ኢያሱ 7 – NASV & PCB

New Amharic Standard Version

ኢያሱ 7:1-26

የአካን ኀጢአት

1እስራኤላውያን ግን ዕርም የሆነውን ነገር7፥1 በዚህም ሆነ በቍጥር 11፡12፡13 እና 15 ላይ የዕብራይስጡ ቃል አንድን ሰው ወይም ነገር ሙሉ በሙሉ በማጥፋት ለእግዚአብሔር መስጠት ማለት ነው። ለራሳቸው በመውሰድ በደሉ፤ ይህም ከይሁዳ ነገድ የሆነው አካን የከርሚ ልጅ፣ የዘንበሪ7፥1 1ዜና 2፥6 እና የሰብዓ ሊቃናት ትርጉም ይመ፤ በዚህም ሆነ በቍጥር 17 እና 18 ላይ ዕብራይስጡ “ዘብዴ” ይላል። ልጅ፣ የዛራ ልጅ ዕርም ከሆነው ነገር ስለ ወሰደ የእግዚአብሔር ቍጣ በእስራኤል ልጆች ላይ ነደደ።

2ኢያሱ ከቤቴል በስተ ምሥራቅ ካለችው ከቤት አዌን አጠገብ ወደምትገኘው ወደ ጋይ ከኢያሪኮ ሰዎችን ልኮ፣ “ወደዚያ ውጡ፤ አገሪቱንም ሰልሉ” አላቸው፤ ሰዎቹም ወጥተው ጋይን ሰለሉ።

3ወደ ኢያሱም ተመልሰው፣ “ጋይን ለመውጋት ሕዝቡ ሁሉ መሄድ አያስፈልገውም፤ በዚያ ያለው ሕዝብ ጥቂት ስለሆነ፣ ከተማዪቱን ለመውጋት ሁለት ወይም ሦስት ሺሕ ሰው ስለሚበቃ ሕዝቡ ሁሉ ወደዚያ በመሄድ አይድከም” አሉት። 4ስለዚህ ሦስት ሺሕ ያህል ሰው ወጣ፤ ከጋይም ሰዎች ፊት ሸሸ፤ 5የጋይም ሰዎች እስራኤላውያንንም ከከተማዪቱ ቅጥር በር ጀምሮ እስከ ሽባሪም7፥5 ወይም እስከ “ድንጋይ መፍለጫው” ተብሎ መተርጐም ይችላል። ድረስ በማባረር ቍልቍለቱ ላይ መቷቸው፤ ከእነርሱም ሠላሳ ስድስት ያህል ሰው ገደሉባቸው። ከዚህ የተነሣም የሕዝቡ ልብ ቀለጠ፤ እንደ ውሃም ፈሰሰ።

6በዚህ ጊዜ ኢያሱ ልብሱን ቀደደ፤ በእግዚአብሔርም ታቦት ፊት በግንባሩ ተደፋ፤ የእስራኤል ሽማግሌዎችም እንደዚሁ አደረጉ፤ በራሳቸውም ላይ ትቢያ ነሰነሱ። 7ኢያሱም እንዲህ አለ፤ “ወዮ! ልዑል እግዚአብሔር ሆይ፤ ዮርዳኖስን አሻግረህ ይህን ሕዝብ ወደዚህ ያመጣኸው ለአሞራውያን አሳልፈህ በመስጠት እንዲያጠፉን ነውን? ምነው ሳንሻገር እዚያው ማዶ በቀረን ኖሮ! 8ጌታ ሆይ፤ እስራኤል በጠላቱ ፊት ሲሸሽ እኔ ምን ልበል? 9ከነዓናውያንና ሌሎቹ የምድሪቱ ነዋሪዎች ሁሉ ይህን ሲሰሙ ይከቡናል፤ ስማችንንም ከምድር ገጽ ያጠፉታል፤ እንግዲህ ስለ ታላቁ ስምህ ስትል የምታደርገው ምንድን ነው?”

