ኤርምያስ 42 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ኤርምያስ 42:1-22

1የቃሬያን ልጅ ዮሐናንና የሆሻያን ልጅ ያእዛንያን42፥1 የዕብራይስጡና የሰብዓ ሊቃናት ትርጕሞች (43፥2 ይመ) አዛርያ ይላሉ። ጨምሮ፣ የጦር መኰንኖች ሁሉ እንዲሁም ሕዝቡ ሁሉ ከትንሹ እስከ ትልቁ ቀርበው፣ 2ነቢዩ ኤርምያስን እንዲህ አሉት፤ “ቀድሞ ብዙዎች ነበርን አሁን እንደምታየን ግን የቀረነው ጥቂት ነን፤ ስለዚህ እባክህ ልመናችንን ስማ፤ ለዚህ ለተረፈው ሕዝብ ሁሉ ወደ አምላክህ ወደ እግዚአብሔር ጸልይ። 3አምላክህ እግዚአብሔር ወዴት መሄድ እንዳለብንና ምን ማድረግ እንደሚገባን እንዲነግረን ጸልይልን።”

4ነቢዩ ኤርምያስም፣ “ሰምቻችኋለሁ፤ እንዳላችሁት ወደ አምላካችሁ ወደ እግዚአብሔር በርግጥ እጸልያለሁ፤ እግዚአብሔር ያለኝን ሁሉ አንዳች ሳላስቀር እነግራችኋለሁ” አላቸው።

5እነርሱም ኤርምያስን እንዲህ አሉት፤ “እግዚአብሔር አምላክህ በአንተ በኩል የሚለውን ነገር ሁሉ ባናደርግ፣ እግዚአብሔር ራሱ በእኛ ላይ እውነተኛና ታማኝ ምስክር ይሁን። 6አምላካችንን እግዚአብሔርን በመታዘዝ መልካም ይሆንልን ዘንድ ነገሩ ቢስማማንም ባይስማማንም፣ አንተን ወደ እርሱ የምንልክህን አምላካችንን እግዚአብሔርን እንታዘዛለን።”

7ከዐሥር ቀን በኋላ የእግዚአብሔር ቃል ወደ ኤርምያስ መጣ። 8ስለዚህ የቃሬያን ልጅ ዮሐናንንና፣ ከእርሱም ጋር የነበሩትን የጦር መኰንኖች ሁሉ እንዲሁም ሕዝቡን ሁሉ ከትንሽ እስከ ትልቅ ጠርቶ፤ 9እንዲህ አላቸው፤ “ልመናችሁን በፊቱ እንዳቀርብ ወደ እርሱ የላካችሁኝ የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ 10‘ባመጣሁባችሁ ጥፋት ዐዝኛለሁና፣ በዚህች ምድር ብትቀመጡ እሠራችኋለሁ እንጂ አላፈርሳችሁም፤ እተክላችኋለሁ እንጂ አልነቅላችሁም። 11አሁን የሚያስፈራችሁን የባቢሎንን ንጉሥ አትፍሩ፤ አድናችሁ ዘንድ ከእጁም አስጥላችሁ ዘንድ እኔ ከእናንተ ጋር ነኝና አትፍሩ ይላል እግዚአብሔር12እርሱ እንዲምራችሁና ወደ አገራችሁ እንዲመልሳችሁ እኔ እምራችኋለሁ።’

13“እናንተ ግን፤ ‘በዚህች ምድር አንቀመጥም’ ብትሉና አምላካችሁን እግዚአብሔርን ባትታዘዙ፣ 14ደግሞም፣ ‘ጦርነት ወደማናይበት፣ የመለከት ድምፅ ወደማንሰማበትና ወደማንራብበት ወደ ግብፅ ምድር ሄደን በዚያ እንኖራለን’ ብትሉ፣ 15እንግዲህ የይሁዳ ቅሬታ ሆይ፤ የእግዚአብሔርን ቃል ስሙ፤ የእስራኤል አምላክ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ ‘ወደ ግብፅ ለመሄድ ወስናችሁ እዚያ ለመቀመጥ ብትሄዱ፣ 16የፈራችሁት ሰይፍ በዚያ ያገኛችኋል፤ የሠጋችሁበት ራብ እስከ ግብፅ ድረስ ተከትሏችሁ ይመጣል፤ በዚያም ትሞታላችሁ። 17በዚያም ለመኖር ወደ ግብፅ ለመሄድ የወሰኑ ሁሉ በሰይፍ፣ በራብና በቸነፈር በርግጥ ይሞታሉ፤ ከማመጣባቸውም ጥፋት አንድ እንኳ የሚተርፍ ወይም የሚያመልጥ አይገኝም።’ 18የእስራኤል አምላክ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፣ ‘ቍጣዬና መዓቴ በኢየሩሳሌም በሚኖሩት ሁሉ ላይ እንደ ፈሰሰ፣ እንዲሁ ወደ ግብፅ በገባችሁ ጊዜ መዓቴ በእናንተ ላይ ይፈስሳል፤ እናንተም የመነቀፊያና የድንጋጤ፣ የመረገሚያና የመዘባበቻ ምልክት ትሆናላችሁ፤ ይህንም ስፍራ ዳግመኛ አታዩም።’

