ኤርምያስ 22 – NASV & CCBT

New Amharic Standard Version

ኤርምያስ 22:1-30

በክፉዎች ነገሥታት ላይ የተሰጠ ፍርድ

1እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ “ወደ ይሁዳ ንጉሥ ቤተ መንግሥት ውረድ፤ ይህንም መልእክት በዚያ እንዲህ ብለህ ተናገር፤ 2‘በዳዊት ዙፋን የተቀመጥህ፣ የይሁዳ ንጉሥ ሆይ፤ አንተና መኳንንትህ፣ በእነዚህም በሮች የሚገባ ሕዝብህ፣ የእግዚአብሔርን ቃል ስሙ። 3እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ “ፍትሕንና ጽድቅን አድርጉ፤ የተበዘበዘውን ከጨቋኙ እጅ አድኑት፤ መጻተኛውን፣ ወላጅ የሌለውንና መበለቲቱን አትበድሉ፤ አትግፏቸውም፤ በዚህም ስፍራ ንጹሕ ደም አታፍስሱ። 4እነዚህን ትእዛዞች በሚገባ ብትጠብቁ፣ በዳዊት ዙፋን ላይ የሚቀመጡ ነገሥታት፣ ከመኳንንታቸውና ከሕዝባቸው ጋር በሠረገሎችና በፈረሶች ተቀምጠው በዚህ ቤተ መንግሥት በሮች ይገባሉ፤ ይወጣሉም። 5ነገር ግን እነዚህን ትእዛዞች ባትጠብቁ፣ ይህ ቤተ መንግሥት እንዲወድም በራሴ ምያለሁ፤” ይላል እግዚአብሔር።’ ”

6ስለዚህ እግዚአብሔር ስለ ይሁዳ ንጉሥ ቤተ መንግሥት እንዲህ ይላል፤

“አንተ ለእኔ እንደ ገለዓድ፣

እንደ ሊባኖስ ተራራ ጫፍ ውብ ብትሆንም፣

በርግጥ እንደ ምድረ በዳ፣

ሰው እንደማይኖርባቸው ከተሞች አደርግሃለሁ።

7በነፍስ ወከፍ መሣሪያ የሚይዙትን፣

አጥፊዎችን በአንተ ላይ አዘጋጃለሁ።

ምርጥ የዝግባ ዛፎችን ይቈርጣሉ፤

ወደ እሳትም ይጥሏቸዋል።

8“ከተለያየ አገር የመጡ ሕዝቦች በዚህች ከተማ በኩል ሲያልፉ፣ ‘እግዚአብሔር በዚህች ታላቅ ከተማ ላይ ለምን እንዲህ አደረገ?’ እያሉ እርስ በርስ ይነጋገራሉ፤ 9ከዚያም፣ ‘የአምላካቸውን የእግዚአብሔርን ኪዳን ትተው ሌሎችን አማልክት ስላመለኩና ስላገለገሉ ነው’ ይላሉ።”

10ከእንግዲህ ስለማይመለስ፣

የተወለደባትንም ምድር ዳግመኛ ስለማያይ፣

ለተማረከው ንጉሥ አምርራችሁ አልቅሱ እንጂ፣

ቀድሞ ለሞተው አታልቅሱ፤ አትዘኑም።

11በአባቱ ምትክ በይሁዳ ላይ ስለ ነገሠው፣ ከዚህ ስፍራ በምርኮ ስለ ተወሰደው፣ ስለ ኢዮስያስ ልጅ ስለ ሰሎ22፥11 ኢዮአካዝ ተብሎም ይጠራል። እግዚአብሔር እንዲህ ይላልና፤ “ከእንግዲህ አይመለስም፤ 12ተማርኮ በሄደበት አገር ይሞታል እንጂ ይህችን ምድር ዳግመኛ አያይም።”

13“ቤተ መንግሥቱን በግፍ ለሚሠራ፣

ሰገነቱንም ፍትሕ በማዛባት ለሚገነባ፣

ወገኑን በነጻ ለሚያሠራ፣

የድካሙንም ዋጋ ለማይከፍለው፣

14‘ባለ ትልልቅ ሰገነት፣

ሰፊ ቤተ መንግሥት ለራሴ እሠራለሁ’ ለሚል ወዮለት!

ሰፋፊ መስኮቶችን ያበጅለታል፤

በዝግባ ዕንጨት ያስጌጠዋል፤

ቀይ ቀለምም ይቀባዋል።

15“በዝግባ ዕንጨት ብዛት፣

የነገሥህ ይመስልሃልን?

