be taken;

their shelters will be carried off

with all their goods and camels.

People will shout to them,

“Terror on every side!”

30‘Flee quickly away!

Stay in deep caves, you who live in Hazor,’

declares the Lord.

‘Nebuchadnezzar king of Babylon has plotted against you;

he has devised a plan against you.

31‘Arise and attack a nation at ease,

which lives in confidence,’

declares the Lord,

‘a nation that has neither gates nor bars;

its people live far from danger.

32Their camels will become plunder,

and their large herds will be spoils of war.

I will scatter to the winds those who are in distant places49:32 Or who clip the hair by their foreheads

and will bring disaster on them from every side,’

declares the Lord.

33‘Hazor will become a haunt of jackals,

a desolate place for ever.

No-one will live there;

no people will dwell in it.’

A message about Elam

34This is the word of the Lord that came to Jeremiah the prophet concerning Elam, early in the reign of Zedekiah king of Judah:

35This is what the Lord Almighty says:

‘See, I will break the bow of Elam,

the mainstay of their might.

36I will bring against Elam the four winds

from the four quarters of heaven;

I will scatter them to the four winds,

and there will not be a nation

where Elam’s exiles do not go.

37I will shatter Elam before their foes,

before those who want to kill them;

I will bring disaster on them,

even my fierce anger,’

declares the Lord.

‘I will pursue them with the sword

until I have made an end of them.

38I will set my throne in Elam

and destroy her king and officials,’

declares the Lord.

39‘Yet I will restore the fortunes of Elam

in days to come,’

declares the Lord.