10እግዚአብሔር ኢያሱን እንዲህ አለው፤ “ተነሥ! ለምን በግንባርህ ተደፋህ? 11እስራኤል በድሏል፤ እንዲጠብቁ ያዘዝኋቸውን ቃል ኪዳኔን ጥሰዋል፤ ዕርም የሆነውን ነገር ወስደዋል፤ ሰርቀዋል፤ ዋሽተዋል፤ የወሰዱትንም ከራሳቸው ንብረት ጋር ደባልቀዋል። 12እንግዲህ እስራኤላውያን ጠላቶቻቸውን ለመቋቋም ያልቻሉት በዚህ ምክንያት ነው። ጀርባቸውን አዙረው የሸሹትም ለጥፋት በመዳረጋቸው ነው። ዕርም የሆነውን ነገር ከመካከላችሁ ካላጠፋችሁ፣ ከዚህ በኋላ ከእናንተ ጋር አልሆንም።

13“ተነሣ፤ ሕዝቡን ቀድስ፤ እንዲህም በላቸው፤ ‘እስራኤል ሆይ፤ እርም የሆነ ነገር በመካከላችሁ ስላለ፣ ይህን ካላስወገዳችሁ ጠላቶቻችሁን ለመቋቋም እንደማትችሉ የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር ተናግሯልና ለነገ ራሳችሁን ለማዘጋጀት ሰውነታችሁን ቀድሱ።

14“ ‘ማለዳ በየነገድ በየነገዳችሁ ሆናችሁ ቅረቡ፤ እግዚአብሔር የሚለየው ነገድ በየጐሣ በየጐሣው ሆኖ ከሕዝቡ መካከል ወደ ፊት ይወጣል፤ እንዲሁም እግዚአብሔር የሚለየው ጐሣ በየቤተ ሰቡ ሆኖ ወደ ፊት ይወጣል፤ እግዚአብሔር የሚለየው ቤተ ሰብ ደግሞ በግለ ሰብ በግለ ሰብ ሆኖ ወደ ፊት ይወጣል። 15ዕርሙ የተገኘበት ሰው፣ እርሱና ያለው ሁሉ በእሳት ይቃጠላል፤ የእግዚአብሔርን ቃል ኪዳን አፍርሷል፤ በእስራኤልም ዘንድ አሳፋሪ ተግባር ፈጽሟልና።’ ”

16በማግስቱም ጧት ኢያሱ ማልዶ ተነሣ፤ እስራኤልንም በየነገድ በየነገዳቸው ሆነው እንዲቀርቡ አደረገ፤ ከዚያም የይሁዳ ነገድ ተለየ። 17የይሁዳንም ጐሣዎች ወደ ፊት አቀረበ፤ ከእነዚህም የዛራን ጐሣ ለየ፤ እነዚህን ደግሞ በየቤተ ሰባቸው እንዲወጡ አደረገ፤ ከእነዚህም ዘንበሪ ተለየ። 18ኢያሱ የዘንበሪን ቤተ ሰብ አባላት አንድ በአንድ ወደ ፊት እንዲቀርቡ አደረገ፤ ከዚያም ከይሁዳ ነገድ የሆነውም የዛራ ልጅ፣ የዘንበሪ ልጅ፣ የከርሚ ልጅ አካን ለብቻው ተለየ።

19ኢያሱም አካንን፣ “ልጄ ሆይ፤ ለእስራኤል አምላክ ለእግዚአብሔር ክብርን ስጥ7፥19 እውነትን ለመናገር የሚደረግ መሐላ ነው።፤ ለእርሱም ተናዘዝ፤ ያደረግኸውን ሳትደብቅ ንገረኝ” አለው።

20አካንም መልሶ ኢያሱን እንዲህ አለው፤ “እውነት ነው! የእስራኤልን አምላክ እግዚአብሔርን በድያለሁ፤ ያደረግሁትም ይህ ነው፤ 21ከምርኮው ዕቃ መካከል ከሰናዖር7፥21 አንዳንድ ቅጆች “ባቢሎን” ይላሉ። የመጣ አንድ የሚያምር ካባ፣ ሁለት መቶ ሰቅል7፥21 2.3 ኪሎ ግራም ያህል ነው። ብርና7፥21 0.6 ኪሎ ግራም ያህል ነው። ክብደቱ አምሳ ሰቅል የሚሆን የወርቅ ቡችላ አይቼ ጐመጀሁ፤ ወሰድኋቸውም፤ ዕቃውም ብሩ ከታች ሆኖ፣ በድንኳኔ ውስጥ መሬት ተቀብሯል።”