አባትህስ ፍትሕንና ጽድቅን በማድረጉ፣

የሚበላውና የሚጠጣው ጐድሎት ነበርን?

እነሆ፤ ሁሉም መልካም ሆነለት።

16የድኾችንና የችግረኞችን ፍትሕ አላጓደለም፤

ስለዚህም ሁሉ መልካም ሆነለት።

እኔን ማወቅ ማለት ይህ አይደለምን?”

ይላል እግዚአብሔር

17“የአንተ ዐይንና ልብ ያረፉት ግን፣

አጭበርብሮ ጥቅምን በማግኘት፣

የንጹሑን ደም በማፍሰስ፣

ጭቈናንና ግፍን በመሥራት ላይ ብቻ ነው።”

18ስለዚህ እግዚአብሔር ስለ ይሁዳ ንጉሥ ስለ ኢዮስያስ ልጅ ስለ ኢዮአቄም እንዲህ ይላል፤

“ ‘ዋይ ወንድሜ! ዋይ፣ እኅቴን!’

ብለው አያለቅሱለትም።

‘ዋይ፣ ጌታዬን! ዋይ፣ ለግርማዊነቱ!’

ብለውም አያለቅሱለትም።

19አህያ እንደሚቀበር ይቀበራል፤

ከኢየሩሳሌም በሮች ውጪ፤

ተጐትቶ ይጣላል።

20“ሊባኖስ ላይ ወጥተሽ ጩኺ፤

ድምፅሽን በባሳን አሰሚ፤

በዓባሪም ሆነሽ ጩኺ፤

ወዳጆችሽ ሁሉ ወድመዋልና።

21ተመችቶሽ በነበረ ጊዜ አስጠነቀቅሁሽ፤

አንቺ ግን፣ ‘አልሰማም’ አልሽ፤

ከትንሽነትሽ ጀምሮ መንገድሽ ይኸው ነበር፤

ቃሌንም አልሰማሽም።

22እረኞችሽ ሁሉ በነፋስ ይወሰዳሉ፤

ወዳጆችሽም ተማርከው ይሄዳሉ፤

ከክፋትሽም ሁሉ የተነሣ፣

ታፍሪያለሽ፤ ትዋረጂያለሽም።

23አንቺ፣ ‘በሊባኖስ’22፥23 ሊባኖስ የተባለው በኢየሩሳሌም ያለው ቤተ መንግሥት ነው (1ነገ 7፥23 ይመ)። ውስጥ የምትኖሪ፣

መኖሪያሽን በዝግባ ዛፍ የሠራሽ ሆይ፤

ምጥ እንደ ያዛት ሴት፣

መከራ በላይሽ ሲመጣ ጩኸትሽ እንዴት ይሆን!

24“በሕያውነቴ እምላለሁ”፤ ይላል እግዚአብሔር “የይሁዳ ንጉሥ የኢዮአቄም ልጅ ኢኮንያን22፥24 በዕብራይስጥ ኮንያ ሲሆን የኢዮአኪን አቻ ስም ቃል ነው፤ 28 ይመ። የቀኝ እጄ የቀለበት ማኅተም ብትሆን እንኳ ኖሮ፣ አውልቄ እጥልሃለሁ፤ 25ሕይወትህን ለሚሿት፣ ለምትፈራቸው ለባቢሎናውያንና22፥25 ወይም ከለዳውያን ለባቢሎን ንጉሥ ለናቡከደነፆር አሳልፌ እሰጥሃለሁ። 26አንተንና የወለደችህን እናትህን ወዳልተወለዳችሁበት ወደ ሌላ አገር ወርውሬ እጥላችኋለሁ፤ በዚያም ትሞታላችሁ። 27ልትመለሱባት ወደ ምትናፍቋት ምድር ከቶ አትመለሱም።”

28ይህ ኢኮንያን የተባለ ሰው፣ የተናቀና የተሰበረ ገንቦ፣

ማንም የማይፈልገው ዕቃ ነውን?

እርሱና ልጆቹ ለምን ወደ ውጪ ተጣሉ?

ወደማያውቁትስ ምድር ለምን ተወረወሩ?

29ምድር ሆይ፤ አንቺ ምድር፣ አንቺ ምድር፤

የእግዚአብሔርን ቃል ስሚ!

30እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“አንድ እንኳ የረባ ዘር የማይወጣለት፣

አንድ እንኳ በዳዊት ዙፋን የሚቀመጥ፣

ወይም በይሁዳ የሚገዛ የማይኖረው ነውና፤

በሕይወት ዘመኑ የማይከናወንለት፣

መካን ሰው ብላችሁ መዝግቡት።”

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

耶利米書 22:1-30

警告猶大的王

1耶和華對我說:「你下到猶大王的宮殿,這樣宣告, 2『坐在大衛寶座上的猶大王啊,你和你的臣僕以及進出這城門的百姓都要聽耶和華的話。 3耶和華說,你們為人要公義正直,要從欺壓者手中解救受剝削的人。不要欺凌、虐待異鄉人和孤兒寡婦,不可在這地方濫殺無辜。 4如果你們遵守我的命令,大衛的子孫必繼續做王,並乘車、騎馬率領臣民進出王宮。 5但如果你們不遵守我的命令,我憑自己起誓,這王宮必淪為廢墟。這是耶和華說的。』」

6論到猶大王的宮殿,耶和華說:

「雖然它在我眼中美如基列

又像黎巴嫩的山峰,

但我必使它變成不毛之地,

變成杳無人煙的城邑。

7我要派人拿著兵器來摧毀它,

他們要砍下它最好的香柏木,

扔進火裡。

8「各國的人經過這城時都會彼此議論說,『為什麼耶和華這樣對待這座大城?』 9有人會回答,『因為城裡的人背棄了他們的上帝耶和華的約,供奉、祭拜其他神明。』」

10你們不要為死去的王哀哭,

要為被擄走的王哀哭,

因為他必一去不返,

再也看不到自己的家園。

11論到接替父親約西亞猶大王、後來被擄走的沙龍22·11 沙龍」也叫「約哈斯」。,耶和華說:「他必一去不返, 12客死異鄉,永別故土。」

對約雅敬的審判

13耶和華說:

約西亞的兒子猶大約雅敬啊,你有禍了!

你以不公不義的手段建造宮廷殿宇,

不給工人發工錢。

14你說要為自己建造宏偉的宮殿、寬敞的房間。

你安上窗戶,

鑲上香柏木,

塗上紅漆。

15難道你大肆使用香柏木就能顯出你做王的氣派嗎?

你父親也吃也喝,

但他秉公行義,

所以他凡事順利;

16他為困苦和貧窮的人伸冤,

所以他凡事順利。

這才是真正認識我。

這是耶和華說的。

17可是,你一心貪圖不義之財,

濫殺無辜,橫徵暴斂。」

18因此,論到猶大約西亞的兒子約雅敬,耶和華說:

「沒有人會為他哀悼說,

『唉,我的弟兄啊!

唉,我的姊妹啊!』

沒有人會為他哀悼說,

『唉,主人啊!

唉,他的尊榮!』

19你必像死驢一樣被拖到耶路撒冷的城門外,曝屍荒野。」

對耶路撒冷的警告

20耶路撒冷人啊,

你們要上黎巴嫩大聲哭喊,

巴珊哀號,

亞巴琳痛哭,

因為你們的盟友被消滅了。

21在你們興盛的時候,

我曾警告過你們,

你們卻不聽。

你們從小就叛逆,

不聽我的話。

22你們的首領都要被風捲去,

你們的盟友都要被擄走,

你們必因自己的惡行而蒙羞受辱。

23住在黎巴嫩、安居在香柏木宮殿中的人啊,

當婦人分娩般的痛苦臨到你們的時候,

你們將怎樣呻吟呢!」

對哥尼雅的審判

24耶和華說:「猶大約雅敬的兒子哥尼雅22·24 哥尼雅」即「耶哥尼雅」,又叫「約雅斤」。啊,我憑我的永恆起誓,即使你是我右手上蓋章的戒指,我也要把你摘下來, 25交給那些想殺你的人,交給你所懼怕的人,就是巴比倫尼布甲尼撒和他的迦勒底軍隊。 26我要把你和你母親趕到異鄉,那裡不是你們的出生之地,卻是葬身之處。 27你們渴望回到故鄉,卻不能如願以償。」

28難道哥尼雅是個被人鄙視、無人理睬的破瓶子嗎?

為什麼他和他的子孫被趕到陌生之地?

29大地啊,大地啊,大地啊,

要聽耶和華的話!

30耶和華說:

「你要把這人作為無兒無女、

一生失敗的人記錄下來,

因為他的後裔中無一人能成功地繼承大衛的寶座,

統治猶大。」