ኢዮብ 34 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ኢዮብ 34:1-37

1ኤሊሁ በመቀጠል እንዲህ አለ፤

2“እናንት ጠቢባን፣ ቃሌን ስሙ፤

ዐዋቂዎችም አድምጡኝ።

3ምላስ ምግብን አጣጥሞ እንደሚለይ፣

ጆሮም የንግግርን ለዛ ለይቶ ያውቃል።

4የሚበጀንን እንምረጥ፣

መልካሙንም አብረን እንወቅ።

5“ኢዮብ እንዲህ ይላል፤ ‘እኔ ንጹሕ ነኝ፤

እግዚአብሔር ግን ፍትሕ ነሣኝ፤

6እውነተኛ ብሆንም፣

እንደ ውሸታም ተቈጥሬአለሁ፤

በደል ባይኖርብኝም፣

በማይፈወስ ቍስል ተመትቻለሁ።’

7ፌዝን እንደ ውሃ የሚጠጣት፣

እንደ ኢዮብ ያለ ሰው ማን ነው?

8ከክፉ አድራጊዎች ጋር ይተባበራል፤

ከኀጢአተኞችም ጋር ግንባር ይፈጥራል።

9‘እግዚአብሔርን ለማስደሰት መሞከር፣

ለሰው አንዳች አይጠቅምም’ ብሏልና።

10“ስለዚህ፣ እናንተ አስተዋዮች ስሙኝ፤

ክፋትን ማድረግ ከእግዚአብሔር ዘንድ፣

በደልንም መፈጸም ሁሉን ከሚችል አምላክ ይራቅ።

11ለሰው እንደ ሥራው ይመልስለታል፤

እንደ አካሄዱም ይከፍለዋል።

12በእውነት እግዚአብሔር ክፋትን አይሠራም፤

ሁሉን የሚችል አምላክ ፍትሕን አያጣምምም።

13ምድርን እንዲገዛ የሾመው አለን?

የዓለምስ ሁሉ ባለቤት ያደረገው ማን ነው?

14እርሱ መንፈሱን መልሶ ቢወስድ፣

እስትንፋሱንም ወደ ራሱ ቢሰበስብ፣

15ሥጋ ለባሽ ሁሉ በአንድነት በጠፋ፣

ሰውም ወደ ዐፈር በተመለሰ ነበር።

16“ማስተዋል ካለህ ይህን ስማ፤

እኔ የምለውንም አድምጥ።

17ፍትሕን የሚጠላ ሊያስተዳድር ይችላልን?

አንተስ ጻድቁንና ኀያል የሆነውን ትኰንናለህ?

18ነገሥታትን ‘የማትረቡ ናችሁ፣’

መኳንንትንም፣ ‘ክፉዎች ናችሁ’

የሚላቸው እርሱ አይደለምን?

19ሁሉም የእጁ ሥራ ስለሆኑ፣

እርሱ ለገዦች አያደላም፤

ባለጠጋውንም ከድኻው አብልጦ አይመለከትም።

20እነርሱም እኩለ ሌሊት ላይ በድንገት ይሞታሉ፤

ሕዝብ ተንቀጥቅጦ ሕይወቱ ያልፋል፤

ኀያላኑም የሰው እጅ ሳይነካቸው ይወገዳሉ።

21“ዐይኖቹ የሰውን አካሄድ ይመለከታሉ፤

ርምጃውንም ሁሉ ይከታተላሉ።

22ክፉ አድራጊዎች የሚደበቁበት፣

ጨለማ ስፍራ ወይም የሞት ጥላ የለም።

23ሰው ለፍርድ ፊቱ ይቀርብ ዘንድ፣

እግዚአብሔር ቀጠሮ አይዝለትም።

24ያለ ምንም ጥያቄ ኀያላንን ያንኰታኵታል፤

ሌሎችንም በቦታቸው ይሾማል።

25እርሱ ሥራቸውን ሁሉ ስለሚያውቅ፣

በሌሊት ይገለብጣቸዋል፤

እነርሱም ይደቅቃሉ።

26ስለ ክፋታቸውም፣

በሰው ሁሉ ፊት ይቀጣቸዋል፤

27እርሱን ከመከተል ተመልሰዋልና፤

መንገዱንም ችላ ብለዋል።

28የድኾች ልቅሶ ወደ እርሱ እንዲደርስ ሰበብ ሆኑ፤

የመከረኞችን ጩኸት ሰማ።

29እርሱ ዝም ቢል፣ ማን ሊወቅሰው ይችላል?