19“እናንተ የይሁዳ ቅሬታ ሆይ፤ እግዚአብሔር፤ ‘ወደ ግብፅ አትሂዱ’ ብሏችኋል፤ እኔም ዛሬ እንዳስጠነቀቅኋችሁ በርግጥ ዕወቁ፤ 20‘ወደ አምላካችን ወደ እግዚአብሔር ጸልይልን፤ እርሱ ያለህን ሁሉ ንገረን፤ እኛም እንታዘዛለን’ ብላችሁ ወደ አምላካችሁ ወደ እግዚአብሔር በላካችሁኝ ጊዜ ሕይወታችሁን የሚያጠፋ ስሕተት42፥20 ወይም በልባችሁ ስሕተት ሠራችሁ ፈጸማችሁ። 21እነሆ፤ ዛሬ በግልጥ ነገርኋችሁ፤ እናንተ ግን እግዚአብሔር አምላካችሁ ልኮኝ የነገርኋችሁን ሁሉ አሁንም አልታዘዛችሁም፤ 22እንግዲህ ሄዳችሁ ልትኖሩበት በፈለጋችሁት ስፍራ በሰይፍ፣ በራብና በቸነፈር እንደምትሞቱ በርግጥ ዕወቁ።”

Thai New Contemporary Bible

เยเรมีย์ 42:1-22

1แล้วบรรดาแม่ทัพนายกองรวมทั้งโยฮานันบุตรคาเรอาห์ เยซันยาห์42:1 ฉบับ LXX. ว่าอาซาริยาห์(ดู 43:2)บุตรโฮชายาห์ และประชากรทั้งปวงไม่ว่าผู้ใหญ่หรือผู้น้อยพากันมาหาผู้เผยพระวจนะเยเรมีย์ 2และกล่าวกับเขาว่า “โปรดฟังคำอ้อนวอนของเราและอธิษฐานต่อพระยาห์เวห์พระเจ้าของท่านเพื่อชนที่เหลืออยู่ทั้งหมดนี้ เพราะท่านก็เห็นแล้วว่า แม้แต่ก่อนเรามีกันมากมาย บัดนี้ก็เหลือเพียงหยิบมือเดียว 3โปรดอธิษฐานขอให้พระยาห์เวห์พระเจ้าของท่านบอกเราด้วยว่าควรไปที่ไหนและควรทำอะไร”

4ผู้เผยพระวจนะเยเรมีย์ตอบว่า “ข้าพเจ้าได้ยินแล้ว ข้าพเจ้าจะอธิษฐานต่อพระยาห์เวห์พระเจ้าของท่านตามที่ท่านขอร้องอย่างแน่นอน ข้าพเจ้าจะบอกท่านทุกอย่างตามที่องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัส จะไม่ปิดบังสิ่งใดจากพวกท่านเลย”

5แล้วพวกเขากล่าวกับเยเรมีย์ว่า “ขอองค์พระผู้เป็นเจ้าทรงเป็นพยานที่ซื่อตรงเที่ยงแท้ลงโทษเราเถิด หากเราไม่ยอมประพฤติตามทุกสิ่งที่พระยาห์เวห์พระเจ้าของท่านทรงใช้ท่านมาบอกเรา 6ไม่ว่าจะดีหรือร้าย เราก็จะเชื่อฟังพระยาห์เวห์พระเจ้าของเราผู้ซึ่งเราขอให้ท่านไปเข้าเฝ้าเพื่อจะเป็นประโยชน์สุขแก่เราเพราะเราจะเชื่อฟังพระยาห์เวห์พระเจ้าของเรา”

