ኤርምያስ 18 – NASV & JCB

New Amharic Standard Version

ኤርምያስ 18:1-23

በሸክላ ሠሪው ቤት

1ከእግዚአብሔር ወደ ኤርምያስ እንዲህ የሚል ቃል መጣ፦ 2“ተነሥተህ ወደ ሸክላ ሠሪው ቤት ውረድ፤ በዚያ መልእክቴን እሰጥሃለሁ።” 3እኔም ወደ ሸክላ ሠሪው ቤት ወረድሁ፤ ሸክላውንም በመንኰራኵር ላይ ይሠራ ነበር። 4ከጭቃ ይሠራው የነበረውም ሸክላ በእጁ ላይ ተበላሸ፤ ሸክላ ሠሪውም በሚፈልገው ሌላ ቅርጽ መልሶ አበጀው።

5የእግዚአብሔርም ቃል ወደ እኔ እንዲህ ሲል መጣ፤ 6“የእስራኤል ቤት ሆይ፤ ሸክላ ሠሪው እንደሚሠራው፣ እኔ በእናንተ ላይ መሥራት አይቻለኝምን?” ይላል እግዚአብሔር፤ “የእስራኤል ቤት ሆይ፤ ጭቃው በሸክላ ሠሪው እጅ እንዳለ፣ እናንተም እንዲሁ በእጄ ውስጥ ናችሁ። 7አንድ ሕዝብ ወይም መንግሥት እንዲነቀል፣ እንዲፈርስና እንዲጠፋ በተናገርሁ ጊዜ፣ 8ያስጠነቀቅሁት ሕዝብ ከክፋቱ ቢመለስ፣ እኔ ላደርስበት ያሰብሁትን ክፉ ነገር እተዋለሁ። 9በሌላም ጊዜ አንድን ሕዝብ ወይም መንግሥት አንጸውና እተክለው ዘንድ ተናግሬ፣ 10በፊቴ ክፉ ነገር ቢያደርግና ባይታዘዘኝ፣ አደርግለታለሁ ብዬ ያሰብሁትን መልካም ነገር አስቀርበታለሁ።

11“አሁንም እንግዲህ ለይሁዳ ሕዝብና በኢየሩሳሌም ለሚኖሩ እንዲህ በላቸው፤ ‘እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ “እነሆ፤ ጥፋትን እያዘጋጀሁላችሁ ነው፤ ክፋትንም እየጠነሰስሁላችሁ ነው። ስለዚህ ሁላችሁ ከክፉ መንገዳችሁ ተመለሱ፤ መንገዳችሁንና ተግባራችሁን አቅኑ።” ’ 12እነርሱ ግን፣ ‘በከንቱ አትድከም፤ ባቀድነው እንገፋበታለን፤ እያንዳንዳችንም የክፉ ልባችንን እልኸኝነት እንከተላለን’ ይላሉ።”

13ስለዚህ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“እስቲ አሕዛብን፣

‘እንዲህ ዐይነት ነገር በመካከላችሁ ተሰምቶ ያውቃል?’ ብላችሁ ጠይቁ።

ድንግሊቱ እስራኤል፣

እጅግ ክፉ ነገር አድርጋለች።

14የሊባኖስ ተራራ ድንጋያማ ተረተር፣

በረዶ ተለይቶት ያውቃልን?

ከጋራው የሚወርደውስ ቀዝቃዛ ውሃ፤

መፍሰሱን ያቋርጣልን?18፥14 በዕብራይስጡ የዚህ ዐረፍተ ነገር ትርጕም በግልጽ አይታወቅም።

15ሕዝቤ ግን ረስቶኛል፤

ለማይረቡ ነገሮች ዐጥኗል፣

በራሱ መንገድ፣

በቀደሞው ጐዳና ተሰናክሏል፤

በሻካራው መሄጃ፣

ባልቀናውም ጥርጊያ መንገድ ሄዷል።

16ምድራቸው ባድማ፣

ለዘላለም መሣለቂያ ይሆናል፤

በዚያ የሚያልፍ ሁሉ ይደነቃል፤

በመገረምም ራሱን ይነቀንቃል።

17ከምሥራቅ እንደሚወጣ ነፋስ፣

በጠላቶቻቸው ፊት እበትናቸዋለሁ፤

በመጥፊያቸው ቀን፣

ጀርባዬን እንጂ ፊቴን አላሳያቸውም።”

18እነርሱም፣ “ሕግ ከካህናት፣ ምክር ከጠቢባን፣ ቃልም ከነቢያት ስለማይታጣ ኑና በኤርምያስ ላይ እንማከር፤ ኑ፤ በአንደበታችን እናጥቃው፣ እርሱ የሚናገረውንም ሁሉ አንስማ” አሉ።

19እግዚአብሔር ሆይ፤ ስማኝ፤

ባላንጣዎቼ የሚሉትን አድምጥ።

20የመልካም ተግባር ወሮታው ክፉ ነውን?

