ኤርምያስ 21 – NASV & BPH

New Amharic Standard Version

ኤርምያስ 21:1-14

ለንጉሥ ሴዴቅያስ የተሰጠ ምላሽ

1የይሁዳ ንጉሥ ሴዴቅያስ፣ የመልክያን ልጅ ጳስኮርን እንዲሁም የመዕሤያን ልጅ ካህኑን ሶፎንያስን ወደ እርሱ በላከ ጊዜ፣ ቃል ከእግዚአብሔር ወደ ኤርምያስ መጣ፤ የተላኩትም እንዲህ ብለውት ነበር፤ 2“የባቢሎን ንጉሥ ናቡከደነፆር21፥2 ናቡከደነፆር አቻ የሆነው የዕብራይስጡ ናቡከደነፆር በዚህ ክፍልና ብዙ ጊዜ በኤርምያስና ሕዝቅኤል መጽሐፍ ይገኛል። ሊወጋን ስለሆነ፣ እባክህን ፈጥነህ፣ እግዚአብሔርን ጠይቅልን፤ ምናልባት ንጉሡ ከእኛ ይመለስ ዘንድ እግዚአብሔር እንደ ቀድሞው ታምራት ያደርግልን ይሆናል” ብለው ነበር።

3ኤርምያስ ግን እንዲህ አላቸው፤ “ለሴዴቅያስ እንዲህ ብላችሁ ንገሩት፤ 4‘የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ ከቅጥሩ ውጭ የከበቧችሁን የባቢሎንን ንጉሥና ባቢሎናውያንን21፥4 ወይም ከለዳውያን፤ 9 ላይ ይመ። ለመውጋት በእጃችሁ የያዛችሁትን የጦር መሣሪያ በእናንተው ላይ አዞራለሁ፤ ወደዚህችም ከተማ ሰብስቤ አስገባቸዋለሁ። 5እኔ ራሴ ለቅጣት በተዘረጋ እጅና በብርቱ ክንድ፣ በቍጣና በመዓት፣ በታላቅም መቅሠፍት እወጋችኋለሁ። 6በዚህች ከተማ የሚኖሩትን፣ ሰዎችንም ሆኑ እንስሳትን እመታለሁ፤ እነርሱም በታላቅ መቅሠፍት ይሞታሉ። 7ከዚያ በኋላ፣ ይላል እግዚአብሔር፤ የይሁዳን ንጉሥ ሴዴቅያስንና መኳንንቱን፣ ከመቅሠፍት፣ ከሰይፍና ከራብ የተረፈውንም ሕዝብ ለባቢሎን ንጉሥ ለናቡከደነፆርና ሕይወታቸውን ለማጥፋት ለሚሹ ጠላቶቻቸው አሳልፌ እሰጣለሁ፤ እርሱም በሰይፍ ይመታቸዋል፤ አያዝንላቸውም፤ አይራራላቸውም፤ አይምራቸውምም።’

8“በተጨማሪም ለዚህ ሕዝብ እንዲህ በል፤ ‘እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ “እነሆ፤ የሕይወትን መንገድና የሞትን መንገድ በፊታችሁ አድርጌአለሁ፤ 9በዚህች ከተማ የሚቈይ ሁሉ በሰይፍ፣ በራብና በመቅሠፍት ይሞታል፤ ወጥቶ ለከበቧችሁ ባቢሎናውያን እጁን የሚሰጥ ግን ነፍሱን ያተርፋል፤ በሕይወትም ይኖራል። 10በዚህች ከተማ ላይ በጎ ሳይሆን ክፉ ለማድረግ ወስኛለሁ፤” ይላል እግዚአብሔር፤ ለባቢሎን ንጉሥ ትሰጣለች፤ እርሱም በእሳት ያጠፋታል።’

11“ለይሁዳ ንጉሥ ቤትም እንዲህ በል፤ ‘የእግዚአብሔርን ቃል ስሙ፤ 12የዳዊት ቤት ሆይ፤ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ ‘ካደረጋችሁት ክፋት የተነሣ፣

ቍጣዬ እንዳይቀጣጠል፣

ማንም ሊያጠፋው እስከማይችል እንዳይነድድ፣

በየማለዳው ፍትሕን አድርጉ፤

የተበዘበዘውን ሰው፣

ከጨቋኙ እጅ አድኑት።

13ከሸለቆው በላይ፣

በድንጋያማው ዐምባ ላይ የምትኖሪ ሆይ፤

እኔ በአንቺ ላይ ወጥቻለሁ፤ ይላል እግዚአብሔር

“ማን በእኛ ላይ ይወጣል?

ማንስ ወደ መኖሪያችን ደፍሮ ይገባል?” የምትሉ ሆይ፤

14እንደ ሥራችሁ መጠን እቀጣችኋለሁ፤

ይላል እግዚአብሔር

በዱሯም እሳት እለኵሳለሁ፤

በዙሪያዋ ያለውንም ሁሉ ይበላል።’ ”

Bibelen på hverdagsdansk

Jeremiasʼ Bog 21:1-14

Gud afslår kongens anmodning om hjælp

1Kong Zidkija sendte senere Pashhur, Malkijas søn, og præsten Sefanja, Ma’asejas søn, til Jeremias med følgende anmodning: 2„Bed Herren om at hjælpe os, for kong Nebukadnezar af Babylonien har belejret byen. Forhåbentlig vil Herren være barmhjertig og gøre et mirakel som i gamle dage, så Nebukadnezar bliver tvunget til at trække sine tropper tilbage.”

3-4Jeremias svarede: „Gå tilbage til kong Zidkija med denne besked fra Herren, Israels Gud: Jeg vil sørge for, at dine krigere, som netop nu kæmper imod den babyloniske konge og hans hær, må give op og flygte tilbage ind i byen. 5Jeg kæmper personligt imod jer med min vældige magt, for min vrede er stor. 6Jeg vil lade en epidemi bryde ud i byen, så både mennesker og dyr omkommer. 7Derefter vil jeg overgive kong Zidkija, hans embedsmænd og de overlevende indbyggere til kong Nebukadnezar, som vil slå dem ned uden medfølelse eller barmhjertighed.

8Endvidere siger Herren til sit folk: Jeg stiller jer over for et valg. Vil I dø eller leve? 9De, som bliver i Jerusalem, vil dø i kampen, eller på grund af sult eller sygdom. Men de, som går ud og overgiver sig til babylonierne, vil overleve. 10Jeg har besluttet at bringe en katastrofe over denne by, siger Herren. Den babyloniske konge vil indtage den og brænde den ned til grunden.

11-12Og til Judas konge siger Herren: Vær altid retfærdig overfor dine undersåtter. Hjælp dem, som bliver bestjålet eller uretfærdigt behandlet. Gør, hvad der er det rigtige, ellers vil min vrede blusse op imod dig som en fortærende ild på grund af alle dine synder. 13Jeg vil kæmpe imod Jerusalem, den stolte by, der praler af at være uindtagelig og sikker på bjergets top. 14Jeg vil selv straffe dig for dit oprør og dine onde handlinger, siger Herren. Jeg sætter ild til dit fornemme palads,21,14 Ordret „skoven”, men det er en henvisning til paladset, som var bygget af udsøgte træsorter. Jf. 22,6. og alt, hvad der er i nærheden, skal brændes op.”