ኢዮብ 31 – NASV & NIVUK

New Amharic Standard Version

ኢዮብ 31:1-40

1“ወደ ኰረዳዪቱ ላለመመልከት፣

ከዐይኔ ጋር ቃል ኪዳን ገብቻለሁ።

2ከላይ ከእግዚአብሔር ዘንድ የሰው ዕድል ፈንታው፣

ከአርያም ሁሉን ከሚችል አምላክስ ዘንድ ቅርሱ ምንድን ነው?

3ለኀጢአተኞች ጥፋት፣

ክፉ ለሚያደርጉም መቅሠፍት አይደለምን?

4እርሱ መንገዴን አያይምን?

ርምጃዬንስ ሁሉ አይቈጥርምን?

5“በሐሰት ሄጄ እንደ ሆነ፣

እግሬም ወደ ሽንገላ ቸኵሎ ከሆነ፣

6እግዚአብሔር በእውነተኛ ሚዛን ይመዝነኝ፤

ነውር እንደሌለብኝም ይወቅ።

7አረማመዴ ከመንገድ ወጣ ብሎ፣

ልቤ ዐይኔን ተከትሎ፣

ወይም እጄ ረክሶ ከሆነ፣

8የዘራሁትን ሌላ ይብላው፤

ሰብሌም ተነቅሎ ይጥፋ።

9“ልቤ ሌላዋን ሴት ከጅሎ፣

በባልንጀራዬ ደጅ አድብቼ ከሆነ፣

10ሚስቴ የሌላ ሰው እህል ትፍጭ፤

ሌሎች ሰዎችም ይተኟት፤

11ይህ አሳፋሪ፣

ፍርድም የሚገባው ኀጢአት ነውና።

12ይህ የሚያቃጥልና የሚያጠፋ31፥12 ዕብራይስጡ አባዶን ይላል። እሳት ነው፤

ቡቃያዬንም ባወደመ ነበር።

13“ወንዶችና ሴቶች አገልጋዮቼ አቤቱታ ባቀረቡ ጊዜ፣

ፍርድ አዛብቼ ከሆነ፣

14እግዚአብሔር ሲነሣ ምን አደርጋለሁ?

ሲጠይቀኝስ ምን መልስ እሰጣለሁ?

15እኔን በማሕፀን ውስጥ የፈጠረኝ እነርሱን የፈጠረ አይደለምን?

በሆድ ውስጥ የሠራንስ እርሱ ራሱ አይደለምን?

