ኢዮብ 5 – NASV & NAV

New Amharic Standard Version

ኢዮብ 5:1-27

1“እስቲ ተጣራ፤ የሚመልስልህ አለን?

ከቅዱሳንስ ወደ ማንኛው ዘወር ትላለህ?

2ሞኙን ሰው ብስጭት ይገድለዋል፤

ቂሉንም ቅናት ያጠፋዋል።

3ቂል ሰው ሥር ሰድዶ አየሁት፤

ግን ድንገት ቤቱ ተረገመ።

4ልጆቹ የኑሮ ዋስትና የራቃቸው፤

በፍርድ አደባባይ ጥቃት የደረሰባቸው፣ ታዳጊ የሌላቸው ናቸው።

5ከእሾኽ መካከል እንኳ አውጥቶ፣

ራብተኛ ሰብሉን ይበላበታል፤

ጥማተኛም ሀብቱን ይመኝበታል።

6ችግር ከምድር አይፈልቅም፤

መከራም ከመሬት አይበቅልም።

7ፍንጣሪው ከእሳቱ ላይ ሽቅብ እንደሚወረወር፣

ሰውም ለመከራ ይወለዳል።

8“እኔ ብሆን ኖሮ፣ ወደ እግዚአብሔር በቀረብሁ፣

ጕዳዬንም በፊቱ በገለጽሁለት ነበር።

9እርሱ፣ የማይመረመሩ ድንቅ ነገሮች፣

የማይቈጠሩም ታምራት ያደርጋል።

10ምድሪቱን በዝናብ ያረሰርሳል፤

ሜዳውንም ውሃ ያጠጣል።

11የተዋረዱትን በከፍታ ቦታ ያስቀምጣል፤

ያዘኑትንም ወደ አስተማማኝ ስፍራ ያወጣቸዋል።

12እጃቸው ያሰቡትን እንዳይፈጽም፣

የተንኰለኞችን ዕቅድ ያከሽፋል።

13ጠቢባንን በጥበባቸው ይይዛል፤

የተንኰለኞችንም ሤራ ያጠፋል።

14ቀኑ ጨለማ ይሆንባቸዋል፤

በቀትርም ጊዜ በሌሊት እንዳለ ሰው በዳበሳ ይሄዳሉ።

15ችግረኛውን ከአፋቸው ሰይፍ፣

ከኀይለኛውም እጅ ያድነዋል።

16ስለዚህ ድኻ ተስፋ አለው፤

ዐመፅም አፏን ትዘጋለች።

17“እነሆ፤ እግዚአብሔር የሚገሥጸው ሰው ምስጉን ነው፤

ስለዚህ ሁሉን የሚችለውን5፥17 በዕብራይስጥ ሻዳይ ማለት ሲሆን፣ በዚህ ቍጥርና በኢዮብ መጽሐፍ ውስጥም እንዲሁ ነው። አምላክ ተግሣጽ አትናቅ።

18እርሱ ያቈስላል፤ ይፈውሳል፤

እርሱ ይሰብራል፤ በእጁም ይጠግናል፤

19እርሱ ከስድስት መቅሠፍት ይታደግሃል፤

በሰባተኛውም ጕዳት አያገኝህም።

20በራብ ጊዜ ከሞት፣

በጦርነትም ከሰይፍ ያድንሃል።

21ከምላስ ጅራፍ ትሰወራለህ፤

ጥፋት ሲመጣም አትፈራም።

22በጥፋትና በራብ ላይ ትሥቃለህ፤

የምድርንም አራዊት አትፈራም።

23ከሜዳ ድንጋዮች ጋር ትዋዋላለህና፤

የዱር አራዊትም ከአንተ ጋር ይስማማሉ።

24ድንኳንህ በሚያስተማምን ሁኔታ እንዳለ ታውቃለህ፤

በረትህን ትቃኛለህ፤ አንዳችም አይጐድልብህም።

25ዘሮችህ አያሌ እንደሚሆኑ፣

የምትወልዳቸውም እንደ ሣር እንደሚበዙ ታውቃለህ።

26የእህል ነዶ ጐምርቶ በወቅቱ እንደሚሰበሰብ፣

ዕድሜ ጠግበህ ወደ መቃብር ትሄዳለህ።

27“እነሆ፤ ይህን ሁሉ መርምረናል፤ እውነት ሆኖ አግኝተነዋል፤

ስለዚህ ልብ በል፤ ተቀበለውም።”