እነርሱ ግን ጕድጓድ ቈፈሩልኝ፤

ቍጣህን ከእነርሱ እንድትመልስ፣

በፊትህ ቆሜ፣

ስለ እነርሱ እንደ ተናገርሁ ዐስብ።

21ስለዚህ ልጆቻቸውን ለራብ፣

ለሰይፍም ስለት አሳልፈህ ስጥ፤

ሚስቶቻቸው የወላድ መካን፣ መበለትም ይሁኑ፤

ወንዶቻቸው በሞት ይቀሠፉ፤

ጕልማሶቻቸው በጦር ሜዳ ለሰይፍ ይዳረጉ።

22ሊይዙኝ ጕድጓድ ስለ ቈፈሩ፣

ለእግሮቼም በስውር ወጥመድ ስለ ዘረጉ፣

በድንገት ወራሪ ስታመጣባቸው፣

ከቤታቸው ጩኸት ይሰማ።

23አንተ ግን እግዚአብሔር ሆይ፤

ሊገድሉኝ ያሤሩብኝን ሤራ ሁሉ ታውቃለህ፤

በደላቸውን ይቅር አትበል፤

ኀጢአታቸውንም ከፊትህ አትደምስስ፤

በፊትህ ወድቀው የተጣሉ ይሁኑ፤

በቍጣህም ጊዜ አትማራቸው።

Japanese Contemporary Bible

エレミヤ書 18:1-23

18

陶器師の家

1主からエレミヤに、次のようなことばがありました。 2「さあ、陶器を作っている者の家に行きなさい。そこで、おまえに話そう。」 3言われたとおりにすると、陶器師はろくろを回している最中でした。 4ところが、彼は手がけていたつぼが気に入らなかったので、それをつぶして粘土のかたまりに戻し、初めからやり直しました。

5その時、主が語りました。

6「イスラエルよ。この陶器師と同じことを、わたしがおまえたちにできないというのか。陶器師の手の中に粘土があるように、おまえたちもわたしの手の中にある。 7わたしが、一つの国が引き抜かれて滅ぼされると言ったとき、 8その国が悪の道を捨てるなら、わたしは予定を変更して、その国を滅ぼすのをやめる。 9また、わたしが、ある国を強くすると言ったとしても、 10その国が途中で考えを変えて悪の道に走り、わたしに従わなくなれば、わたしも考えを変えて、祝福の約束を撤回する。 11だから出かけて行って、ユダとエルサレムの全住民に、こう警告しなさい。さあ、神のことばを聞きなさい。わたしは今おまえたちのために、良いことではなく悪いことを計画している。だから悪の道を捨て、正しいことを行うのだ。」 12ところが彼らは、こう答えました。「おせっかいはやめてくれ。神の言われたことを行う気など全くない。私たちはだれからも束縛されない。強情を張りとおし、悪を身につけたまま、いつまでも好き勝手な生活をしたい。」

13そのとき、主はこう言いました。

「たとえ異教の民の間でも、

こんなことを聞いた者はいない。

考えただけでもおぞましいことを

わたしの民がしたのだ。

14レバノン山頂の雪は決してとけず、

ヘルモン山から流れ下る冷たい水は決してかれない。

15これらのものは、いつもあてにできる。

ところがわたしの民は、全くあてにならない。

彼らはわたしを置き去りにし、

むなしい偶像のもとに走った。

昔からの正しい道をはずれ、罪の泥沼に迷い込んだ。

16そのため、国は荒れ果て、

そこを通る人は思わず息をのみ、

あまりにもすさまじい光景に驚いて頭を振る。

17わたしはわたしの民を、

東風がちりを巻き上げるように、敵の前でまき散らす。

彼らがどんなに悩んでも、知らないふりをし、

彼らの苦しみを心に留めない。」

18すると、人々はこう相談しました。「エレミヤを殺してしまおう。われわれには、祭司や学者、それに預言者がついている。彼の忠告などいらない。二度とわれわれに不利なことを語り、われわれを苦しめないように、彼の口を封じよう。」

19ああ主よ、私を助けてください。

彼らが私にどんなことをしようとしているか、

見てください。

20彼らは、悪をもって善に報いようとするのですか。

彼らは私を殺そうと、罠をしかけました。

それでも私は神に、彼らのことを良く伝え、

何とかして、神の怒りが彼らに向かないように

努力しました。

21神よ、彼らの子どもを飢え死にさせてください。

彼らを剣にかけてください。

彼らの妻を未亡人とし、

子どもを一人残らず奪ってください。

男は疫病で死なせ、

若者は戦場で倒れさせてください。

22兵士の一隊が不意に襲うとき、

彼らの家から泣き叫ぶ声が聞こえますように。

彼らは落とし穴を掘り、

私の歩く道に、こっそり罠をしかけたからです。

23主よ。

あなたは、私を殺そうとする彼らの計画をご存じです。

彼らを赦さないでください。

彼らの罪を赦さず、御前で滅ぼしてください。

彼らに御怒りをもって罰してください。