ኢዮብ 14 – NASV & CCB

New Amharic Standard Version

ኢዮብ 14:1-22

1“ከሴት የተወለደ ሰው፣

ዘመኑ ዐጭርና በመከራ የተሞላ ነው፤

2እንደ አበባ ይፈካል፤ ይረግፋልም፤

እንደ ጥላ ይፈጥናል፤ አይጸናምም።

3እንደዚህ ባለ ሰው ላይ ዐይንህን ታሳርፋለህን?

ለፍርድስ በፊትህ ታቀርበዋለህን?14፥3 ሰብዓ ሊቃናት፣ ቩልጌትና ሱርስት እንዲሁ ሲሆን ዕብራይስጡ ግን ታቀርበኛለህን? ይላል

4ከርኩስ ነገር ውስጥ ንጹሕን ማን ሊያወጣ ይችላል?

አንድ እንኳ የሚችል የለም!

5የሰው ዕድሜ አስቀድሞ የተወሰነ ነው፤

የወራቱንም ብዛት ወስነህ አስቀምጠሃል፤

ሊያልፈው የማይችለውንም ገደብ አኖርህለት።

6እንግዲህ ዘመኑን እንደ ምንደኛ እስኪፈጽም ድረስ፣

ፊትህን ከእርሱ መልስ፤ ተወው።

7“ዛፍ እንኳ ቢቈረጥ፣

እንደ ገና ሊያቈጠቍጥ፣

አዳዲስ ቅርንጫፍም ሊያበቅል ተስፋ አለው።

8ሥሩ በምድር ውስጥ ቢያረጅ፣

ጕቶው በመሬት ውስጥ ቢበሰብስም፣

9የውሃ ሽታ ባገኘ ጊዜ ያቈጠቍጣል፤

እንደ ተተከለም ችግኝ ቅርንጫፍ ያወጣል።

10ሰው ግን ይሞታል፤ ክንዱንም ይንተራሳል፤

ነፍሱም ትወጣለች፤ ከእንግዲህስ የት ይገኛል?

11ውሃ ከባሕር ውስጥ እንደሚያልቅ፣

የወንዝ ውሃም ጠፍቶ እንደሚደርቅ፣

12እንደዚሁም ሰው ይተኛል፤ ቀናም አይልም፤

ሰማይ እስከሚያልፍ ድረስ አይነቃም፤

ከእንቅልፉም አይነሣም።

13“ምነው መቃብር14፥13 በዕብራይስጥ ሲኦል ማለት ነው። ውስጥ በሰወርኸኝ!

ቍጣህም እስከሚያልፍ በሸሸግኸኝ!

ምነው ቀጠሮ ሰጥተህ፣

ከዚያ በኋላ ባስታወስኸኝ!

14ሰው ከሞተ በኋላ ተመልሶ በሕይወት ይኖራል?

እድሳቴ14፥14 ወይም መፈታቴ እስከሚመጣ ድረስ፣

ተጋድሎ የሞላበትን ዘመኔን ሁሉ እታገሣለሁ።

15ትጠራኛለህ፤ እኔም እመልስልሃለሁ፤

የእጅህንም ሥራ ትናፍቃለህ።

16በዚያን ጊዜ በርግጥ ርምጃዬን ትከታተላለህ፤

ነገር ግን ኀጢአቴን አትቈጣጠርም።

17መተላለፌ በከረጢት ይቋጠራል፤

ኀጢአቴንም ትሸፍናለህ።

18“ተራራ እንደሚሸረሸርና እንደሚወድቅ፣

ዐለትም ከስፍራው እንደሚወገድ፣

19ውሃ ድንጋይን እንደሚቦረቡር፣

ጐርፍም ዐፈርን ዐጥቦ እንደሚወስድ፣

አንተም የሰውን ተስፋ ታጠፋለህ።

20አንድ ጊዜ ፈጽመህ ትበረታለህ፤ እርሱም ያልፋል፤

ገጽታውን ትቀይራለህ፤ ትሸኘዋለህም።

21ልጆቹ ቢከበሩ አያውቅም፤

ቢዋረዱም አያይም።

22የገዛ አካሉ ሕመም ብቻ ይሰማዋል፤

ለራሱም ብቻ ያለቅሳል።”

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

约伯记 14:1-22

1“人为妇人所生,

一生短暂,充满患难。

2他如花盛开,转眼凋谢;

如影消逝,无法久留。

3你还察看这样的世人吗?

还要把我召来受审吗?

4谁能使污秽产生洁净呢?

没有人能。

5人的年日已被限定,

你掌管他的岁月,

设定他无法逾越的界限。

6求你转身,别去管他,

好让他如雇工度完他的日子。

7树木若被砍下,还有希望,

它仍可重新萌芽,

嫩枝生长不息。

8虽然树根在土里衰老,

树干在地里死去,

9但一有水气,

它就会像新栽的树一样发芽长枝。

10但人一死,就失去力量;

人一咽气,就不知去向。

11湖水会枯竭,

江河会干涸,

12人躺下便不再起来,

到诸天不复存在,

他仍不会醒来,

不会从长眠中被唤醒。

13但愿你把我藏在阴间,

把我藏起来直到你息怒,

定下眷顾我的日期。

14人若死了,还能复生吗?

我要在劳苦的岁月中等待,

直到我得释放的日子来临。

15那时你呼唤,我便回应,

你必惦念你亲手所造之物。

16那时你必鉴察我的脚步,

但不会追究我的罪恶。

17我的过犯会被封在袋中,

你会遮盖我的罪愆。

18“高山崩塌,

磐石挪移;

19流水磨损石头,

急流冲走泥土;

你也这样粉碎人的希望。

20你永远击败他,使他消逝;

你改变他的容颜,让他离世。

21他的后人得尊荣,他无从知晓;

他们遭贬抑,他也无法察觉。

22他只能感受自身的痛苦,

为自己哀哭。”