ኢሳይያስ 50 – NASV & KLB

New Amharic Standard Version

ኢሳይያስ 50:1-11

የእስራኤል ኀጢአትና የእግዚአብሔር ባሪያ ታዛዥነት

1እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“እናታችሁን የፈታሁበት

የፍቺ ወረቀት የት አለ?

ወይስ እናንተን የሸጥኋችሁ

ለየትኛው አበዳሪዬ ነው?

እነሆ፤ ስለ ኀጢአታችሁ ተሸጣችኋል፤

ስለ መተላለፋችሁም እናታችሁ ተፈትታለች።

2በመጣሁ ጊዜ ለምን በዚያ ሰው አልነበረም?

በተጣራሁስ ጊዜ የሚመልስ ሰው እንዴት በዚያ ታጣ?

ስለ እናንተ ወጆ ለመክፈል ክንዴ ዐጥራ ነበርን?

እናንተንስ ለማዳን ኀይል አነሰኝን?

እነሆ፤ በተግሣጼ ባሕሩን አደርቃለሁ፤

ወንዞችን ምድረ በዳ አደርጋለሁ፤

ዓሦቻቸው ውሃ በማጣት ይሸታሉ፤

በጥማትም ይሞታሉ።

3ሰማይን ጨለማ አለብሰዋለሁ፤

ማቅን መሸፈኛው አደርጋለሁ።”

4ልዑል እግዚአብሔር የተባ አንደበት ሰጥቶኛል፤

ስለዚህ ደካሞችን ብርቱ ለማድረግ ምን ማለት እንዳለብኝ ዐውቃለሁ፤

በየማለዳው ያነቃኛል፤

በመማር ላይ እንዳለ ተማሪ ለመስማት ጆሮዬን ያነቃዋል።

5ልዑል እግዚአብሔር ጆሮዬን ከፍቶታል፤

እኔም ዐመፀኛ አይደለሁም፤

ወደ ኋላም አላፈገፈግሁም።

6ለሚገርፉኝ ጀርባዬን፣

ጢሜን ለሚነጩ ጕንጬን ሰጠሁ፤

ፊቴን ከውርደት፣

ከጥፋትም አልሰወርሁም።

7ጌታ እግዚአብሔር ስለሚረዳኝ አልዋረድም፤

ስለዚህ ፊቴን እንደ ባልጩት ድንጋይ

አድርጌአለሁ፤

እንደማላፍርም ዐውቃለሁ።

8ንጹሕ መሆኔን የሚያረጋግጥልኝ በአጠገቤ አለ፤

ታዲያ ማን ሊከስሰኝ ይችላል?

እስቲ ፊት ለፊት እንጋጠም!

ተቃዋሚዬስ ማን ነው?

እስቲ ይምጣ!

9የሚረዳኝ እርሱ ጌታ እግዚአብሔር ነው፤

የሚፈርድብኝስ ማን ነው?

እነሆ፤ ሁሉም እንደ ልብስ ያረጃሉ፤

ብልም ይበላቸዋል።

10ከእናንተ እግዚአብሔርን የሚፈራ፣

የባሪያውንም ቃል የሚሰማ ማን ነው?

ያ ሰው በጨለማ የሚሄድ ከሆነና፣

ብርሃንም ከሌለው፣

በእግዚአብሔር ስም ይታመን፤

በአምላኩም ይደገፍ።

11አሁን ግን እናንተ እሳት አንድዳችሁ፣

የራሳችሁን የሚንቦገቦግ ችቦ የያዛችሁ ሁሉ፣

በሉ በእሳታችሁ ብርሃን ሂዱ፤

ባንቦገቦጋችሁትም የችቦ ብርሃን ተመላለሱ።

እንግዲህ ከእጄ የምትቀበሉት ይህ ነው፤

በሥቃይም ትጋደማላችሁ።

Korean Living Bible

이사야 50:1-11

이스라엘의 죄와 순종하는 여호와의 종

1여호와께서 말씀하신다. “남자가 자기 아내를 내쫓듯이 내가 너희를 쫓아내었느냐? 그렇다면 그 이혼 증서는 어디 있느냐? 너희는 사람이 자기 자녀를 종으로 팔듯이 내가 너희를 팔았다고 생각하느냐? 아니다. 너희는 너희 죄와 허물 때문에 팔려 포로로 잡혀갔다.

2“내가 내 백성을 구원하려고 찾아왔어도 반응을 보이는 자가 아무도 없었다. 내가 불러도 어째서 그들은 대답하지 않는가? 내가 50:2 또는 ‘손이 짧아’힘이 부족하고 능력이 없어서 그들을 구원하지 못하겠느냐? 내 명령 한마디면 바다가 마르고 강이 사막이 되어 물이 없으므로 고기들이 죽어 악취가 난다.

3그리고 나는 하늘을 온통 흑암으로 덮어 버릴 수도 있다.”

4주 여호와께서 나에게 할 말을 가르치셔서 피곤한 자를 격려하고 도와줄 수 있게 하시며 아침마다 나를 깨우치셔서 그의 가르치심을 알아듣게 하시는구나.

5여호와께서 나에게 깨닫는 마음을 주셨으므로 나는 거역하거나 뒤로 물러가지 않았으며

6나를 때리는 자들에게 내 등을 맡기고 내 수염을 뽑는 자들에게 내 뺨을 맡기며 그들이 침을 뱉고 모욕할 때에도 내가 얼굴을 가리지 않았다.

7주 여호와께서 나를 도우시므로 내가 당황하지 않을 것이며 내가 얼굴을 부싯돌처럼 굳게 하였으니 수치를 당하지 않을 줄로 안다.

8나를 변호하시는 분이 가까이 계시는데 누가 감히 나와 다툴 수 있겠는가? 내 고소자가 누구냐? 함께 법정으로 가서 맞서 보자.

9주 여호와께서 나를 도우시는데 나를 죄인으로 단정할 자가 누구냐? 나의 모든 원수들은 좀먹은 옷처럼 해어져 없어질 것이다.

10너희 중에 여호와를 두려운 마음으로 섬기며 그 종의 말에 순종하는 자가 누구냐? 빛 없이 흑암 가운데 사는 자들도 여호와를 신뢰하며 자기 하나님을 의지하게 하라.

11다른 사람을 해치려고 하는 자들아, 너희는 너희 꾀에 스스로 망할 것이니 너희가 여호와의 형벌을 받아 고통을 당할 것이다.