ኢሳይያስ 66 – NASV & NAV

New Amharic Standard Version

ኢሳይያስ 66:1-24

ፍርድና ተስፋ

1እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ሰማይ ዙፋኔ ነው፤

ምድርም የእግሬ ማረፊያ ናት፤

ታዲያ የምትሠሩልኝ ቤት፣

የማርፍበትስ ስፍራ የቱ ነው?

2እነዚህን ነገሮች ሁሉ እጄ አልሠራችምን?

እንዲገኙስ ያደረግሁ እኔ አይደለሁምን?”

ይላል እግዚአብሔር

“ነገር ግን እኔ ወደዚህ፣

ትሑት ወደ ሆነና መንፈሱ ወደ ተሰበረ፣

በቃሌም ወደሚንቀጠቀጥ ሰው እመለከታለሁ።

3ነገር ግን ወይፈን የሚሠዋልኝ፣

ሰው እንደሚገድል ነው፤

የበግ ጠቦት የሚያቀርብልኝ፣

የውሻ ዐንገት እንደሚሰብር ሰው ነው፤

የእህል ቍርባን የሚያዘጋጅልኝ፣

የዕሪያ ደም እንደሚያቀርብልኝ ሰው ነው፤

የመታሰቢያን ዕጣን የሚያጥንልኝም፣

ጣዖትን እንደሚያመልክ ሰው ነው፤

የገዛ መንገዳቸውን መርጠዋል፤

ነፍሳቸውም በርኩሰታቸው ደስ ይላታል።

4ስለዚህ ችግር እንዲደርስባቸው አደርጋለሁ፤

የፈሩትንም አመጣባቸዋለሁ፤

በተጣራሁ ጊዜ የመለሰ፣

በተናገርሁ ጊዜ ያደመጠ ሰው የለምና።

በፊቴ ክፉ ነገር አደረጉ፤

የሚያስከፋኝንም መረጡ።”

5እናንት በቃሉ የምትንቀጠቀጡ፣

ይህን የእግዚአብሔር ቃል ስሙ፤

“እናንት ወንድሞቻችሁ የጠሏችሁ፣

ስለ ስሜም አውጥተው የጣሏችሁ፣

‘እስቲ እግዚአብሔር ይክበርና፣

የእናንተን ደስታ እንይ’ አሏችሁ፤

ይሁን እንጂ ማፈራቸው አይቀርም።

6ያን የጩኸት ድምፅ ከከተማው ስሙ!

ያን ጫጫታ ከቤተ መቅደሱ ስሙ!

ይኸውም የእግዚአብሔር ድምፅ ነው፤

ለጠላቶቹም የሚገባቸውን ሁሉ ይከፍላቸዋል።

7“ከማማጧ በፊት፣

ትወልዳለች፤

በምጥ ጣር ከመያዟ በፊት፣

ወንድ ልጅ ትገላገላለች።

8እንዲህ ያለ ነገር ማን ሰምቶ ያውቃል?

እንዲህ ያለ ነገርስ ማን አይቶ ያውቃል?

አገር በአንድ ጀንበር ይፈጠራልን?

ወይስ ሕዝብ በቅጽበት ይገኛል?

ጽዮንን ምጥ ገና ሲጀምራት፣

ልጆቿን ወዲያውኑ ትወልዳለች።

9ሊወለድ የተቃረበውን፣

እንዳይወለድ አደርጋለሁን?” ይላል እግዚአብሔር

“በሚገላገሉበት ጊዜስ፣

ማሕፀን እዘጋለሁን?” ይላል አምላክሽ።

10“ወዳጆቿ የሆናችሁ ሁሉ፣

ከኢየሩሳሌም ጋር ደስ ይበላችሁ፤

ስለ እርሷም ሐሤት አድርጉ፤

ለእርሷ ያለቀሳችሁ ሁሉ፣

ከእርሷ ጋር እጅግ ደስ ይበላችሁ።

11ከሚያጽናኑ ጡቶቿ፣

ትጠባላችሁ፤ ትረካላችሁም፤

እስክትረኩም ትጠጣላችሁ፤

በተትረፈረፈ ሀብቷም ትደሰታላችሁ።”

12እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“እነሆ፤ ሰላምን እንደ ወንዝ ውሃ አፈስስላታለሁ፤

የመንግሥታትንም ብልጽግና እንደ ጅረት ውሃ አጐርፍላታለሁ፤

ትጠባላችሁ፤ በዕቅፏም ትያዛላችሁ፤

በጭኖቿም ላይ ትፈነድቃላችሁ።

13እናት ልጇን እሹሩሩ እንደምትል፣

እኔም እናንተን እሹሩሩ እላችኋለሁ፤

በኢየሩሳሌምም ትጽናናላችሁ።”

