ኢዮብ 12 – NASV & NIVUK

New Amharic Standard Version

ኢዮብ 12:1-25

ኢዮብ

1ኢዮብ እንዲህ ሲል መለሰ፤

2“በርግጥ ሰው ማለት እናንተ ናችኋ!

ጥበብም ከእናንተ ጋር ትሞታለቻ!

3ነገር ግን እኔም እንደ እናንተ አእምሮ አለኝ፤

ከእናንተ አላንስም፤

እንዲህ ያለውን ነገር የማያውቅ ማን ነው?

4እግዚአብሔርን ጠርቼ የመለሰልኝ ሰው ብሆንም፣

ለባልንጀሮቼ መሣቂያ ሆኛለሁ፤

ጻድቅና ያለ ነቀፋ ሆኜ እያለሁ፣ መሣቂያ ሆኛለሁ።

5የደላቸው በመከራ ያፌዛሉ፤

እግሩ የተንሸራተተውንም ይገፈትራሉ።

6የቀማኞች ድንኳን አይታወክም፤

አምላካቸውን በእጃቸው ይዘው እየዞሩም፣12፥6 ወይም የእግዚአብሔር እጅ በምታመጣላቸው ነገር

እግዚአብሔርንም እያስቈጡ በሰላም ይኖራሉ።

7“እስቲ እንስሶችን ጠይቁ፤ ያስተምሯችኋል፤

የሰማይ ወፎችንም ጠይቁ፣ ይነግሯችኋል፤

8ለምድር ተናገሩ፤ ታስተምራችኋለች፤

የባሕርም ዓሣ ይነግራችኋል።

9የእግዚአብሔር እጅ ይህን እንዳደረገ፣

ከእነዚህ ሁሉ የማያውቅ ማን ነው?

10የፍጥረት ሁሉ ሕይወት፣

የሰውም ሁሉ መንፈስ በእጁ ናትና፤

11ምላስ የምግብን ጣዕም እንደሚለይ፣

ጆሮ ቃላትን አይለይምን?

12ጥበብ ያለው በአረጋውያን ዘንድ አይደለምን?

ማስተዋልስ ረዥም ዕድሜ ባላቸው ዘንድ አይገኝምን?

13“ጥበብና ኀይል የእግዚአብሔር ናቸው፤

ምክርና ማስተዋልም በእርሱ ዘንድ ይገኛሉ።

14እርሱ ያፈረሰውን መልሶ የሚገነባ የለም፣

እርሱ ያሰረውን የሚፈታ አይገኝም።

15እርሱ ውሃን ቢከለክል፣ ድርቅ ይሆናል፤

ቢለቅቀውም ውሃው ምድሪቱን ያጥለቀልቃል።

16ብርታትና ድል ማድረግ በእርሱ ዘንድ ይገኛል፤

አታላዩም ተታላዩም በእርሱ እጅ ናቸው።

17አማካሪዎችን ከጥበባቸው ያራቍታል፤

ፈራጆችንም ማስተዋል ይነሣል።

18ነገሥታትን ድግ ያስፈታል፤

ገመድም በወገባቸው ያስራል።12፥18 ወይም የነገሥታትን ድግ፤ ሠቅ ያስራል

19ካህናትን ከክህነታቸው ያዋርዳል፤

ለዘመናት የተደላደሉትንም ይገለብጣል።

20ዕውቅ መካሪዎችን ቋንቋ ያሳጣል፤

የሽማግሌዎችንም ማስተዋል ይወስዳል።

21የተከበሩትን ውርደት ያከናንባል፤

ብርቱዎችንም ትጥቅ ያስፈታል።

22የጨለማን ጥልቅ ነገሮች ይገልጣል፤

የሞትንም ጥላ ወደ ብርሃን ያወጣል።

23ሕዝቦችን ታላቅ ያደርጋል፤ መልሶም ያጠፋቸዋል፤

ሕዝቦችን ያበዛል፤ ያፈልሳቸዋልም።

24የዓለም መሪዎችን ማስተዋል ይነሣል፣

መንገድ በሌለበት በረሓም ያቅበዘብዛቸዋል፤

25ብርሃን በሌለበት ጨለማ በዳበሳ ይሄዳሉ፤

እንደ ሰካራምም ይንገዳገዳሉ።

New International Version – UK

Job 12:1-25

Job

1Then Job replied:

2‘Doubtless you are the only people who matter,

and wisdom will die with you!

3But I have a mind as well as you;

I am not inferior to you.

Who does not know all these things?

4‘I have become a laughing-stock to my friends,

though I called on God and he answered –

a mere laughing-stock, though righteous and blameless!

5Those who are at ease have contempt for misfortune

as the fate of those whose feet are slipping.

6The tents of marauders are undisturbed,

and those who provoke God are secure –

those whom God has in his hand.12:6 Or those whose god is in their own hand

7‘But ask the animals, and they will teach you,

or the birds in the sky, and they will tell you;

8or speak to the earth, and it will teach you,

or let the fish in the sea inform you.

9Which of all these does not know

that the hand of the Lord has done this?

10In his hand is the life of every creature

and the breath of all mankind.

11Does not the ear test words

as the tongue tastes food?

12Is not wisdom found among the aged?

Does not long life bring understanding?

13‘To God belong wisdom and power;

counsel and understanding are his.

14What he tears down cannot be rebuilt;

those he imprisons cannot be released.

15If he holds back the waters, there is drought;

if he lets them loose, they devastate the land.

16To him belong strength and insight;

both deceived and deceiver are his.

17He leads rulers away stripped

and makes fools of judges.

18He takes off the shackles put on by kings

and ties a loincloth12:18 Or shackles of kings / and ties a belt round their waist.

19He leads priests away stripped

and overthrows officials long established.

20He silences the lips of trusted advisors

and takes away the discernment of elders.

21He pours contempt on nobles

and disarms the mighty.

22He reveals the deep things of darkness

and brings utter darkness into the light.

23He makes nations great, and destroys them;

he enlarges nations, and disperses them.

24He deprives the leaders of the earth of their reason;

he makes them wander in a trackless waste.

25They grope in darkness with no light;

he makes them stagger like drunkards.