ኢሳይያስ 60 – NASV & KJV

New Amharic Standard Version

ኢሳይያስ 60:1-22

የጽዮን ክብር

1“ብርሃንሽ መጥቷልና ተነሺ አብሪ፤

የእግዚአብሔርም ክብር ወጥቶልሻል።

2እነሆ፤ ጨለማ ምድርን፣

ድቅድቅ ጨለማም ሕዝቦችን ይሸፍናል፤

ነገር ግን እግዚአብሔር ወጥቶልሻል፤

ክብሩንም ይገልጥልሻል።

3ሕዝቦች ወደ ብርሃንሽ፣

ነገሥታትም ወደ ንጋትሽ ጸዳል ይመጣሉ።

4“ቀና በዪ፤ ዙሪያሽን ተመልከቺ፤

ሁሉም ተሰብስበው ወደ አንቺ ይመጣሉ፤

ወንዶች ልጆችሽ ከሩቅ፣

ሴቶች ልጆችሽም በዕቅፍ ወደ አንቺ ይመጣሉ።

5ከዚያም ታያለሽ፤ ታብረቀርቂያለሽ፤

ልብሽ ይዘልላል፤ በደስታም ይሞላል።

በባሕሮች ያለው ሀብት ወደ አንቺ ይመጣል፤

የነገሥታትም ብልጽግና የአንቺ ይሆናል።

6የግመል መንጋ፣

የምድያምና የጌፌር ግልገል ግመሎች

ምድርሽን ይሞላሉ፤

ወርቅና ዕጣን ይዘው፣

የእግዚአብሔርን ምስጋና እያወጁ፣

ሁሉም ከሳባ ይመጣሉ።

7የቄዳር የበግ መንጋ ሁሉ ወደ አንቺ ይሰበሰባል፤

የነባዮት አውራ በጎች ያገለግሉሻል።

እነዚህም በመሠዊያዬ ላይ ተቀባይነት የሚኖራቸው መሥዋዕቶች ይሆናሉ፤

እኔም የክብር መቅደሴን ግርማ አጐናጽፈዋለሁ።

8“ርግቦች ወደ ጐጇቸው እንደሚበርሩ፣

እንደ ደመና የሚጓዙ እነዚህ እነማን ናቸው?