14ይህን ስታዩ፣ ልባችሁ ሐሤት ያደርጋል፤

ዐጥንቶቻችሁም እንደ ሣር ይለመልማሉ፤

የእግዚአብሔር እጅ ከባሮቹ ጋር መሆኑ ይታወቃል፤

ቍጣው ግን በጠላቶቹ ላይ ይገለጣል።

15እነሆ፤ እግዚአብሔር በእሳት ነበልባል ይመጣል፤

ሠረገሎቹም እንደ ዐውሎ ነፋስ ናቸው፤

ንዴቱን በቍጣ፣

ተግሣጹንም በእሳት ነበልባል ይገልጣል።

16በእሳትና በሰይፍ፣

እግዚአብሔር ፍርዱን በሰው ሁሉ ላይ ያመጣል፤

በእግዚአብሔር ሰይፍ የሚታረዱት ብዙ ይሆናሉ።

17“ወደ አትክልት ቦታዎች ለመሄድና ከተክሎቹ አንዱን ለማምለክ ራሳቸውን የሚቀድሱና የሚያነጹ፣ የዕሪያዎችንና የዐይጦችን ሥጋ፣ የረከሱ ነገሮችንም የሚበሉ ሁሉ የመጨረሻ ፍርዳቸውን በአንድነት ይቀበላሉ” ይላል እግዚአብሔር

18“እኔም ሥራቸውንና ሐሳባቸውን ስለማውቅ፣ መንግሥታትንና ልሳናትን ሁሉ ልሰበስብ እመጣለሁ፤66፥18 በዕብራይስጡ የዚህ ሐረግ ትርጕም በትክክል አይታወቅም። እነርሱም መጥተው ክብሬንም ያያሉ።

19“በመካከላቸው ምልክት አደርጋለሁ፤ ከእነርሱም የተረፉትን አንዳንዶቹን ወደ አሕዛብ ወደ ተርሴስ፣ ወደ ፉጥ፣ ወደ ታወቁት ቀስተኞች ወደ ሉድ፣ ወደ ቶባልና ያዋን እንዲሁም ዝናዬን ወዳልሰሙትና ክብሬን ወዳላዩት ራቅ ወዳሉት ደሴቶች እልካቸዋለሁ፤ በሕዝቦችም መካከል ክብሬን ይናገራሉ። 20ለእግዚአብሔር ቍርባን እንዲሆኑ ወንድሞቻችሁን ሁሉ ከየመንግሥታቱ ወደ ተቀደሰው ተራራዬ ወደ ኢየሩሳሌም በፈረስ፣ በሠረገላና በጋሪ፣ በበቅሎና በግመል ያመጧቸዋል” ይላል እግዚአብሔር። “እስራኤላውያን የእህል ቍርባናቸውን በሥርዐቱ መሠረት በነጹ ዕቃዎች ወደ እግዚአብሔር ቤተ መቅደስ እንደሚያቀርቡ እነዚህንም ያቀርቧቸዋል። 21እኔም ካህናትና ሌዋውያን ይሆኑ ዘንድ አንዳንዶቹን እመርጣቸዋለሁ” ይላል እግዚአብሔር

22“እኔ የምሠራቸው አዲስ ሰማያትና አዲስ ምድር በፊቴ ጸንተው እንደሚኖሩ፣ የእናንተና የዘራችሁ ስም እንደዚሁ ጸንቶ ይኖራል” ይላል እግዚአብሔር23“ከአንዱ ወር መባቻ እስከ ሌላው፣ እንዲሁም ከአንዱ ሰንበት እስከ ሌላው፣ የሰው ልጅ ሁሉ በፊቴ ሊሰግድ ይመጣል” ይላል እግዚአብሔር24“ወጥተውም በእኔ ላይ ያመፁትን ሰዎች ሬሳ ያያሉ፤ ትላቸው አይሞትም፤ እሳታቸው አይጠፋም፤ ለሰውም ዘር ሁሉ አስጸያፊ ይሆናሉ።”

