ኢያሱ 10 – NASV & PCB

New Amharic Standard Version

ኢያሱ 10:1-43

ፀሓይ ቆመች

1የኢየሩሳሌም ንጉሥ አዶኒጼዴቅ፣ ኢያሱ ጋይን ይዞ እንደ ደመሰሳት10፥1 የዕብራይስጡ ቃል በዚህም ሆነ በቍጥር 28፡35፡37፡39 እና 40 ላይ ሙሉ በሙሉ በማጥፋት ለእግዚአብሔር መስጠት ማለት ነው።፣ እንደዚሁም በኢያሪኮና በንጉሥዋ ላይ ያደረገውን ሁሉ፣ በጋይና በንጉሥዋ ላይ ማድረጉን፣ የገባዖን ሰዎችም ከእስራኤል ጋር የሰላም ውል አድርገው በአጠገባቸው መኖራቸውን ሰማ። 2በዚህም እርሱና ሕዝቡ ደነገጡ፤ ምክንያቱም ገባዖን እንደ ነገሥታቱ ከተማ ሁሉ ታላቅ ከተማ፣ በስፋቷም ከጋይ የምትበልጥ፣ ሰዎቿም ብርቱ ተዋጊዎች ነበሩ። 3ስለዚህ የኢየሩሳሌም ንጉሥ አዶኒጼዴቅ፣ ሆሃም ወደ ተባለው የኬብሮን ንጉሥ ጲርአም ወደተባለው የየርሙት ንጉሥ፣ ያፊዓ ወደ ተባለው የለኪሶ ንጉሥና ዳቤር ወደተባለው የዔግሎን ንጉሥ በመላክ፣ 4“ወደዚህ ወጥታችሁ አግዙኝ፤ ከኢያሱና ከእስራኤላውያን ጋር ሰላምን መሥርታለችና ገባዖንን እንምታ” አላቸው።

5ከዚያም አምስቱ የአሞራውያን ነገሥታት ማለት የኢየሩሳሌም ንጉሥ፣ የኬብሮን ንጉሥ፣ የያርሙት ንጉሥ፣ የለኪሶ ንጉሥና የዔግሎን ንጉሥ ያላቸውን አስተባብረው፣ ሰራዊታቸውንም ሁሉ ይዘው በመውጣት ገባዖንን ወጓት።

6የገባዖንም ሰዎች በጌልገላ ወደ ሰፈረው ወደ ኢያሱ፣ “በተራራማው አገር የሚኖሩ የአሞራውያን ነገሥታት ኀይላቸውን አስተባብረው ተሰልፈውብናል፤ እኛን ባሮችህን አትተወን፤ ርዳን፤ ፈጥነህ በመድረስም አድነን” ሲሉ ላኩበት።

7ስለዚህ ኢያሱ ምርጥ የሆኑትን ተዋጊዎች ሁሉ ጨምሮ ሰራዊቱን በሙሉ ይዞ ከጌልገላ ወጣ። 8እግዚአብሔርም ኢያሱን፣ “አትፍራቸው፤ ሁሉንም አሳልፌ በእጅህ ሰጥቻቸዋለሁ፤ አንዳቸውም እንኳ ሊቋቋሙህ አይችሉም” አለው።

9ኢያሱ ከጌልገላ ሌሊቱን ሁሉ ሲገሠግሥ ዐድሮ ድንገት ወረራቸው። 10እግዚአብሔርም የአሞራውያንን ነገሥታት በእስራኤል ፊት አሸበራቸው፤ በገባዖን እጅግ መታቸው፤ ወደ ቤትሖሮን በሚያስወጣውም መንገድ ሽቅብ ተከተላቸው፤ እስከ ዓዜቅና እስከ መቄዳም ድረስ አሳድዶ መታቸው። 11ከቤትሖሮን ወደ ዓዜቃ ቍልቍል በሚወስደው መንገድ ላይ፣ ከእስራኤላውያን ፊት በሚሸሹበት ጊዜ፣ እግዚአብሔር ከሰማይ ትልልቅ የበረዶ ድንጋይ አወረደባቸው፤ በእስራኤላውያን ሰይፍ ካለቁት ይልቅ በወረደው የበረዶ ድንጋይ ያለቁት በልጠው ተገኙ።

12እግዚአብሔር አሞራውያንን ለእስራኤል አሳልፎ በሰጠባት ዕለት፣ ኢያሱ እግዚአብሔርን በእስራኤል ፊት እንዲህ አለው፤

“ፀሓይ ሆይ፤ በገባዖን ላይ ቁሚ፤

ጨረቃም ሆይ፤ በኤሎን ሸለቆ ላይ ቀጥ በዪ።”