ፊቱንስ ቢሰውር፣ ማን ሊያየው ይችላል?

እርሱ ከሰውም፣ ከሕዝብም በላይ ነው፤

30ይህም የሆነው ዐመፀኛው ሕዝቡን እንዳይገዛ፣

ወጥመድም በፊታቸው እንዳይዘረጋ ነው።

31“ሰው ለእግዚአብሔር እንዲህ ቢል የተሻለ ነበር፤

‘እኔ በደለኛ ነኝ፤ ከእንግዲህ ግን አልበድልም፤

32ማየት ያልቻልሁትን አስተምረኝ፤

ኀጢአት ሠርቼ እንደ ሆነም፣ ደግሜ አልሠራም።’

33ታዲያ አንተ ለመናዘዝ ፈቃደኛ ሳትሆን፤

እግዚአብሔር እንደ ወደድህ ይከፍልሃልን?

መወሰን ያለብህ አንተ ነህ እንጂ፣ እኔ አይደለሁም፤

እንግዲህ የምታውቀውን ንገረኝ።

34“አስተዋዮች ይናገራሉ፤

የሚሰሙኝም ጠቢባን እንዲህ ይሉኛል፤

35‘ኢዮብ ያለ ዕውቀት ይናገራል፤

ቃሉም ማስተዋል ይጐድለዋል።’

36ምነው ኢዮብ እስከ መጨረሻ በተፈተነ ኖሮ!

እንደ ክፉ ሰው መልሷልና፤

37በኀጢአቱም ላይ ዐመፅን ጨምሯል፤

በመካከላችን ሆኖ በንቀት አጨብጭቧል፤

በእግዚአብሔርም ላይ ብዙ ተናግሯል።”

Thai New Contemporary Bible

โยบ 34:1-37

1แล้วเอลีฮูกล่าวว่า

2“ฟังข้าพเจ้าเถิด ท่านผู้มีปัญญา

โปรดฟังข้าพเจ้า ท่านผู้รอบรู้

3เพราะหูลิ้มลองถ้อยคำ

เหมือนลิ้นลิ้มรสอาหาร

4ขอให้พวกเราแยกแยะเองว่าอะไรถูก

ขอให้พวกเราเรียนรู้ด้วยกันว่าสิ่งใดดี

5“โยบกล่าวว่า ‘ข้าไม่มีความผิด

แต่พระเจ้าไม่ให้ความยุติธรรมแก่ข้า

6แม้ข้าเองเป็นฝ่ายถูก

ก็ยังถูกหาว่าโกหก

แม้ข้าไม่ได้ทำผิด

ก็ยังถูกลงโทษเป็นแผลรักษาไม่หาย’

7มีใครบ้างที่เป็นเหมือนโยบ

ผู้ดื่มด่ำความเย้ยหยันเหมือนดื่มน้ำ?

8เขาเข้าเป็นพวกกับคนชั่ว

เขาคบค้ากับคนเลว

9เพราะเขาพูดว่า ‘มนุษย์ไม่ได้ประโยชน์อะไร

จากการพยายามทำให้พระเจ้าพอพระทัย’

10“ดังนั้นจงฟังข้าพเจ้าเถิด ท่านผู้มีความเข้าใจ

ไม่มีวันที่พระเจ้าจะทำชั่ว

หรือองค์ทรงฤทธิ์จะทำผิด

11พระองค์ทรงสนองแก่มนุษย์ตามสิ่งที่เขาได้ทำ

ทรงให้เขาได้รับสมกับความประพฤติของเขา

12เป็นไปไม่ได้ที่พระเจ้าจะทรงกระทำผิด

หรือองค์ทรงฤทธิ์จะบิดเบือนความยุติธรรม

13ใครหนอแต่งตั้งพระองค์ไว้เหนือโลก?

ใครหนอให้พระองค์ควบคุมดูแลโลกทั้งหมด?

14ถ้าหากพระองค์ตั้งพระทัย

จะถอนจิตวิญญาณ34:14 หรือพระวิญญาณและลมปราณของพระองค์ไปเสีย

15มวลมนุษยชาติก็จะพินาศสิ้น

มนุษย์จะกลับกลายเป็นฝุ่นธุลีดังเดิม

16“หากท่านมีความเข้าใจ

ขอจงฟังถ้อยคำของข้าพเจ้า

17ผู้ที่ชังความยุติธรรมจะปกครองได้หรือ?