22በዚህ ጊዜ ኢያሱ መልእክተኞች ላከ፤ እነርሱም ወደ ድንኳኑ ሮጡ፤ በዚያም ብሩ ከታች ሆኖ ዕቃው እንደ ተቀበረ አገኙ። 23ከድንኳኑም አውጥተው፣ ኢያሱና እስራኤላውያን ሁሉ ወዳሉበት አምጥተው በእግዚአብሔር ፊት አኖሩ።

24ኢያሱም ከመላው እስራኤል ጋር ሆኖ፣ የዛራን ልጅ አካንን፣ ብሩን፣ ካባውን፣ የወርቁን ቡችላ፣ ወንዶችና ሴቶች ልጆቹን፣ የከብቱን መንጋ፣ አህዮቹንና በጎቹን እንዲሁም ድንኳኑንና የእርሱ የሆነውን ሁሉ ወደ አኮር ሸለቆ አስወሰደ። 25ኢያሱም፣ “እንዲህ ያለውን መከራ ለምን አመጣብህን? እነሆ፤ ዛሬ በአንተም ላይ እግዚአብሔር መከራ ያመጣብሃል” አለው።

ከዚያም እስራኤል በሙሉ በድንጋይ ወገሩት፤ የቀሩትንም እንደዚሁ ከወገሩ በኋላ በእሳት አቃጠሏቸው። 26በአካንም ላይ እስከ ዛሬ ድረስ የሚታየውን ታላቅ የድንጋይ ቍልል ከመሩበት፤ ከዚያም እግዚአብሔር ከአስፈሪ ቍጣው ተመለሰ። ስለዚህ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ያ ስፍራ የአኮር7፥26 አኮር” ማለት ችግር ወይም መከራ ማለት ነው። ሸለቆ ተባለ።

Persian Contemporary Bible

يوشع 7:1-26

گناه عخان

1اما بنی‌اسرائيل مرتكب گناه شدند. گرچه خداوند دستور فرموده بود كه چيزی را از شهر به غنيمت نبرند، ولی آنها از اين دستور سرپيچی كردند. عخان (پسر كرمی، نوهٔ زبدی و نوادهٔ زارح از قبيلهٔ يهودا) از اموالی كه حرام شده بود برای خود به غنيمت گرفت و خداوند به خاطر اين عمل بر تمام قوم اسرائيل غضبناک شد.

2بزودی پس از تسخير شهر اريحا، يوشع چند نفر از مردان خود را به شهر عای كه در شرق بيت‌ئيل و نزديک بيت‌آون واقع شده بود فرستاد تا وضع آنجا را بررسی كنند. 3وقتی آنها مراجعت نمودند گفتند: «شهر كوچكی است و فقط كافی است دو يا سه هزار نفر از سربازان ما بروند و آن را تصرف كنند. بنابراين لزومی ندارد كه همهٔ لشكر اسرائيل به آنجا حمله كند.»

4پس يوشع حدود سه هزار سرباز برای تسخير شهر عای فرستاد، اما آنها شكست خوردند. 5مردان عای از دروازهٔ شهر تا بلنديهای اطراف، اسرائيلی‌ها را تعقيب نموده، حدود سی و شش نفر از آنان را در سراشيبی كشتند. لشكر اسرائيل از اين واقعه دچار وحشت شد و روحيهٔ خود را به کلی باخت. 6پس يوشع و بزرگان اسرائيل از شدت ناراحتی جامه‌های خود را پاره كردند، خاک بر سر خود ريختند و تا غروب در برابر صندوق عهد خداوند به خاک افتادند.

7يوشع چنين دعا كرد: «آه ای خداوند، چرا ما را به اين سوی رود اردن آوردی تا به دست اين اموری‌ها كشته شويم؟ ای كاش راضی شده بوديم كه همان طرف رودخانه بمانيم. 8آه، ای خداوند، اينک كه قوم اسرائيل از دشمن شكست خورده است من چه كنم؟ 9چون اگر كنعانی‌ها و ساير قومهای مجاور از اين واقعه باخبر شوند، ما را محاصره نموده، همهٔ ما را نابود می‌كنند. آيا اين عمل به عظمت نام تو لطمه نمی‌زند؟»

10خداوند در پاسخ يوشع فرمود: «بلند شو! چرا اينچنين به خاک افتاده‌ای؟ 11قوم اسرائيل از فرمان من سرپيچی كرده و مرتكب گناه شده‌اند. ايشان مخفيانه از چيزهای حرام شهر برداشته‌اند، ولی انكار نموده، آنها را در ميان اثاثيهٔ خود پنهان ساخته‌اند. 12اين عمل موجب شده است كه اسرائيلی‌ها مغلوب شوند. به همين علت است كه سربازان تو نمی‌توانند در مقابل دشمنان ايستادگی كنند، زيرا گرفتار لعنت شده‌اند. اگر آن غنيمت حرام را از بين نبريد، من ديگر با شما نخواهم بود.

