ኢዮብ 28 – NASV & JCB

New Amharic Standard Version

ኢዮብ 28:1-28

1“የብር ማዕድን የሚወጣበት፣

ወርቅም የሚነጠርበት ስፍራ አለ።

2ብረት ከመሬት ውስጥ ይገኛል፤

መዳብም ከማዕድን ድንጋይ ቀልጦ ይወጣል።

3ሰው፣ እስከ ጨለማ መጨረሻ ይዘልቃል፤

ከድቅድቅ ጨለማ የማዕድን ድንጋይ ለማግኘት፣

እስከ ውስጠኛው ዋሻ ገብቶ ይፈልጋል።

4የሰው እግር ረግጦት በማያውቅበት ስፍራ፣

ከሰዎች መኖሪያ ርቆ መውረጃ ጕድጓድ ይቈፍራል፤

ሰው በሌለበት ቦታ ይንጠላጠላል፤ ይወዛወዛል።

5ከላይዋ ምግብን የምታስገኝ ምድር፣

ከታች በእሳት እንደሚሆን ትለዋወጣለች።

6ሰንፔር28፥6 በዚህና በ16 ላይ፣ ላፒስ ላዙሊ ከዐለቷ ይወጣል፤

ከዐፈሯም የወርቅ አንኳር ይገኛል።

7ያን መንገድ ጭልፊት አያውቀውም፤

የአሞራም ዐይን አላየውም፣

8ኵሩ አራዊት አልረገጡትም፤

አንበሳም በዚያ አላለፈም።

9ሰው እጁን በቡላድ ድንጋይ ላይ ያነሣል፤

ተራሮችንም ከሥር ይገለብጣል።

10በድንጋይ ውስጥ መተላለፊያ ያበጃል፤

ዐይኖቹም የከበሩ ነገሮችን ሁሉ ያያሉ።

11የወንዞችን ምንጭ ይበረብራል፤28፥11 የሰብዓ ሊቃናት ትርጕምና ቩልጌት ከዚህ ጋር ይስማማል፤ ዕብራይስጡ ግን ይገድባል ይላል።

የተሰወረውንም ነገር ወደ ብርሃን ያወጣል።

12“ነገር ግን ጥበብ ከወዴት ትገኛለች?

ማስተዋልስ መኖሪያዋ የት ነው?

13ሰው ዋጋዋን አያውቅም፤

በሕያዋንም ምድር አትገኝም።

14ውቅያኖስ፣ ‘በእኔ ውስጥ የለችም’ ይላል፤

ባሕርም፣ ‘በእኔ ዘንድ አይደለችም’ ይላል።

15ንጹሕ ወርቅ ሊገዛት አይችልም፤

ዋጋዋም በብር አይመዘንም።

16በኦፊር ወርቅ፣

በከበረም መረግድና በሰንፔር አትገመትም።

17ወርቅም ብርሌም አይወዳደሯትም፤

በወርቅ ጌጥም አትለወጥም።

18ዛጐልና አልማዝ ከቍጥር አይገቡም፤

የጥበብ ዋጋ ከቀይ ዕንቍም ይበልጣል።

19የኢትዮጵያ ቶጳዝዮን ሊስተካከላት አይችልም፤

ዋጋዋም በንጹሕ ወርቅ አይተመንም።

20“ታዲያ፣ ጥበብ ከወዴት ትመጣለች?

ማስተዋልስ የት ትገኛለች?

21ከሕያዋን ፍጥረታት ዐይን ሁሉ ተሰውራለች፤

ከሰማይ ወፎችም ተሸሽጋለች።

22ጥፋትና28፥22 ዕብራይስጡ፣ አባዶን ይላል። ሞት፣

‘ወሬዋን ብቻ ሰማን’ ይላሉ።

23ወደ እርሷ የሚወስደውን መንገድ የሚረዳ፣

መኖሪያዋንም የሚያውቅ እግዚአብሔር ብቻ ነው፤

24እርሱ የምድርን ዳርቻ ይመለከታልና፤

ከሰማይ በታች ያለውንም ሁሉ ያያል።

25ለነፋስ ኀይልን በሰጠ ጊዜ፣

የውሆችን መጠን በለካ ጊዜ፣

26ለዝናብ ሥርዐትን፣

ለነጐድጓድም መንገድን ባበጀ ጊዜ፣

27በዚያን ጊዜ ጥበብን ተመለከታት፤ ገመገማትም፤

አጸናት፤ መረመራትም።

28ከዚያም ሰውን፣

‘እግዚአብሔርን መፍራት ጥበብ ነው፤

ከክፋትም መራቅ ማስተዋል ነው’ አለው።”

Japanese Contemporary Bible

ヨブ 記 28:1-28

28

1人は銀を掘り出し、金を精錬し、

2地から鉄をとり、石を溶かして銅をとる。

3-4暗闇に明かりをともして縦坑を掘り、

地底の神秘を探る。

体に縄をかけ、死の陰に覆われた暗い穴の中に

つるされて、揺れ動きながら降りて行く。

5人は地の表面から食物を得る方法を知っているが、

地の下では火が燃えている。

6人はサファイヤや砂金のありかを知っている。

7これらの宝は、猛禽も見たことがなく、

鷲の目に触れたこともない。

8鉱山のふところ深く眠っているからだ。

野獣もそれを踏んだことがなく、

ライオンもその上に爪を立てたことがない。

9人は堅い岩を割り、山々をふもとからくつがえす。

10岩山にトンネルを掘り、貴金属を露出させ、

11川をせき止め、砂を洗って金をとる。

12こんなにも巧みに宝石を見つける人間も、

どこで知恵と悟りを見つけたらよいか知らない。

13どのようにしてそれを手に入れるかわからない。

実際、それは地上には見いだされない。

14大洋は、『ここにはない』と言い、

海は、『ここにもない』と答える。

15それは金や銀で買い取ることはできないし、

16オフィルの金や高価なしまめのう、

それにサファイヤを山と積んでも、

譲ってはもらえない。

17知恵は、金や高価なガラス細工より

はるかに価値がある。

宝石をちりばめた純金の器も

知恵とは交換してもらえない。

18さんごや水晶を差し出しても、

知恵を得ることはできない。

知恵の値段はルビーよりもけたはずれに高い。

19エチオピヤのトパーズはもちろん、

最高品質の純金をもってしても、知恵は手に入らない。

20では、知恵はどこへ行けば手に入るのか。

どこで見つけることができるのか。

21それは全人類の目から隠されている。

空を飛ぶ、鋭い目をした鳥でさえ、

見つけることはできない。

22だが、滅びと死は、

『知恵のことなら少しは知っている』と言う。

23-24神はもちろん、それがどこにあるかご存じだ。

地上をくまなく探し、

天の下を余すところなく見つめているからだ。

25神は風を吹かせ、海の境を決める。

26雨の法則を作り、いなびかりの通り道を決める。

27神は知恵のありかを知っていて、

耳を傾ける者にそれを聞かせる。

吟味に吟味を重ね、知恵を確かなものとする。

28神は全人類に言う。

『主を恐れることがほんとうの知恵、

悪を捨てることがほんとうの悟りだ。』」