ኢሳይያስ 63 – NASV & NIVUK

New Amharic Standard Version

ኢሳይያስ 63:1-19

እግዚአብሔር የሚቤዥበትና የሚበቀልበት ቀን

1ይህ ከኤዶም፣

ቀይ የተነከረ መጐናጸፊያ ለብሶ ከባሶራ የሚመጣ ማን ነው?

ይህ ክብርን የተጐናጸፈ፣

በኀይሉ ታላቅነት እየተራመደ የሚመጣውስ ማን ነው?

“በጽድቅ የምናገር፣

ለማዳንም ኀይል ያለኝ እኔው ነኝ።”

2መጐናጸፊያህ፣ ለምን በወይን መጭመቂያ፣

ወይን እንደሚረግጡ ሰዎች ልብስ ቀላ?

3“እኔ በመጭመቂያው ወይኑን ብቻዬን ረገጥሁ፤

ከመንግሥታት ማንም ከእኔ ጋር አልነበረም፤

በቍጣዬ ረገጥኋቸው፤

በመዓቴም ጨፈለቅኋቸው፤

ደማቸው በመጐናጸፊያዬ ላይ ተረጭቷል፤

ልብሴንም በክዬዋለሁ።

4የበቀል ቀን በልቤ አለ፤

የምቤዥበትም ዓመት ደርሷል።

5ተመለከትሁ፤ የሚረዳ ግን አልነበረም፤

የሚያግዝ ባለመኖሩም ተገረምሁ፤

ስለዚህ የገዛ ክንዴ ድነትን አመጣልኝ፤

የገዛ ቍጣዬም አጸናኝ፤

6መንግሥታትን በቍጣዬ ረጋገጥሁ፤

በመዓቴም አሰከርኋቸው፤

ደማቸውንም በምድር ላይ አፈሰስሁ።”

ውዳሴና ጸሎት

7የእግዚአብሔርን ቸርነት፣

እግዚአብሔር ስላደረገልን ሁሉ፣

ስለሚመሰገንበት ሥራው፣

እንደ ፍቅሩና እንደ ቸርነቱ መጠን፣

ለእስራኤል ቤት ያደረገውን፣

አዎን፣ ስላደረገው መልካም ነገር እናገራለሁ።

8እርሱም፣ “ርግጥ ነው፤ እነርሱ ሕዝቤ ናቸው፤

የማይዋሹኝ ወንዶች ልጆቼ ናቸው” አለ።

ስለዚህም አዳኝ ሆነላቸው።

9በጭንቃቸው ሁሉ ተጨነቀ፤

የፊቱም መልአክ አዳናቸው፤

በፍቅሩና በምሕረቱ ዋጃቸው፤

በቀደመው ዘመን ሁሉ አነሣቸው፤

ተሸከማቸውም።

10እነርሱ ግን ዐመፁ፤

ቅዱስ መንፈሱንም አሳዘኑ፤

ስለዚህ ተመልሶ ጠላት ሆናቸው፤

እርሱ ራሱ ተዋጋቸው።

11ከዚያም ሕዝቡ የጥንቱን ዘመን፣

የሙሴንና የሕዝቡን ጊዜ እንዲህ በማለት አስታወሱ፤

የበጎቹን እረኛ፣

ከባሕሩ ያወጣቸው እርሱ የት አለ?

ቅዱስ መንፈሱንም፣

በመካከላቸው ያኖረ እርሱ የት አለ?

12የከበረው ኀያል ክንድ፣

በሙሴ ቀኝ እጅ ላይ እንዲያርፍ አደረገ፤

ለራሱ የዘላለም ዝና እንዲሆንለት፣

ውሆችን በፊታቸው ከፈለ።

13ፈረስ በምድረ በዳ እንደሚያልፍ ሁሉ፣

እነርሱንም በጥልቁ ውስጥ አሳልፎ መራቸው፤

ስለዚህም አልተሰናከሉም፤

14ወደ ሸለቆ እንደሚወርድ የከብት መንጋ፣

በእግዚአብሔር መንፈስ ዕረፍት ተሰጣቸው።

ሕዝብህን በዚህ ሁኔታ የመራሃቸው፣

ስምህን የከበረ ለማድረግ ነው።

15ከተቀደሰው፣ ከተከበረውና ከፍ ካለው ዙፋንህ፣

ከሰማይ ወደ ታች ተመልከት፤

ኀይልህና ቅናትህ የት አለ?