Ketab El Hayat

إشعياء 66:1-24

الدينونة والرجاء

1هَذَا مَا يَقُولُهُ الرَّبُّ: السَّمَاءُ عَرْشِي وَالأَرْضُ مَوْطِئُ قَدَمَيَّ، فَأَيَّ بَيْتٍ تُشَيِّدُونَ لِي؟ وَأَيْنَ مَقَرُّ رَاحَتِي؟ 2جَمِيعُ هَذِهِ صَنَعَتْهَا يَدِي فَوُجِدَتْ كُلُّهَا، لَكِنَّنِي أُسَرُّ بِالرَّجُلِ الْمُتَوَاضِعِ الْمُنْسَحِقِ الرُّوحِ الَّذِي يَرْتَعِدُ مِنْ كَلِمَتِي. 3إِنَّ مَنْ يَنْحَرُ ثَوْراً كَمَنْ يَقْتُلُ إِنْسَاناً، وَمَنْ يُقَرِّبُ حَمَلاً كَمَنْ يَكْسِرُ عُنُقَ كَلْبٍ، وَمَنْ يُصْعِدُ تَقْدِمَةَ حِنْطَةٍ كَمَنْ يُقَدِّمُ دَمَ خِنْزِيرٍ، وَمَنْ يُحْرِقُ بَخُوراً كَمَنْ يُبَارِكُ وَثَناً، لأَنَّ هَؤُلاءِ آثَرُوا طُرُقَهُمْ، وَاسْتَطَابَتْ نُفُوسُهُمْ أَرْجَاسَهُمْ. 4لِهَذَا أَنَا أَيْضاً أَخْتَارُ بَلايَاهُمْ لَهُمْ وَأُوْقِعُ بِهِمِ الْمَخَاوِفَ، لأَنِّي عِنْدَمَا دَعَوْتُ لَمْ يَسْتَجِيبُوا، وَحِينَ تَكَلَّمْتُ لَمْ يُصْغُوا، إِنَّمَا ارْتَكَبُوا الشَّرَّ فِي عَيْنَيَّ وَاخْتَارُوا مَا لَا أُسَرُّ بِهِ.

5اسْمَعُوا قَوْلَ الرَّبِّ أَيُّهَا الْمُرْتَعِدُونَ مِنْ كَلامِهِ: يَسْخَرُ مِنْكُمْ إخْوَتُكُمُ الَّذِينَ يَكْرَهُونَكُمْ وَيَنْبِذُونَكُمْ لأَنَّكُمْ تَخَافُونَ اسْمِي قَائِلِينَ: لِيَتَمَجَّدِ الرَّبُّ حَتَّى نَشْهَدَ فَرَحَكُمْ. وَلَكِنَّهُمْ لَا يَعْرِفُونَ أَنَّهُمْ هُمُ الَّذِينَ يَخْزَوْنَ. 6اسْمَعُوا صَوْتَ جَلَبَةٍ فِي الْمَدِينَةِ، صَوْتاً مِنَ الْهَيْكَلِ، صَوْتَ الرَّبِّ يُجَازِي أَعْدَاءَهُ. 7شَعْبِي مِثْلُ امْرَأَةٍ وَلَدَتْ قَبْلَ أَنْ تَتَمَخَّضَ، وَقَبْلَ أَنْ تُقَاسِيَ مِنَ الطَّلْقِ أَنْجَبَتْ ذَكَراً. 8مَنْ سَمِعَ مِثْلَ هَذَا، وَمَنْ رَأَى نَظِيرَهُ؟ أَتُوْلَدُ بِلادٌ فِي يَوْمٍ وَاحِدٍ؟ أَمْ تُخْلَقُ أُمَّةٌ دَفْعَةً وَاحِدَةً؟ فَمَا إِنْ تَمَخَّضَتْ صِهْيَوْنُ حَتَّى أَنْجَبَتْ أَبْنَاءَهَا. 9يَقُولُ الرَّبُّ: هَلْ أُمْخِضُ وَلا أُوَلِّدُ؟ هَلْ أُغْلِقُ الرَّحِمَ وَأَنَا الْمُوَلِّدُ؟ 10تَهَلَّلُوا مَعَ أُورُشَلِيمَ وَافْرَحُوا لَهَا يَا كُلَّ مُحِبِّيهَا، ابْتَهِجُوا مَعَهَا بِفَرَحٍ يَا جَمِيعَ النَّائِحِينَ عَلَيْهَا. 11لِكَيْ تَرْضَعُوا وَتَشْبَعُوا مِنْ ثَدْيِ تَعْزِيَاتِهَا، وَلِكَيْ تَحْلِبُوا بِوَفْرَةٍ وَتَتَلَذَّذُوا مِنْ دِرَّةِ مَجْدِهَا.