13«حال برخيز و مراسم پاک كردن گناه قوم را بجا آور و به آنها بگو كه برای فردا آماده شوند، زيرا من كه خداوند، خدای اسرائيل هستم می‌گويم: ای اسرائيل، مال حرام در ميان شماست و تا آن را از خود دور نكنيد، نخواهيد توانست در برابر دشمنانتان بايستيد. 14به همهٔ قبايل بگو كه فردا صبح نزد من حاضر شوند تا من معلوم كنم كه آن شخص خطاكار، متعلق به كدام قبيله است. پس از آن، تمام خاندانهای آن قبيله جلو بيايند تا مشخص كنم كه آن شخص خطاكار، در ميان كدام خاندان است. سپس تمام خانواده‌های آن خاندان حاضر شوند تا نشان دهم كه آن شخص مقصر، عضو كدام خانواده است. بعد تمام اعضای مقصر آن خانواده پيش بيايند. 15آنگاه شخصی كه مال حرام را دزديده است، با خانواده‌اش و هر چه كه دارد سوخته و نابود شود، زيرا عهد مرا شكسته و اسرائيل را رسوا نموده است.»

16پس يوشع صبح زود برخاسته، قبيله‌های اسرائيل را در حضور خداوند حاضر ساخت و قبيلهٔ يهودا مقصر شناخته شد. 17آنگاه تمام خاندانهای قبيلهٔ يهودا جلو آمدند و خاندان زارح مقصر تشخيص داده شد. بعد خانواده‌های آن خاندان جلو آمدند و خانوادهٔ زبدی مقصر شناخته شد. 18مردان خانوادهٔ زبدی جلو آمدند و عخان نوهٔ زبدی مقصر شناخته شد.

19يوشع به عخان گفت: «فرزندم در حضور خداوند، خدای اسرائيل حقيقت را بگو و به گناه خود اعتراف كن. به من بگو چه كرده‌ای و چيزی را از ما مخفی نكن.»

20عخان در جواب يوشع گفت: «من به خداوند، خدای اسرائيل خيانت كرده‌ام و مرتكب گناه شده‌ام. 21در ميان غنايم، چشمم به يک ردای زيبای بابلی، دويست مثقال نقره و يک شمش طلا كه وزنش پنجاه مثقال بود، افتاد و من از روی طمع آنها را برداشتم و در ميان خيمه‌ام آنها را زير خاک پنهان كردم. اول نقره را زير خاک گذاشتم، بعد طلا و سپس ردا را.»

22يوشع چند نفر را به دنبال غنايم فرستاد و آنها بشتاب به خيمه رفتند و چنانكه عخان گفته بود، ردا و طلا و نقره را پيدا كردند و نقره در قسمت زيرين قرار داشت. 23اشیا دزديده شده را نزد يوشع و تمام قوم اسرائيل آوردند و در حضور خداوند بر زمين گذاشتند. 24آنگاه يوشع و همهٔ اسرائیلی‌ها، عخان را گرفته، او را با ردا و نقره و شمش طلايی كه دزديده بود، با پسران و دخترانش و گاوها و گوسفندها و الاغهايش و خيمه‌اش و هر چه كه داشت به دره عخور بردند.

25در آنجا يوشع به عخان گفت: «چرا چنين بلايی بر سر ما آوردی؟ اكنون خداوند، تو را دچار بلا می‌كند.» آنگاه تمام بنی‌اسرائيل آنها را سنگسار نمودند و بعد بدنهايشان را سوزاندند 26و روی جنازهٔ سوختهٔ عخان، تودهٔ بزرگی از سنگ بر پا كردند. آن تودهٔ سنگ هنوز باقيست و آن مكان تا به امروز به «درهٔ بلا» معروف است. بدين ترتيب خشم خداوند فرو نشست.