7สิบวันหลังจากนั้น มีพระดำรัสจากองค์พระผู้เป็นเจ้ามาถึงเยเรมีย์ 8ดังนั้นเขาจึงเรียกโยฮานันบุตรคาเรอาห์ บรรดาแม่ทัพนายกอง และประชาชนทั้งปวงไม่ว่าผู้ใหญ่หรือผู้น้อยมาชุมนุมกัน 9แล้วเขากล่าวแก่คนทั้งหลายว่า “พระยาห์เวห์พระเจ้าแห่งอิสราเอลซึ่งพวกท่านใช้ให้ข้าพเจ้าไปทูลอ้อนวอนนั้นตรัสว่า 10‘หากพวกเจ้าคงอยู่ในดินแดนนี้ เราจะสร้างเจ้าขึ้นไม่ใช่รื้อลง จะปลูกเจ้าไว้ ไม่ใช่ถอนราก เพราะเราเศร้าใจกับภัยพิบัติซึ่งเราบันดาลให้เกิดแก่เจ้า 11อย่ากลัวกษัตริย์บาบิโลนที่พวกเจ้ากลัวอยู่ในขณะนี้ อย่ากลัวเขาเลย องค์พระผู้เป็นเจ้าประกาศดังนี้ อย่ากลัวเขาเลยเพราะเราอยู่กับเจ้า เราจะช่วยเจ้าและกอบกู้เจ้าจากมือของเขา 12เราจะสำแดงความเมตตาแก่เจ้า เพื่อเขาจะเอ็นดูสงสารเจ้าและให้เจ้ากลับคืนสู่ดินแดนของเจ้า’

13“แต่หากพวกท่านกล่าวว่า ‘เราจะไม่ยอมอาศัยอยู่ในดินแดนแห่งนี้’ ซึ่งเป็นการไม่เชื่อฟังพระสุรเสียงของพระยาห์เวห์พระเจ้าของท่าน 14และถ้าท่านกล่าวว่า ‘เราจะไปอาศัยอยู่ในอียิปต์ จะได้ไม่ต้องเห็นสงคราม หรือได้ยินเสียงแตรศึก หรือหิวโหย’ 15ก็จงฟังพระดำรัสขององค์พระผู้เป็นเจ้าเถิด ชนหยิบมือที่เหลือแห่งยูดาห์เอ๋ย พระยาห์เวห์ผู้ทรงฤทธิ์ พระเจ้าแห่งอิสราเอลตรัสว่า ‘หากพวกเจ้าตั้งใจไปอียิปต์และตั้งรกรากอยู่ที่นั่น 16เมื่อนั้นสงครามและการกันดารอาหารที่เจ้ากลัวจะตามติดประชิดเจ้าไปถึงอียิปต์ และเจ้าจะตายที่นั่น 17คนทั้งปวงที่ตั้งใจไปตั้งรกรากที่อียิปต์จะตายเพราะสงคราม การกันดารอาหาร และโรคระบาด จะไม่มีสักคนที่รอดพ้นภัยพิบัติซึ่งเราจะนำมายังพวกเขา’ 18พระยาห์เวห์ผู้ทรงฤทธิ์ พระเจ้าแห่งอิสราเอลตรัสว่า ‘เช่นเดียวกับที่ความโกรธและโทสะของเราโหมกระหน่ำลงเหนือประชากรเยรูซาเล็ม เราก็จะระบายความโกรธลงเหนือเจ้าเมื่อเจ้าไปยังอียิปต์ เจ้าจะตกเป็นเป้าของการแช่งด่าและความสยดสยอง เป้าของคำสาปแช่งและตำหนิติเตียน เจ้าจะไม่มีวันได้เห็นสถานที่นี้อีก’

19“ชนหยิบมือที่เหลือของยูดาห์เอ๋ย องค์พระผู้เป็นเจ้าได้ตรัสสั่งพวกท่านแล้วว่า ‘อย่าไปที่อียิปต์’ จงมั่นใจในข้อนี้ คือข้าพเจ้าขอเตือนท่านในวันนี้ 20ท่านทำผิดอย่างร้ายแรงถึงตาย42:20 หรือเจ้าทำผิดอยู่ในใจเมื่อให้ข้าพเจ้าไปหาพระยาห์เวห์พระเจ้าของท่านและกล่าวว่า ‘จงอธิษฐานเผื่อเราต่อพระยาห์เวห์พระเจ้าของเรา จงบอกทุกสิ่งที่พระองค์ตรัส แล้วเราจะทำตาม’ 21ในวันนี้ข้าพเจ้าก็ได้แจ้งท่านแล้ว แต่ท่านกลับไม่เชื่อฟังพระสุรเสียงของพระยาห์เวห์พระเจ้าของท่าน ไม่ทำตามทุกสิ่งที่พระองค์ทรงใช้ข้าพเจ้ามาแจ้งท่าน 22ฉะนั้นขอให้มั่นใจได้เลยว่าท่านจะตายเพราะสงคราม การกันดารอาหาร และโรคระบาดในสถานที่ซึ่งท่านตั้งใจจะไปตั้งรกรากอยู่”