ኢዮብ 28 – NASV & KLB

New Amharic Standard Version

ኢዮብ 28:1-28

1“የብር ማዕድን የሚወጣበት፣

ወርቅም የሚነጠርበት ስፍራ አለ።

2ብረት ከመሬት ውስጥ ይገኛል፤

መዳብም ከማዕድን ድንጋይ ቀልጦ ይወጣል።

3ሰው፣ እስከ ጨለማ መጨረሻ ይዘልቃል፤

ከድቅድቅ ጨለማ የማዕድን ድንጋይ ለማግኘት፣

እስከ ውስጠኛው ዋሻ ገብቶ ይፈልጋል።

4የሰው እግር ረግጦት በማያውቅበት ስፍራ፣

ከሰዎች መኖሪያ ርቆ መውረጃ ጕድጓድ ይቈፍራል፤

ሰው በሌለበት ቦታ ይንጠላጠላል፤ ይወዛወዛል።

5ከላይዋ ምግብን የምታስገኝ ምድር፣

ከታች በእሳት እንደሚሆን ትለዋወጣለች።

6ሰንፔር28፥6 በዚህና በ16 ላይ፣ ላፒስ ላዙሊ ከዐለቷ ይወጣል፤

ከዐፈሯም የወርቅ አንኳር ይገኛል።

7ያን መንገድ ጭልፊት አያውቀውም፤

የአሞራም ዐይን አላየውም፣

8ኵሩ አራዊት አልረገጡትም፤

አንበሳም በዚያ አላለፈም።

9ሰው እጁን በቡላድ ድንጋይ ላይ ያነሣል፤

ተራሮችንም ከሥር ይገለብጣል።

10በድንጋይ ውስጥ መተላለፊያ ያበጃል፤

ዐይኖቹም የከበሩ ነገሮችን ሁሉ ያያሉ።

11የወንዞችን ምንጭ ይበረብራል፤28፥11 የሰብዓ ሊቃናት ትርጕምና ቩልጌት ከዚህ ጋር ይስማማል፤ ዕብራይስጡ ግን ይገድባል ይላል።

የተሰወረውንም ነገር ወደ ብርሃን ያወጣል።

12“ነገር ግን ጥበብ ከወዴት ትገኛለች?

ማስተዋልስ መኖሪያዋ የት ነው?

13ሰው ዋጋዋን አያውቅም፤

በሕያዋንም ምድር አትገኝም።

14ውቅያኖስ፣ ‘በእኔ ውስጥ የለችም’ ይላል፤

ባሕርም፣ ‘በእኔ ዘንድ አይደለችም’ ይላል።

15ንጹሕ ወርቅ ሊገዛት አይችልም፤

ዋጋዋም በብር አይመዘንም።

16በኦፊር ወርቅ፣

በከበረም መረግድና በሰንፔር አትገመትም።

17ወርቅም ብርሌም አይወዳደሯትም፤

በወርቅ ጌጥም አትለወጥም።

18ዛጐልና አልማዝ ከቍጥር አይገቡም፤

የጥበብ ዋጋ ከቀይ ዕንቍም ይበልጣል።

19የኢትዮጵያ ቶጳዝዮን ሊስተካከላት አይችልም፤

ዋጋዋም በንጹሕ ወርቅ አይተመንም።

20“ታዲያ፣ ጥበብ ከወዴት ትመጣለች?

ማስተዋልስ የት ትገኛለች?

21ከሕያዋን ፍጥረታት ዐይን ሁሉ ተሰውራለች፤

ከሰማይ ወፎችም ተሸሽጋለች።

22ጥፋትና28፥22 ዕብራይስጡ፣ አባዶን ይላል። ሞት፣

‘ወሬዋን ብቻ ሰማን’ ይላሉ።

23ወደ እርሷ የሚወስደውን መንገድ የሚረዳ፣

መኖሪያዋንም የሚያውቅ እግዚአብሔር ብቻ ነው፤

24እርሱ የምድርን ዳርቻ ይመለከታልና፤

ከሰማይ በታች ያለውንም ሁሉ ያያል።

25ለነፋስ ኀይልን በሰጠ ጊዜ፣

የውሆችን መጠን በለካ ጊዜ፣

26ለዝናብ ሥርዐትን፣

ለነጐድጓድም መንገድን ባበጀ ጊዜ፣

27በዚያን ጊዜ ጥበብን ተመለከታት፤ ገመገማትም፤

አጸናት፤ መረመራትም።

28ከዚያም ሰውን፣

‘እግዚአብሔርን መፍራት ጥበብ ነው፤

ከክፋትም መራቅ ማስተዋል ነው’ አለው።”

Korean Living Bible

욥기 28:1-28

1“은은 채굴하는 광산이 있고 금은 제련하는 제련소가 있으며

2철은 땅에서 파내고 구리는 광석을 녹여서 얻는다.

3사람들은 광맥을 찾기 위해 땅을 깊이 파고 아주 어두운 곳을 조사한다.

4그들은 사람이 사는 곳에서 멀리 떨어져 인적이 끊어진 곳에 갱도를 깊이 파고 갱 속에서 밧줄로 몸을 묶어 흔들거리면서 외롭게 일하고 있다.

5지면에서는 먹을 것이 나오지만 지하에서는 땅이 불로 뒤집힌다.

6광석에는 청옥도 있고 사금도 있다.

7그런 보화를 캐내는 길은 솔개도 모르고 매의 눈도 그것을 보지 못하며

8사자나 다른 사나운 짐승도 밟아 보지 못한다.

9사람들은 아주 단단한 바위를 쪼개고 산을 파서 그 뿌리까지 드러내며

10바위를 뚫어 굴을 내고 보석을 찾아내며

1128:11 또는 ‘시냇물을 막아’강의 자원을 찾아서 감추인 것을 드러낸다.

12“그러나 지혜는 어디서 찾을 수 있으며 깊은 깨달음은 어디서 얻을 수 있는가?

13이 세상에서는 참 지혜를 찾을 수 없으므로 사람들이 그 가치를 모른다.

14대양이 ‘그것은 내 속에 없다’ 고 말하며 바다도 ‘그것은 나에게 없다’ 고 말한다.

15그것은 금이나 은으로 살 수 없고

16청옥과 마노와 같은 값진 보석으로도 그 값을 치를 수가 없다.

17지혜는 황금이나 유리와 비교가 안 되고 순금으로 장식한 보석으로도 살 수 없으며

18산호나 수정이나 홍옥도 그 가치에 미치지 못하며

1928:19 원문에는 ‘구스’에티오피아의 황옥이나 순금도 지혜의 값을 따를 수 없다.

20그렇다면 그 지혜를 어디서 얻을 수 있는가?

21그것은 모든 생물의 눈에 숨겨져 있고 공중의 새도 그것을 보지 못하며

22멸망과 사망까지도 그것을 소문으로만 들었을 뿐이라고 말한다.

23“하나님만이 지혜가 있는 곳을 아신다.

24이것은 그가 땅 끝까지 살피시며 천하에 있는 모든 것을 보고 계시기 때문이다.

25하나님이 바람의 힘을 조절하시고 물의 분량을 측정하시며

26비의 법칙과 번개가 다니는 길을 정하셨을 때에

27지혜를 보시고 28:27 또는 ‘선포하시며 굳게 세우시며 궁구하셨고’그 가치를 시험하여 인정하셨다.

28그러고서 하나님은 모든 인류에게 이렇게 말씀하셨다. ‘나 여호와를 두려운 마음으로 섬기는 것이 참 지혜요 악에서 떠나는 것이 진정한 깨달음이다.’ ”