ท่านจะกล่าวโทษองค์ผู้เที่ยงธรรมและทรงฤทธิ์หรือ?

18ไม่ใช่พระองค์หรือที่ตรัสกับกษัตริย์ว่า ‘พวกเจ้าไม่มีค่า’

และตรัสกับบรรดาเจ้านายว่า ‘พวกเจ้าชั่วช้า’?

19พระองค์ไม่ได้ลำเอียงเข้าข้างเจ้านาย

หรือเห็นแก่คนรวยมากกว่าคนจน

เพราะพวกเขาล้วนเป็นฝีพระหัตถ์ของพระองค์

20กลางดึกพวกเขาตายอย่างฉับพลัน

ผู้คนสั่นสะท้านแล้วตายจากไป

บรรดาผู้เกรียงไกรถูกคร่าไป ไม่ใช่ด้วยน้ำมือมนุษย์

21“พระเนตรของพระเจ้าเฝ้าดูวิถีทางของมนุษย์

ทรงเห็นทุกย่างก้าวของพวกเขา

22ไม่มีที่มืดและเงาทึบใดๆ

ที่คนชั่วจะซ่อนตัวได้

23พระเจ้าไม่จำเป็นต้องใช้เวลาสอบสวนมนุษย์อีก

พวกเขาจึงไม่ต้องมาต่อหน้าพระองค์เพื่อรับการตัดสิน

24พระองค์ทรงทำลายผู้เกรียงไกรลงโดยไม่ต้องไต่สวน

และทรงตั้งคนอื่นแทนพวกเขา

25เพราะทรงสังเกตเห็นการกระทำของพวกเขา

ทรงคว่ำพวกเขาลงในชั่วข้ามคืน และพวกเขาก็ถูกขยี้แหลกลาญ

26พระองค์ทรงลงโทษพวกเขาต่อหน้าทุกๆ คน

โทษฐานที่ทำความชั่ว

27เพราะพวกเขาหันเหจากการติดตามพระเจ้า

ไม่สนใจวิถีทางใดๆ ของพระองค์

28พวกเขาทำให้เสียงร่ำร้องของผู้ยากไร้มาถึงพระเจ้า

พระองค์จึงทรงได้ยินเสียงร้องของผู้ขัดสน

29แต่หากพระองค์ทรงนิ่งอยู่ ใครจะกล่าวโทษพระองค์ได้?

หากทรงซ่อนพระพักตร์ไว้ ใครเล่าจะเห็นพระองค์?

แต่พระองค์ทรงอยู่เหนือมนุษย์และเหนือประชาชาติด้วย

30เพื่อทรงป้องกันไม่ให้คนอธรรมขึ้นปกครอง

ไม่ให้เขาวางตาข่ายดักประชาชน

31“หากผู้หนึ่งทูลพระเจ้าว่า ‘ข้าพระองค์ผิดไปแล้ว

แต่จะไม่ทำผิดอีก

32ที่ยังไม่รู้ว่าผิดตรงไหน ก็ขอทรงชี้แนะสั่งสอน

หากข้าพระองค์ได้ทำผิดไป จะไม่ทำเช่นนั้นอีก’

33แล้วควรหรือที่พระเจ้าจะตอบสนองตามที่ท่านกำหนด

ในเมื่อท่านไม่ยอมกลับใจสำนึกผิด?

ท่านต้องเป็นฝ่ายตัดสินใจ ไม่ใช่ข้าพเจ้า

ฉะนั้นโปรดบอกสิ่งที่ท่านทราบแก่ข้าพเจ้า

34“บรรดาผู้ที่มีความเข้าใจ

คนมีปัญญาที่ได้ฟังข้าพเจ้า พูดกับข้าพเจ้าว่า

35‘โยบพูดโดยขาดความรู้

คำพูดของโยบขาดความเข้าใจที่ลึกซึ้ง’

36ขอให้โยบถูกทดสอบจนถึงที่สุดเถิด

เพราะเขาตอบเหมือนคนชั่วร้าย!

37นอกเหนือจากทำบาปแล้ว เขายังกบฏอีก

เขาตบมือเยาะเย้ยอยู่ในหมู่พวกเรา

และพรั่งพรูคำพูดต่อว่าพระเจ้า”