ኢዮብ 41 – NASV & BPH

New Amharic Standard Version

ኢዮብ 41:1-34

1“ሌዋታንን41፥1 ምናልባት ዐዞ ሊሆን ይችላል። በመንጠቆ ልታወጣው፣

ወይም ምላሱን በገመድ ልታስረው ትችላለህን?

2መሰነጊያ በአፍንጫው ልታስገባ፣

ወይም ጕንጩን በሜንጦ ልትበሳ ትችላለህን?

3እርሱ እንድትምረው ይለማመጥሃል?

በለስላሳ ቃላትስ ይናገርሃል?

4ለዘላለም ባሪያ ታደርገው ዘንድ፣

ከአንተ ጋር ይዋዋላልን?

5እንደ ወፍ አልምደኸው ከእርሱ ጋር ልትጫወት ትችላለህ?

ወይስ ለሴት አገልጋዮችህ መጫወቻነት ታስረዋለህን?

6ነጋዴዎችስ በእርሱ ላይ ይከራከራሉን?

ለቸርቻሪዎችስ ያከፋፍሉታል?

7ቈዳው ላይ ዐንካሴ ልትሰካ፣

ጭንቅላቱንም በዓሣ መውጊያ ጦር ልትበሳ ትችላለህን?

8እርሱን እስቲ ንካው፣

ግብግቡን ታስታውሳለህ፤ ከቶም አያላምድህም።

9እርሱን በቍጥጥር ሥር አውላለሁ ማለት ዘበት ነው፤

በዐይን ማየት እንኳ ብርክ ያስይዛል።

10ሊቀሰቅሰው የሚደፍር የለም፤

ማን ፊቱ ሊቆም ይችላል?

11ነክቶት በሰላም የሚሄድ ማን ነው?

ከሰማይ በታች ማንም የለም።41፥11 አንዳንድ ትርጕሞች፣ በዕዳ የሚጠይቀኝ ማን ነው? ከሰማይ በታች ያለው ሁሉ ንብረቴ ነው ይላሉ።

12“ስለ ብርታቱና ስለ አካላቱ ውበት፣

ስለ እጅና እግሩ ከመናገር አልቈጠብም።

13የደረበውን ልብስ ማን ሊያወልቅ ይችላል?

ማንስ ሊለጕመው ወደ መንጋጋው ይቀርባል?

14አስፈሪ ጥርሶቹ የተገጠገጡበትን፣

የአፉን ደጅ ማን ደፍሮ ይከፍታል?