12لأَنَّهُ هَكَذَا يَقُولُ الرَّبُّ: هَا أَنَا أُسْبِغُ عَلَيْهَا الْخَيْرَ كَنَهْرٍ، وَأُجْرِي إِلَيْهَا ثَرْوَةَ الأُمَمِ كَسَيْلٍ مُتَدَفِّقٍ، فَتَرْضَعُونَ، وَتُحْمَلُونَ فِي الْحِضْنِ، وَعَلَى رُكْبَتَيْهَا تُدَلَّلُونَ. 13وَأُعَزِّيكُمْ كَمَنْ تُعَزِّيه أُمُّهُ، وَفِي أُورُشَلِيمَ تُعَزَّوْنَ. 14وَتَشْهَدُونَ فَتُسَرُّ قُلُوبُكُمْ وَتَزْدَهِرُ عِظَامُكُمْ كَالْعُشْبِ، فَتُصبِحُ يَدُ الرَّبِّ مَعْرُوفَةً عِنْدَ عَبِيدِهِ، وَيَنْصَبُّ غَضَبُهُ عَلَى أَعْدَاِئهِ. 15لأَنَّهُ هَا هُوَ الرَّبُّ مُقْبِلٌ بِنَارٍ، وَمَرْكَبَاتُهُ كَالْعَاصِفَةِ، لِيَسْكُبَ غَضَبَهُ بِسَخَطٍ، وَزَجْرَهُ بِلَهِيبِ نَارٍ. 16لأَنَّ الرَّبَّ يُعَاقِبُ أَهْلَ الأَرْضِ بِنَارِهِ وَسَيْفِهِ، وَيَكْثُرُ قَتْلَى الرَّبِّ. 17وَالَّذِينَ يَتَطَهَّرُونَ وَيَتَقَدَّسُونَ وَيَقْصِدُونَ إِلَى الْحَدَائِقِ حَيْثُ يَعْبُدُونَ وَثَناً قَائِماً وَرَاءَ أَشْجَارِهَا، وَيَأْكُلُونَ لَحْمَ الْخِنْزِيرِ وَالْفِئْرَانِ، وَكُلَّ اللُّحُومِ الْمُحَرَّمَةِ، مَصِيرُهُمُ الْهَلاكُ.

الله يتمجد بشعبه

18وَلأَنِّي عَالِمٌ بِأَعْمَالِهِمْ وَأَفْكَارِهِمْ فَأَنَا مُزْمِعٌ أَنْ آتِيَ لأَجْمَعَ كُلَّ الأُمَمِ وَالأَلْسِنَةِ، فَيَتَوَافَدُونَ وَيَرَوْنَ مَجْدِي 19وَأَجْعَلُ بَيْنَهُمْ آيَةً وَأَبْعَثُ بَعْضَ النَّاجِينَ مِنْهُمْ إِلَى الأُمَمِ: إِلَى تَرْشِيشَ، وَفُولَ، وَلُودَ، الْمَهَرَةِ فِي رَمْيِ السِّهَامِ، وَإِلَى تُوبَالَ وَيَاوَانَ وَإِلَى الْجَزَائِرِ الْبَعِيدَةِ مِمَّنْ لَمْ يَسْمَعُوا بِشُهْرَتِي أَوْ يَرَوْا مَجْدِي، فَيُذِيعُونَ مَجْدِي بَيْنَ الأُمَمِ. 20وَيُحْضِرُونَ جَميِعَ إِخْوَتِكُمْ مِنْ سَائِرِ الأُمَمِ، تَقْدِمَةً لِلرَّبِّ، عَلَى مُتُونِ الْجِيَادِ، وَفِي الْمَرْكَبَاتِ وَالْهَوَادِجِ، وَعَلَى ظُهُورِ الْبِغَالِ وَأَسْنِمَةِ الْجِمَالِ، إِلَى أُورُشَلِيمَ جَبَلِ قُدْسِي، كَمَا يُحْضِرُ الإِسْرَائِيلِيُّونَ تَقْدِمَةَ الْحِنْطَةِ فِي آنِيَةٍ طَاهِرَةٍ إِلَى بَيْتِ الرَّبِّ 21وَمِنْهُمْ أَصْطَفِي كَهَنَةً وَلاوِيِّينَ يَقُولُ الرَّبُّ. 22لأَنَّهُ كَمَا تَدُومُ أَمَامِي السَّمَاوَاتُ الْجَدِيدَةُ وَالأَرْضُ الْجَدِيدَةُ الَّتِي أَنَا أَصْنَعُهَا هَكَذَا تَدُومُ ذُرِّيَّتُكُمْ وَذِكْرُكُمْ. 23وَيَأْتِي مِنْ رَأْسِ شَهْرٍ إِلَى رَأْسِ شَهْرٍ، وِمِنْ سَبْتٍ إِلَى سَبْتٍ كُلُّ بَنِي الْبَشَرِ لِيَعْبُدُونِي، 24ثُمَّ يَمْضُونَ لِمُشَاهَدَةِ جُثَثِ الرِّجَالِ الَّذِينَ تَمَرَّدُوا عَلَيَّ، لأَنَّ دُودَهُمْ لَا يَمُوتُ وَنَارَهُمْ لَا تَخْمَدُ. وَيَكُونُونَ مَثَارَ اشْمِئْزَازِ جَمِيعِ النَّاسِ.