13ስለዚህ ሕዝቡ ጠላቶቹን እስኪበቀል

ድረስ10፥13 ወይም ሕዝቡ እስኪያሸንፍ ድረስ፣ ፀሓይ ባለችበት ቆመች፤

ጨረቃም አልተንቀሳቀሰችም።

ይህም በያሻር መጽሐፍ ተጽፎ ይገኛል።

ፀሓይ በሰማዩ መካከል ቆመች፤ ለመጥለቅም ሙሉ ቀን ፈጀባት። 14እግዚአብሔር የሰውን ቃል የሰማበት እንደዚያ ያለ ዕለት ከዚያ በፊትም ሆነ ከዚያ በኋላ አልነበረም፤ እግዚአብሔር ለእስራኤል ተዋግቶ ነበርና።

15ከዚያም ኢያሱ ከመላው እስራኤል ጋር ጌልገላ ወዳለው ሰፈር ተመለሰ።

አምስቱ የአሞራውያን ነገሥታት ተገደሉ

16በዚህ ጊዜ አምስቱ የአሞራውያን ነገሥታት ሸሽተው በመቄዳ ዋሻ ተደብቀው ነበር። 17ኢያሱም አምስቱ ነገሥታት በመቄዳ ዋሻ ውስጥ ተደብቀው መገኘታቸውን ሰማ፤ 18እንዲህም አለ፤ “ትልልቅ ድንጋዮች ወደ ዋሻው አፍ አንከባሉ፤ ጠባቂ ሰዎችንም በዚያ አቁሙ፤ 19ጠላቶቻችሁን አሳድዷቸው እንጂ ችላ አትበሉ፤ ከበስተ ኋላ ሆናችሁም አደጋ ጣሉባቸው፤ ወደ ከተሞቻቸው እንዳይገቡ ከልክሏቸው፤ እነሆ፤ እግዚአብሔር አምላካችሁ በእጃችሁ አሳልፎ ሰጥቷቸዋልና።”

20ስለዚህ ኢያሱና እስራኤላውያን እስከ መጨረሻው ደመሰሷቸው፤ የተረፉት ጥቂቶቹ ግን ወደ ተመሸጉት ከተሞቻቸው ለመድረስ ቻሉ። 21ከዚያም ሰራዊቱ ሁሉ በደኅና ተመልሶ፣ ኢያሱ ወደ ሰፈረበት ወደ መቄዳ መጣ፤ በእስራኤላውያንም ላይ አንዲት ቃል የተናገረ ሰው አልነበረም።

22ኢያሱም፤ “ዋሻውን ከፍታችሁ እነዚያን አምስቱን ነገሥታት አውጥታችሁ አምጡልኝ” አላቸው። 23እነርሱም አምስቱን ነገሥታት ማለትም የኢየሩሳሌምን ንጉሥ፣ የኬብሮንን ንጉሥ፣ የያርሙትን ንጉሥ፣ የለኪሶን ንጉሥ የዔግሎንን ንጉሥ አውጥተው አመጡለት። 24እነዚህን ነገሥታት ባመጡለትም ጊዜ፣ ኢያሱ መላውን የእስራኤልን ወንዶች ከጠራ በኋላ አብረውት የመጡትን የጦር አዛዦች፣ “ወደዚህ ቅረቡና እግሮቻችሁን በእነዚህ ነገሥታት ዐንገት ላይ አድርጉ” አላቸው፤ እነርሱም ወደ ፊት ቀርበው እግራቸውን በነገሥታቱ ዐንገት ላይ አሳረፉ።

25ኢያሱም፣ “አትፍሩ፤ አትደንግጡ፤ በርቱ፤ ጽኑ፤ እንግዲህ በምትወጓቸው ጠላቶች ሁሉ ላይ እግዚአብሔር እንደዚሁ ያደርጋልና” አላቸው። 26ከዚያም ኢያሱ ነገሥታቱን መትቶ ገደላቸው፤ በአምስትም ዛፎች ላይ ሰቀላቸው፤ ሬሳቸውም እስኪመሽ ድረስ አልወረደም ነበር።

27ፀሓይ ለመጥለቅ በማዘቅዘቅ ላይ ሳለች ኢያሱ ትእዛዝ ሰጠ፤ ከዚያም የነገሥታቱን ሬሳ ከዛፎቹ ላይ አውርደው ቀድሞ ተደብቀው ወደ ነበሩበት ዋሻ ውስጥ ጣሏቸው። በዋሻውም አፍ ትልልቅ ድንጋዮች አኖሩ፤ ድንጋዮቹም እስከ ዛሬ ድረስ በዚያ ይገኛሉ።