15ጀርባው፣ አንድ ላይ የተጣበቁ፣

የጋሻ ረድፎች አሉት፤

16እጅግ የተቀራረቡ ስለሆኑ፣

ነፋስ በመካከላቸው አያልፍም፤

17እርስ በርስ የተገጣጠሙ ናቸው፤

አንዱ ከአንዱ ጋር ተጣብቋልና ማንም ሊለያያቸው አይችልም።

18እንጥሽታው የብርሃን ብልጭታ ያወጣል፤

ዐይኖቹም እንደ ማለዳ ጮራ ናቸው።

19ከአፉ ፍም ይወጣል፤

የእሳት ትንታግ ይረጫል።

20በሸንበቆ ማገዶ ላይ ከተጣደ ድስት እንደሚወጣ እንፋሎት፣

ከአፍንጫው ጢስ ይትጐለጐላል።

21እስትንፋሱ ከሰል ያቀጣጥላል፤

የእሳትም ነበልባል ከአፉ ይወጣል።

22ብርታት በዐንገቱ ውስጥ አለ፤

አሸባሪነትም በፊቱ እመር እመር ይላል።

23የሥጋው ንብርብር እርስ በርስ የተጣበቀ፣

በላዩ የጸናና ከቦታው የማይናጋ ነው።

24ደረቱ እንደ ዐለት የጠጠረ፣

እንደ ወፍጮ ድንጋይም የጠነከረ ነው።

25እርሱ በተነሣ ጊዜ፣ ኀያላን ይርዳሉ፤

በሚንቀሳቀስበትም ጊዜ ወደ ኋላ ያፈገፍጋሉ።

26ጦር፣ ፍላጻ ወይም ዐንካሴ፣

ሰይፍም ቢያገኘው አንዳች አይጐዳውም።

27እርሱ ብረትን እንደ አገዳ፣

ናስንም እንደ ነቀዘ ዕንጨት ይቈጥራል።

28ቀስት አያባርረውም፤

የወንጭፍ ድንጋይም ለእርሱ እንደ ገለባ ነው።

29ቈመጥ በእርሱ ፊት እንደ ገለባ ነው፤

ጦር ሲሰበቅ ይሥቃል።

30የሆዱ ሥር እንደ ሸካራ ገል ነው፤

እንደ መውቂያ መሣሪያም በጭቃ ላይ ምልክት ጥሎ ያልፋል።

31እንደሚፈላ ምንቸት ጥልቁን ያናውጠዋል፤

ባሕሩንም እንደ ሽቶ ብልቃጥ ያደርገዋል።

32ያለፈበትን መንገድ ብሩህ ያደርጋል፤

ቀላዩንም ሽበት ያወጣ ያስመስለዋል።

33ያለ ፍርሀት የተፈጠረ፣

እንደ እርሱ ያለ በምድር ላይ የለም።

34ከፍ ያሉትን ሁሉ በንቀት ይመለከታል፤

በትዕቢተኞችም ሁሉ ላይ ንጉሥ ነው።”

Bibelen på hverdagsdansk

Jobs Bog 41:1-26

1Det er håbløst at forsøge at fange den.

Synet af den er nok til, at modet forsvinder.

2Når ingen tør kæmpe mod dette mægtige dyr,

hvem tør da kæmpe imod mig?

3Hvem tør sige, at jeg skylder dem noget?

Alt i hele verden tilhører mig.

4Lad mig beskrive Livjatans krop.

Den er velformet med enorme lemmer og vældig styrke.

5Hvem kan flå huden af den

eller trænge ind under dens panser?

6Hvem kan åbne munden på den,

så man ser de frygtindgydende tænder?

7Ryggen er dækket af rækker af plader,

der beskytter den fuldstændigt som skjolde.

8Pladerne sidder så tæt,

at intet kan trænge ind imellem dem.

9De overlapper hinanden,

og det er umuligt at skille dem ad.

10Når den fnyser, er det som lysglimt,

øjnene gløder som en solopgang.

11Flammer står ud af munden på den,

et fyrværkeri af gnister.

12Damp kommer ud ad dens næsebor

som fra en kedel med kogende vand.

13Dens ånde får kul til at gløde,

fra gabet spruder den ild.

14Halsmusklerne er utroligt stærke,

den skaber rædsel overalt, hvor den kommer.

15Dens bug er hård og fast,

den kan modstå ethvert angreb.

16Dens hjerte er hårdt som sten,

urokkeligt som en møllesten.

17Går den til angreb, gyser de stærkeste helte,

de løber rædselsslagne deres vej.

18Det er nytteløst at kæmpe imod den med sværd,

hverken spyd, pil eller lanse kan bruges.

19Den bøjer jernstænger, som var det strå,

bronze splintrer den som råddent træ.

20Pile kan ikke jage den på flugt,

og sten preller af som ingenting.

21Stridskøller har ingen virkning,

og kastespyd ler den blot ad.

22Dens bug er dækket af skarpe skæl,

som sætter dybe spor i jorden.

23Flodvandet pisker den i kog,

det bobler som i en gryde.

24Kølvandet er som en glinsende sti,

en stribe af sølvhvidt skum.

25Der findes ingen skabning på jorden,

der er så frygtløs som den.

26Den har intet at være bange for,

den er det stolteste dyr på jorden.”