16“ለድኻ የሚያስፈልገውን ከልክዬ ከሆነ፣

ወይም የመበለቲቱን ዐይን አፍዝዤ ከሆነ፣

17እንጀራዬን ከድኻ ዐደጉ ጋር ሳልካፈል፣

ለብቻዬ በልቼ ከሆነ፣

18ይልቁን ድኻ ዐደጉን ከታናሽነቴ ጀምሮ እንደ አባት አሳደግሁት፤

መበለቲቱንም ከተወለድሁ ጀምሮ መንገድ መራኋት፤

19በልብስ ዕጦት ሰው ሲጠፋ፣

ወይም ዕርቃኑን ያልሸፈነ ድኻ አይቼ፣

20በበጎቼ ጠጕር ስላሞቅሁት፣

ልቡ ባርኮኝ ካልሆነ፣

21በአደባባይ ተሰሚነት አለኝ ብዬ፣

በድኻ ዐደጉ ላይ እጄን አንሥቼ ከሆነ፣

22ትከሻዬ ከመጋጠሚያው ይነቀል፤

ክንዴም ከመታጠፊያው ይሰበር፤

23የእግዚአብሔርን ቍጣ በመፍራቴ፣

እንዲህ ያሉ ነገሮች መፈጸም አልቻልሁም።

24“ወርቅን ተስፋ አድርጌ፣

ወይም ንጹሑን ወርቅ፣ ‘አንተ መታመኛዬ ነህ’ ብዬ ከሆነ፣

25እጄ ባገኘችው ሀብት፣

በባለጠግነቴም ብዛት ደስ ብሎኝ ከሆነ፣

26የፀሓይን ድምቀት አይቼ፣

ወይም የጨረቃን አካሄድ ግርማ ተመልክቼ፣

27ልቤ በስውር ተታልሎ፣

ስለ ክብራቸው አፌ እጄን ስሞ ከሆነ፣

28ለልዑል እግዚአብሔር ታማኝ አለመሆኔ ነውና፣

ይህም ደግሞ የሚያስቀጣኝ በደል በሆነ ነበር።

29“በጠላቴ ውድቀት ደስ ብሎኝ፣

በደረሰበትም መከራ ሐሤት አድርጌ እንደ ሆነ፣

30እኔ ግን በነፍሱ ላይ ክፉ እንዲመጣ በመራገም፣

አንደበቴን ለኀጢአት ከቶ አሳልፌ አልሰጠሁም።

31የቤቴ ሰዎች፣ ‘ከኢዮብ ከብት ሥጋ አስቈርጦ፣

ያልጠገበ ማን ነው?’ ብለው ካልሆነ፣

32ነገር ግን ቤቴ ለመንገደኛው ዘወትር ክፍት ስለ ነበር፣

መጻተኛው በጐዳና ላይ አያድርም ነበር።

33ሰዎች31፥33 ወይም አዳም እንዳደረገው እንደሚያደርጉት በደሌን በልቤ በመሰወር፣

ኀጢአቴን ሸሽጌ ከሆነ፣

34ሕዝቡን በመፍራት፣

የወገኖቼንም ንቀት በመሸሽ፣

ወደ ደጅ ሳልወጣ፣ ዝም ብዬ ቤት ውስጥ አልተቀመጥሁም።

35“ምነው የሚሰማኝ ባገኝ!

የመከላከያ ፊርማዬ እነሆ፤ ሁሉን የሚችል አምላክ ይመልስልኝ፤

ከሳሼም ክሱን በጽሑፍ ያቅርብ።

36በርግጥ ትከሻዬ ላይ በደረብሁት፣

እንደ አክሊልም ራሴ ላይ በደፋሁት ነበር።

37እያንዳንዱን ርምጃዬን በገለጽሁለት፣

እንደ ልዑል እየተንጐራደድሁ በቀረብሁት ነበር።

38“ዕርሻዬ በእኔ ላይ ጮኻ ከሆነ፣

ትልሞቿ ሁሉ በእንባ ርሰው እንደ ሆነ፣

39ፍሬዋን ያለ ዋጋ በልቼ፣

የባለመሬቶቿን ነፍስ አሳዝኜ ከሆነ፣

40በስንዴ ፈንታ እሾኽ፣

በገብስም ምትክ ዐረም ይብቀልብኝ።”

የኢዮብ ቃል ተፈጸመ።

New International Version – UK

Job 31:1-40

1‘I made a covenant with my eyes

not to look lustfully at a young woman.

2For what is our lot from God above,

our heritage from the Almighty on high?

3Is it not ruin for the wicked,

disaster for those who do wrong?

4Does he not see my ways

and count my every step?

5‘If I have walked with falsehood

or my foot has hurried after deceit –

6let God weigh me in honest scales

and he will know that I am blameless –

7if my steps have turned from the path,

if my heart has been led by my eyes,

or if my hands have been defiled,

8then may others eat what I have sown,

and may my crops be uprooted.

9‘If my heart has been enticed by a woman,

or if I have lurked at my neighbour’s door,

10then may my wife grind another man’s grain,

and may other men sleep with her.

11For that would have been wicked,

a sin to be judged.

12It is a fire that burns to Destruction31:12 Hebrew Abaddon;

it would have uprooted my harvest.

13‘If I have denied justice to any of my servants,

whether male or female,

when they had a grievance against me,

14what will I do when God confronts me?

What will I answer when called to account?

15Did not he who made me in the womb make them?

Did not the same one form us both within our mothers?

16‘If I have denied the desires of the poor

or let the eyes of the widow grow weary,

17if I have kept my bread to myself,

not sharing it with the fatherless –

18but from my youth I reared them as a father would,

and from my birth I guided the widow –

19if I have seen anyone perishing for lack of clothing,

or the needy without garments,

20and their hearts did not bless me

for warming them with the fleece from my sheep,

21if I have raised my hand against the fatherless,

knowing that I had influence in court,

22then let my arm fall from the shoulder,

let it be broken off at the joint.

23For I dreaded destruction from God,

and for fear of his splendour I could not do such things.

24‘If I have put my trust in gold

or said to pure gold, “You are my security,”

25if I have rejoiced over my great wealth,

the fortune my hands had gained,

26if I have regarded the sun in its radiance

or the moon moving in splendour,

27so that my heart was secretly enticed

and my hand offered them a kiss of homage,

28then these also would be sins to be judged,

for I would have been unfaithful to God on high.

29‘If I have rejoiced at my enemy’s misfortune

or gloated over the trouble that came to him –

30I have not allowed my mouth to sin

by invoking a curse against their life –

31if those of my household have never said,

“Who has not been filled with Job’s meat?” –

32but no stranger had to spend the night in the street,

for my door was always open to the traveller –

33if I have concealed my sin as people do,31:33 Or as Adam did

by hiding my guilt in my heart

34because I so feared the crowd

and so dreaded the contempt of the clans

that I kept silent and would not go outside –

35(‘Oh, that I had someone to hear me!

I sign now my defence – let the Almighty answer me;

let my accuser put his indictment in writing.

36Surely I would wear it on my shoulder,

I would put it on like a crown.

37I would give him an account of my every step;

I would present it to him as to a ruler.) –

38‘if my land cries out against me

and all its furrows are wet with tears,

39if I have devoured its yield without payment

or broken the spirit of its tenants,

40then let briers come up instead of wheat

and stinkweed instead of barley.’

The words of Job are ended.