ኤርምያስ 47 – NASV & NVI

New Amharic Standard Version

ኤርምያስ 47:1-7

ስለ ፍልስጥኤማውያን የተነገረ መልእክት

1ፈርዖን ጋዛን ድል ከማድረጉ በፊት፣ ስለ ፍልስጥኤማውያን ወደ ነቢዩ ወደ ኤርምያስ የመጣው የእግዚአብሔር ቃል ይህ ነው፤

2እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“እነሆ፤ በሰሜን በኩል ውሃ እየሞላ ነው፤

ኀይለኛ ጐርፍ ይሆናል፤

አገሪቷንና በውስጧ ያሉትንም ሁሉ፣

ከተሞቿንና ነዋሪዎቻቸውን ያጥለቀልቃል።

ሕዝቡም ድምፁን ከፍ አድርጎ ይጮኻል፤

የምድሪቱ ነዋሪ ሁሉ ዋይ ዋይ ይላል፤

3ከፈረስ ኮቴ ድምፅ፣

ከጠላት ሠረገላ ጩኸትና

ከሠረገላው ሽክርክሪት ፍትጊያ ድምፅ የተነሣ፣

አባቶች ልጆቻቸውን ለመርዳት ወደ ኋላ መለስ አይሉም፤

እጃቸውም ስንኩል ይሆናል።

4ፍልስጥኤማውያንን ሁሉ ለማጥፋት፣

ተርፈውም የሚረዷቸውን ሁሉ፣

ከጢሮስና ከሲዶና ለመቍረጥ፣

ቀኑ ደርሷልና።

እግዚአብሔር በከፍቶር47፥4 ቀርጤስ ነው ዳርቻ የቀሩትን፣ ፍልስጥኤማውያንን ሊያጠፋ

ተነሥቷል።

5ጋዛ በማዘን ራሷን ትላጫለች፤

አስቀሎና አፏን ትይዛለች።

በሜዳማ ስፍራ የምትገኙ ቅሬታዎች ሆይ፤

እስከ መቼ ሰውነታችሁን ትቧጥጣላችሁ?

6“ ‘የእግዚአብሔር ሰይፍ ሆይ፤

የማታርፈው እስከ መቼ ነው?

ወደ ሰገባህ ተመልሰህ ግባ፤

ጸጥ ብለህ ተቀመጥ’ ትላላችሁ።

7ነገር ግን እግዚአብሔር አስቀሎናንና የባሕሩን ዳርቻ፣

እንዲወጋ ሲያዝዘው፣

እንዲፈጽመውም ትእዛዝ ሲሰጠው፣

እንዴት ማረፍ ይችላል?”

Nueva Versión Internacional

Jeremías 47:1-7

Mensaje para los filisteos

1Antes de que el faraón atacara Gaza, la palabra del Señor acerca de los filisteos vino al profeta Jeremías:

2«Así dice el Señor:

»“¡Miren! Las aguas del norte

suben cual torrente desbordado.

Inundan la tierra y todo lo que contiene,

sus ciudades y sus habitantes.

¡Grita toda la gente!

¡Gimen todos los habitantes de la tierra!

3Al oír el galope de sus corceles,

el estruendo de sus carros

y el estrépito de sus ruedas,

los padres abandonan a sus hijos

porque sus fuerzas desfallecen.

4Ha llegado el día

de exterminar a todos los filisteos

y de destruir a Tiro y Sidón

y a todos los aliados que puedan ayudarlos.

El Señor exterminará a los filisteos

y al resto de las costas de Caftor.47:4 Caftor. Es decir, Creta.

5Se rapan la cabeza los de Gaza;

se quedan mudos los de Ascalón.

Tú, remanente de la llanura,

¿hasta cuándo te harás incisiones?

6»”¡Ay, espada del Señor!

¿Cuándo vas a descansar?

¡Vuélvete a la vaina!

¡Detente, quédate quieta!

7¿Cómo va a descansar

si el Señor le ha dado órdenes

de atacar a Ascalón

y a la costa del mar?”».