28በዚያች ዕለት ኢያሱ መቄዳን ያዘ፤ ከተማዪቱንና ንጉሥዋንም በሰይፍ ስለት መታ፤ አንድም ሰው ሳያስቀር በውስጧ ያለውን ሁሉ ፈጽሞ ደመሰሰ፤ በኢያሪኮ ንጉሥ ላይ ያደረገውንም ሁሉ፣ በመቄዳ ንጉሥ ላይ አደረገ።

የደቡብ ከተሞች መያዝ

29ከዚያም ኢያሱና ከእርሱ ጋር የነበሩት እስራኤላውያን በሙሉ ከመቄዳ ወደ ልብና ዐለፉ፤ ወጓትም። 30እንዲሁም እግዚአብሔር ከተማዪቱንና ንጉሥዋን በእስራኤል እጅ አሳልፎ ሰጣቸው። ኢያሱ ከተማዪቱንና በውስጧ ያለውን ሁሉ በሰይፍ ስለት አጠፋ፤ አንድም ሰው አላስተረፈም። በኢያሪኮ ንጉሥ ላይ ያደረገውንም በልብና ንጉሥ ላይ ደገመው።

31ከዚያም ኢያሱና ከእርሱ ጋር የነበሩት እስራኤላውያን በሙሉ ከልብና ወደ ለኪሶ ዐለፉ፤ ወጓትም። 32እግዚአብሔር ለኪሶን አሳልፎ ለእስራኤል ሰጠ፤ ኢያሱም በሁለተኛው ቀን ያዛት፤ በልብና እንዳደረገው ሁሉ እዚህም ከተማዪቱንና በውስጧ ያሉትን ሁሉ በሰይፍ ስለት ፈጃቸው። 33በዚህ ጊዜ የጌዝር ንጉሥ ሆራም ለኪሶን ለመርዳት መጣ፤ ኢያሱ ግን አንድ እንኳ ሳያስተርፍ ንጉሡንና ሕዝቡን መታቸው።

34ከዚያም ኢያሱና ከእርሱ ጋር የነበሩት እስራኤላውያን በሙሉ ከለኪሶ ወደ ዔግሎን ዐለፉ፤ ወጓትም። 35በዚያኑ ዕለት ያዟት፤ በሰይፍም ስለት አጠፏት፤ በለኪሶ እንዳደረጉት ሁሉ እዚህም በውስጧ የሚገኙትን ፈጽመው ደመሰሷቸው።

36ከዚያም ኢያሱና ከእርሱ ጋር የነበሩት እስራኤላውያን በሙሉ ከዔግሎን ወደ ኬብሮን ወጡ፤ ወጓትም። 37ከተማዪቱንም ከንጉሧ፣ ከመንደሮቿና በውስጧ ካሉት ጋር ሁሉ አንድም ሰው ሳያስቀሩ በሰይፍ ስለት ፈጇቸው፤ በዔግሎን እንዳደረጉት ሁሉ እዚህም ከተማዪቱንና በውስጧ ያለውን ሁሉ ፈጽመው ደመሰሱ።

38ከዚያም ኢያሱና ከእርሱ ጋር የነበሩት እስራኤላውያን በሙሉ ወደ ኋላ ተመልሰው ዳቤርን ወጓት። 39ከተማዪቱን፣ ንጉሥዋንና መንደሮቿን ይዘው በሰይፍ ስለት ፈጇቸው፤ በውስጧ ያለውንም ሁሉ አንድም ሳያስቀሩ ደመሰሱ፤ በልብናና በንጉሥዋ እንዲሁም በኬብሮን ያደረጉትን ሁሉ እዚህም በዳቤርና በንጉሥዋ ላይ ደገሙት።

40በዚህ ሁኔታም ኢያሱ ተራራማውን አገር ኔጌቭን፣ የምዕራቡን ቈላና የተራራውን ሸንተረሮች ጨምሮ ምድሪቱን በሙሉ ከነገሥታቷ ጋር ያዘ። የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር ባዘዘውም መሠረት፣ እስትንፋስ ያላቸውን ሁሉ ፈጽሞ ደመሰሰ፤ ማንንም በሕይወት አላስቀረም። 41ኢያሱም ከቃዴስ በርኔ እስከ ጋዛ እንዲሁም የጎሶምን ምድር ሁሉ እስከ ገባዖን ድረስ በሙሉ ያዘ። 42ኢያሱ እነዚህን ሁሉ ነገሥታትና ምድራቸውን ያሸነፈው በአንድ ዘመቻ ብቻ ነበር፤ የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር ለእስራኤላውያን ተዋግቶላቸዋልና።