ገርነትህና ርኅራኄህ ከእኛ ርቀዋል።

16አብርሃም ባያውቀን፣

እስራኤልም ባያስታውሰን እንኳ፣

አንተ እኮ አባታችን ነህ፤

እግዚአብሔር ሆይ፤ አንተ አባታችን ነህ፤

ከጥንትም ቢሆን ስምህ “ቤዛችን” ነው።

17እግዚአብሔር ሆይ፤ ከመንገድህ እንድንወጣ፣

ልባችንን በማደንደን ለምን እንዳንፈራህ አደረግኸን?

ስለ ባሮችህ ስትል፣

ስለ ርስትህ ነገዶች ስትል እባክህ ተመለስ።

18ለጥቂት ጊዜ ሕዝብህ የተቀደሰውን ስፍራ ወርሶ ነበር፤

አሁን ግን ጠላቶቻችን መቅደስህን ረገጡት።

19እኛ እኮ ጥንትም የአንተው ነን፤

እነርሱን ግን አንተ አላገዝሃቸውም፤

በስምህም አልተጠሩም።63፥19 ወይም፣ አንተ እንዳልገዛሃቸው እንመስላለን፣ ልክ በአንተ ስም እንዳልተጠሩት

New International Version – UK

Isaiah 63:1-19

God’s day of vengeance and redemption

1Who is this coming from Edom,

from Bozrah, with his garments stained crimson?

Who is this, robed in splendour,

striding forward in the greatness of his strength?

‘It is I, proclaiming victory,

mighty to save.’

2Why are your garments red,

like those of one treading the winepress?

3‘I have trodden the winepress alone;

from the nations no-one was with me.

I trampled them in my anger

and trod them down in my wrath;

their blood spattered my garments,

and I stained all my clothing.

4It was for me the day of vengeance;

the year for me to redeem had come.

5I looked, but there was no-one to help,

I was appalled that no-one gave support;

so my own arm achieved salvation for me,

and my own wrath sustained me.

6I trampled the nations in my anger;

in my wrath I made them drunk

and poured their blood on the ground.’

Praise and prayer

7I will tell of the kindnesses of the Lord,

the deeds for which he is to be praised,

according to all the Lord has done for us –

yes, the many good things

he has done for Israel,

according to his compassion and many kindnesses.

8He said, ‘Surely they are my people,

children who will be true to me’;

and so he became their Saviour.

9In all their distress he too was distressed,

and the angel of his presence saved them.63:9 Or Saviour 9 in their distress. / It was no envoy or angel / but his own presence that saved them

In his love and mercy he redeemed them;

he lifted them up and carried them

all the days of old.

10Yet they rebelled

and grieved his Holy Spirit.

So he turned and became their enemy

and he himself fought against them.

11Then his people recalled63:11 Or But may he recall the days of old,

the days of Moses and his people –

where is he who brought them through the sea,

with the shepherd of his flock?

Where is he who set

his Holy Spirit among them,

12who sent his glorious arm of power

to be at Moses’ right hand,

who divided the waters before them,

to gain for himself everlasting renown,

13who led them through the depths?

Like a horse in open country,

they did not stumble;

14like cattle that go down to the plain,

they were given rest by the Spirit of the Lord.

This is how you guided your people

to make for yourself a glorious name.

15Look down from heaven and see,

from your lofty throne, holy and glorious.

Where are your zeal and your might?

Your tenderness and compassion are withheld from us.

16But you are our Father,

though Abraham does not know us

or Israel acknowledge us;

you, Lord, are our Father,

our Redeemer from of old is your name.

17Why, Lord, do you make us wander from your ways

and harden our hearts so we do not revere you?

Return for the sake of your servants,

the tribes that are your inheritance.

18For a little while your people possessed your holy place,

but now our enemies have trampled down your sanctuary.

19We are yours from of old;

but you have not ruled over them,

they have not been called63:19 Or We are like those you have never ruled, / like those never called by your name.