Ketab El Hayat

أيوب 5:1-27

1ادْعُ الآنَ، فَهَلْ مِنْ مُجِيبٍ؟ وَإِلَى أَيِّ القِدِّيسِينَ تَلْتَفِتُ؟ 2الْغَيْظُ يَقْتُلُ الأَحْمَقَ، وَالْغَيْرَةُ تُمِيتُ الأَبْلَهَ. 3لَقَدْ شَاهَدْتُ الْغَبِيَّ يَتَأَصَّلُ، ثُمَّ لَمْ أَلْبَثْ أَنْ لَعَنْتُ مَسْكَنَهُ. 4أَبْنَاؤُهُ لَا أَمْنَ لَهُمْ. يَتَحَطَّمُونَ عِنْدَ الْبَابِ وَلا مُنْقِذَ. 5يَأْكُلُ الْجَائِعُ حَصِيدَهُمْ، وَيَلْتَهِمُهُ حَتَّى مِنْ بَيْنِ الشَّوْكِ، وَيَمْتَصُّ الظَّامِئُ ثَرْوَتَهُمْ. 6إِنَّ الْبَلِيَّةَ لَا تَخْرُجُ مِنَ التُّرَابِ، وَالْمَشَقَّاتِ لَا تَنْبُتُ مِنَ الأَرْضِ، 7وَمَعَ ذَلِكَ فَإِنَّ الإِنْسَانَ مَوْلُودٌ لِمُعَانَاةِ الْمَتَاعِبِ، كَمَا وُلِدَتِ الْجَوَارِحُ لِتُحَلِّقَ بِأَجْنِحَتِهَا.

8لَوْ كُنْتُ فِي مَكَانِكَ لاتَّجَهْتُ إِلَى اللهِ وَعَرَضْتُ أَمْرِي عَلَيْهِ. 9هُوَ صَانِعُ عَجَائِبَ لَا تُفْحَصُ وَعَظَائِمَ لَا تُحْصَى. 10يُهْطِلُ الْغَيْثَ عَلَى وَجْهِ الأَرْضِ، وَيُرْسِلُ الْمِيَاهَ إِلَى الْحُقُولِ. 11يُقِيمُ الْمُتَوَاضِعِينَ فِي الْعُلَى، وَيَرْفَعُ النَّائِحِينَ إِلَى مَكَانِ الطُّمَأْنِينَةِ. 12يُبْطِلُ تَدْبِيرَاتِ الْمُحْتَالِينَ فَيُخْفِقُونَ، 13أَوْ يُوْقِعُ الْحُكَمَاءَ فِي خِدْعَتِهِمْ، فَتَتَلاشَى مَشُورَةُ الْمَاكِرِينَ. 14يَكْتَنِفُهُمْ ظَلامٌ فِي النَّهَارِ، وَيَتَحَسَّسُونَ طَرِيقَهُمْ فِي الظَّهِيرَةِ، كَمَنْ يَمْشِي فِي اللَّيْلِ. 15يُنَجِّي الْبَائِسِينَ مِنْ سَيْفِ فَمِهِمْ، وَمِنْ قَبْضَةِ الْقَوِيِّ يُنْقِذُهُمْ، 16فَيُصْبِحُ لِلْمِسْكِينِ رَجَاءٌ، وَالظُّلْمُ يَسُدُّ فَمَهُ.

17طُوبَى لِلرَّجُلِ الَّذِي يُقَوِّمُهُ اللهُ، فَلا تَرْفُضْ تَأْدِيبَ الْقَدِيرِ. 18لأَنَّ اللهَ يَجْرَحُ وَيَعْصِبُ، يَسْحَقُ وَيَدَاهُ تُبْرِئَانِ. 19مِنْ سِتِّ بَلايَا يُنَجِّيكَ، وَفِي سَبْعٍ لَا يَقَعُ بِكَ أَذىً. 20يَفْدِيكَ مِنَ الْمَوْتِ جُوعاً، وَفِي الْحَرْبِ مِنَ الْمَوْتِ بِحَدِّ السَّيْفِ. 21يَقِيكَ مِنْ لَذَعَاتِ اللِّسَانِ، فَلا تَخَافُ مِنَ الدَّمَارِ إِذَا أَقْبَلَ. 22تَسْخَرُ مِنَ الدَّمَارِ وَالْمَجَاعَةِ، وَلا تَخْشَى وُحُوشَ الأَرْضِ، 23لأَنَّ عَهْدَكَ مَعَ حِجَارَةِ الْحَقْلِ، وَوُحُوشُ الصَّحْرَاءِ تُسَالِمُكَ. 24فَتُدْرِكُ أَنَّ خَيْمَتَكَ آمِنَةٌ، وَتَتَعَهَّدُ حَظِيرَتَكَ فَلا تَفْقِدُ شَيْئاً. 25عِنْدَئِذٍ تَعْلَمُ أَنَّ ذُرِّيَّتَكَ كَثِيرَةٌ، وَأَنَّ نَسْلَكَ كَعُشْبِ الأَرْضِ، 26وَتَدْخُلُ الْقَبْرَ فِي شَيْبَةٍ نَاضِجَةٍ، كَمَا يُرْفَعُ كُدْسُ الْقَمْحِ فِي مَوْسِمِهِ. 27فَانْظُرْ. هَذَا مَا بَحَثْنَا عَنْهُ، وَهُوَ حَقٌّ، فَاسْمَعْهُ وَاخْتَبِرْهُ بِنَفْسِكَ».