43ከዚህ በኋላ ኢያሱ ከመላው እስራኤላውያን ጋር ጌልገላ ወዳለው ሰፈር ተመለሰ።

Persian Contemporary Bible

يوشع 10:1-43

آفتاب از حركت باز می‌ايستد

1ادونی صَدَق، پادشاه اورشليم، شنيد كه يوشع شهر عای را گرفته و به کلی ويران كرده و پادشاهش را كشته است، همانگونه كه قبلاً اريحا را ويران كرده و پادشاهش را از بين برده بود. او همچنين شنيد كه ساكنان جبعون با اسرائيل صلح كرده و با آنها متحد شده‌اند. 2او و مردم اورشليم با شنيدن اين خبرها بسيار ترسيدند، زيرا جبعون مانند ديگر شهرهای پادشاه نشين، بزرگ بود حتی بزرگتر از عای و مردمانش جنگجويانی شجاع بودند. 3از اين رو ادونی صدق به فكر چاره افتاد و قاصدانی را نزد هوهام پادشاه حبرون، فرآم پادشاه يرموت، يافيع پادشاه لاخيش و دبير پادشاه عجلون فرستاد و اين پيغام را داد: 4«بياييد مرا كمک كنيد تا به جبعون حمله كنيم، زيرا ساكنانش با يوشع و قوم اسرائيل پيمان صلح بسته‌اند.»

5پس اين پنج پادشاه اموری با هم متحد شدند و لشكر خود را برای جنگ با جبعون بسيج نمودند.

6بزرگان جبعون با شتاب قاصدانی به جلجال نزد يوشع فرستادند و التماس كرده، گفتند: «بشتابيد و خدمتگزاران خود را كمک كنيد و از نابودی نجات دهيد؛ تمام پادشاهان اموری كه در كوهستان ساكنند لشكرهای خود را بر ضد ما بسيج كرده‌اند.»

7يوشع با تمام سربازان و جنگاوران شجاعش از جلجال به كمک مردم جبعون شتافت.

8خداوند به يوشع فرمود: «از ايشان نترس، زيرا من آنها را به دست تو تسليم كرده‌ام و كسی از ايشان يارای مقاومت در برابر تو را نخواهد داشت.»

9يوشع راه بين جلجال و جبعون را شبانه پيمود و لشكرهای دشمن را غافلگير كرد. 10خداوند دشمن را دچار وحشت نمود و اسرائيلی‌ها عده زيادی از آنها را در جبعون كشتند و بقيه را تا گردنهٔ بيت‌حورون تعقيب نموده، تا عزيقه و مقيده به كشتار خود ادامه دادند. 11وقتی دشمن به سرازيری بيت‌حورون رسيد، خداوند از آسمان بر سر آنها تگرگ درشت بارانيد كه تا به عزيقه ادامه داشت و عدهٔ زيادی از آنها را كشت. تعداد افرادی كه به‌وسیلهٔ تگرگ كشته شدند بيشتر از آنانی بود كه با شمشير اسرائيلی‌ها هلاک شدند!

12در حالی که سربازان اسرائيلی دشمن را تعقيب می‌كردند و آنها را عاجز ساخته بودند، يوشع نزد خدا دعا كرد و در حضور بنی‌اسرائيل گفت: «ای آفتاب بر بالای جبعون، و ای ماه بر فراز درهٔ اَيَلون از حركت باز بايستيد.»

13آفتاب و ماه از حركت باز ايستادند تا بنی‌اسرائيل دشمن را نابود كردند. اين واقعه در كتاب ياشر نيز نوشته شده است. پس آفتاب، تمام روز در وسط آسمان از حركت باز ايستاد! 14نظير چنين روزی كه خدا آفتاب و ماه را به خاطر دعای يک انسان متوقف ساخته باشد هرگز ديده نشده و ديده نخواهد شد. در واقع، اين خداوند بود كه برای بنی‌اسرائيل می‌جنگيد.

15پس از آن يوشع با تمام سربازانش به اردوگاه خود در جلجال بازگشتند.