9በርግጥ ደሴቶች እኔን ተስፋ ያደርጋሉ፤

እርሱ ክብሩን ስላጐናጸፈሽ፣

ለእስራኤል ቅዱስ፣

ለእግዚአብሔር አምላክሽ ክብር፣

ከሩቅ ወንዶች ልጆችሽን፣

ከነብራቸውና ከነወርቃቸው ለማምጣት፣

የተርሴስ መርከቦች60፥9 ወይም፣ የንግድ መርከቦች ቀድመው ይወጣሉ።

10“ባዕዳን ቅጥሮችሽን ይሠራሉ፤

ነገሥታቶቻቸው ያገለግሉሻል፤

በቍጣዬ ብመታሽም፣

ርኅራኄዬን በፍቅር አሳይሻለሁ።

11በሮችሽ ምንጊዜም የተከፈቱ ይሆናሉ፤

ቀንም ሆነ ሌሊት ከቶ አይዘጉም፤

ይህም ሰዎች የመንግሥታትን ብልጽግና ወደ አንቺ እንዲያመጡ፣

ነገሥታታቸውም በድል ወደ አንቺ እንዲገቡ ነው።

12ለአንቺ የማይገዛ ሕዝብና መንግሥት ይጠፋል፤

ፈጽሞም ይደመሰሳል።

13“የመቅደሴን ቦታ ለማስጌጥ፣

የሊባኖስ ክብር፣

ጥዱ፣ አስታውና ባርሰነቱ በአንድነት ወደ አንቺ ይመጣሉ፤

እግሬ የሚያርፍበትንም ስፍራ አከብራለሁ።

14የአስጨናቂዎችሽ ወንዶች ልጆች እየሰገዱ ወደ አንቺ ይመጣሉ፤

የናቁሽም ሁሉ እግርሽ ላይ ይደፋሉ፤

የእግዚአብሔር ከተማ፣

የእስራኤል ቅዱስ ገንዘብ የሆንሽው ጽዮን ብለው ይጠሩሻል።

15“የተተውሽና የተጠላሽ፣

ማንም ሰው የማያልፍብሽ ብትሆኝም እንኳ፣

እኔ የዘላለም ትምክሕት፣

የትውልድም ሁሉ ደስታ አደርግሻለሁ።

16የመንግሥታትን ወተት ትጠጪያለሽ፤

የነገሥታትንም ጡት ትጠቢያለሽ፤

ከዚያም እኔ እግዚአብሔር አዳኝሽ፣

ቤዛሽም እኔ የያዕቆብ ኀያል እንደ ሆንሁ ታውቂያለሽ።

17በናስ ፈንታ ወርቅ፣

በብረትም ፈንታ ብር አመጣልሻለሁ።

ሰላምን ገዥሽ፣

ጽድቅንም አለቃሽ አደርጋለሁ።

18ከእንግዲህ በምድርሽ ሁከት፣

በጠረፎችሽም ጥፋትና መፈራረስ አይሰማም፤

ነገር ግን ቅጥሮችሽን ድነት፣

በሮችሽንም ምስጋና ብለሽ ትጠሪያቸዋለሽ።

19ከእንግዲህ በቀን የፀሓይ ብርሃን አያስፈልግሽም፤

በሌሊትም የጨረቃ ብርሃን አያበራልሽም፤

እግዚአብሔር የዘላለም ብርሃን፣

አምላክሽም ክብርሽ ይሆናልና።

20ፀሓይሽ ከእንግዲህ አትጠልቅም፤

ጨረቃሽም ብርሃን መስጠቷን አታቋርጥም፤

እግዚአብሔር የዘላለም ብርሃንሽ ይሆናል፤

የሐዘንሽም ቀን ያከትማል።

21ሕዝብሽም ሁሉ ጻድቃን ይሆናሉ፤

ምድሪቱንም ለዘላለም ይወርሳሉ፤

ለክብሬ መግለጫ ይሆኑ ዘንድ፣

የእጆቼ ሥራ፣

እኔ የተከልኋቸው ቍጥቋጦች ናቸው።

22ከአንቺ ታናሽ የሆነው ሺሕ፣

ከሁሉም የመጨረሻው ታናሽ ኀያል መንግሥት ይሆናል፤

እኔ እግዚአብሔር ነኝ፤

ጊዜውም ሲደርስ ይህን በፍጥነት አደርጋለሁ።”

King James Version

Isaiah 60:1-22

1Arise, shine; for thy light is come, and the glory of the LORD is risen upon thee.60.1 shine…: or, be enlightened; for thy light cometh 2For, behold, the darkness shall cover the earth, and gross darkness the people: but the LORD shall arise upon thee, and his glory shall be seen upon thee. 3And the Gentiles shall come to thy light, and kings to the brightness of thy rising. 4Lift up thine eyes round about, and see: all they gather themselves together, they come to thee: thy sons shall come from far, and thy daughters shall be nursed at thy side. 5Then thou shalt see, and flow together, and thine heart shall fear, and be enlarged; because the abundance of the sea shall be converted unto thee, the forces of the Gentiles shall come unto thee.60.5 abundance…: or, noise of the sea shall be turned toward thee60.5 forces: or, wealth 6The multitude of camels shall cover thee, the dromedaries of Midian and Ephah; all they from Sheba shall come: they shall bring gold and incense; and they shall shew forth the praises of the LORD. 7All the flocks of Kedar shall be gathered together unto thee, the rams of Nebaioth shall minister unto thee: they shall come up with acceptance on mine altar, and I will glorify the house of my glory. 8Who are these that fly as a cloud, and as the doves to their windows?

9Surely the isles shall wait for me, and the ships of Tarshish first, to bring thy sons from far, their silver and their gold with them, unto the name of the LORD thy God, and to the Holy One of Israel, because he hath glorified thee. 10And the sons of strangers shall build up thy walls, and their kings shall minister unto thee: for in my wrath I smote thee, but in my favour have I had mercy on thee. 11Therefore thy gates shall be open continually; they shall not be shut day nor night; that men may bring unto thee the forces of the Gentiles, and that their kings may be brought.60.11 forces: or, wealth 12For the nation and kingdom that will not serve thee shall perish; yea, those nations shall be utterly wasted. 13The glory of Lebanon shall come unto thee, the fir tree, the pine tree, and the box together, to beautify the place of my sanctuary; and I will make the place of my feet glorious. 14The sons also of them that afflicted thee shall come bending unto thee; and all they that despised thee shall bow themselves down at the soles of thy feet; and they shall call thee, The city of the LORD, The Zion of the Holy One of Israel.

15Whereas thou hast been forsaken and hated, so that no man went through thee, I will make thee an eternal excellency, a joy of many generations. 16Thou shalt also suck the milk of the Gentiles, and shalt suck the breast of kings: and thou shalt know that I the LORD am thy Saviour and thy Redeemer, the mighty One of Jacob. 17For brass I will bring gold, and for iron I will bring silver, and for wood brass, and for stones iron: I will also make thy officers peace, and thine exactors righteousness. 18Violence shall no more be heard in thy land, wasting nor destruction within thy borders; but thou shalt call thy walls Salvation, and thy gates Praise. 19The sun shall be no more thy light by day; neither for brightness shall the moon give light unto thee: but the LORD shall be unto thee an everlasting light, and thy God thy glory. 20Thy sun shall no more go down; neither shall thy moon withdraw itself: for the LORD shall be thine everlasting light, and the days of thy mourning shall be ended. 21Thy people also shall be all righteous: they shall inherit the land for ever, the branch of my planting, the work of my hands, that I may be glorified. 22A little one shall become a thousand, and a small one a strong nation: I the LORD will hasten it in his time.