شكست پادشاهان اموری

16اما در خلال جنگ، آن پنج پادشاه به مقيده گريختند و خود را در يک غار پنهان كردند. 17يوشع وقتی از مخفيگاه آنها باخبر شد، 18دستور داد: «دهانهٔ غار را با سنگهای بزرگ مسدود كنيد و چند نگهبان در آنجا بگذاريد تا مانع خروج آنها شوند؛ 19ولی شما از تعقيب دشمن دست برنداريد. به دنبال آنها برويد، از پشت سر به آنها حمله كنيد و نگذاريد دوباره به شهرهای خود بازگردند. خداوند، خدای شما آنها را به دست شما تسليم كرده است.»

20يوشع و لشكر اسرائيل آنقدر به كشتار ادامه دادند تا افراد پنج لشكر دشمن نابود شدند، و فقط عده كمی از آنان جان به در بردند و توانستند خود را به شهرهای حصاردار خود برسانند. 21سپس تمام لشكر اسرائيل به سلامت به اردوگاه خود در مقيده بازگشتند. از آن پس، هيچكس جرأت نكرد عليه قوم اسرائيل حتی سخنی بر زبان بياورد.

22بعد يوشع گفت: «سنگها را از دهانهٔ غار كنار بزنيد و آن پنج پادشاه را بيرون بياوريد.» 23پس آنها پادشاهان اورشليم، حبرون، يرموت، لاخيش و عجلون را بيرون آوردند. 24يوشع تمام مردان اسرائيل را فرا خواند و به سردارانی كه همراه او بودند دستور داد پاهای خود را بر گردن آن پنج پادشاه بگذارند، و آنها چنين كردند. 25سپس به مردان خود گفت: «از كسی نترسيد و جرأت خود را از دست ندهيد، بلكه قوی و شجاع باشيد، زيرا خداوند با تمام دشمنان شما بدين نحو رفتار خواهد كرد!»

26پس از آن، يوشع با شمشير خود آن پنج پادشاه را كشت و آنها را بر پنج دار آويخت. پيكرهای بی‌جان آنها تا غروب بردار ماندند.

27بعد از غروب آفتاب، مطابق دستور يوشع جنازه‌های آنها را از بالای دار پايين آورده، در درون همان غاری كه پنهان شده بودند، انداختند. سپس سنگهای بزرگ بر دهانهٔ آن غار گذاشتند كه تا امروز همچنان باقيست.

تصرف شهرهای جنوبی اموری‌ها

28در همان روز يوشع به شهر مقيده حمله كرده، آن را گرفت و پادشاه و تمام اهالی آنجا را كشت به طوری كه هيچكدام از ساكنان آنجا نتوانستند جان به در ببرند. 29بعد از آن، يوشع و افرادش به لبنه حمله كردند، 30و خداوند آنجا را نيز با پادشاهش به دست ايشان تسليم نمود، و آنها تمام ساكنان آن را مانند اهالی شهر اريحا از دم شمشير گذراندند.

31بعد از آن، به شهر لاخيش حمله بردند. 32در روز دوم، خداوند آن شهر را به دست ايشان تسليم نمود. آنها تمام اهالی شهر را مثل اهالی لبنه از دم شمشير گذراندند.

33هنگامی كه اسرائيلی‌ها به لاخيش حمله كردند، هورام پادشاه جازر با لشكر خود سر رسيد تا به مردمان شهر لاخيش كمک نمايد. اما يوشع، او و تمام افرادش را شكست داد و كسی از آنها را زنده نگذاشت.

34‏-35يوشع و افرادش در همان روز به شهر عجلون نيز حمله بردند و تمام ساكنان آنجا را مانند اهالی لاخيش هلاک نمودند. 36‏-37بعد از عجلون به شهر حبرون حمله كردند و آن را با تمام آبادی‌های اطرافش گرفتند و پادشاه و همهٔ ساكنانش را كشتند، به طوری كه يک نفر هم زنده باقی نماند. 38‏-39سپس از آنجا به شهر دبير بازگشتند و آن را با تمام دهكده‌های اطرافش گرفتند و پادشاه و همهٔ مردمش را مانند اهالی لبنه قتل عام نمودند.

40به اين ترتيب، يوشع تمام آن سرزمين را به تصرف درآورد و قبايل و پادشاهانی را كه در كوهستانها، كوهپايه‌ها، دشتها و نگب زندگی می‌كردند از بين برد. قوم اسرائيل چنانكه خداوند دستور داده بود، تمام ساكنان آن سرزمين را هلاک نمودند. 41از قادش برنيع تا غزه و از جوشن تا جبعون همه را قتل عام كردند. 42همهٔ اين پيروزیها در يک لشكركشی انجام شد، زيرا خداوند، خدای اسرائيل، برای قومش می‌جنگيد. 43پس از آن، يوشع با تمام افراد خود به اردوگاه خويش در جلجال بازگشت.