ኢሳይያስ 40 – NASV & KJV

New Amharic Standard Version

ኢሳይያስ 40:1-31

የእግዚአብሔርን ሕዝብ የሚያጽናና ቃል

1አጽናኑ፤ ሕዝቤን አጽናኑ፤

ይላል አምላካችሁ።

2ለኢየሩሳሌም አለዝባችሁ ንገሯት፤

ዐውጁላትም፤

በባርነት ያገለገለችበት ዘመን አብቅቷል፤

የኀጢአቷም ዋጋ ተከፍሏል፤

ስለ ኀጢአቷ ሁሉ ከእግዚአብሔር እጅ

ሁለት ዕጥፍ ተቀብላለች።

3የዐዋጅ ነጋሪ ድምፅ እንዲህ ይላል፤

የእግዚአብሔርን መንገድ፣

በምድረ በዳ አዘጋጁ፤

ለአምላካችን አውራ ጐዳና፣

በበረሓ አስተካክሉ።

4ሸለቆው ሁሉ ከፍ ይላል፤

ተራራውና ኰረብታው ሁሉ ዝቅ ይላል፤

ወጣ ገባው ምድር ይስተካከላል፤

ሰርጓጕጡም ሜዳ ይሆናል።

5የእግዚአብሔርም ክብር ይገለጣል፤

ሰው ሁሉ በአንድነት ያየዋል፤

የእግዚአብሔር አፍ ይህን ተናግሯልና።”

6ድምፅም፣ “ጩኽ” አለኝ፤

እኔም፣ “ምን ብዬ ልጩኽ?” አልሁ።

“ሰው ሁሉ እንደ ሣር ነው፤

ክብሩም ሁሉ እንደ ሜዳ አበባ ነው።

7ሣሩ ይደርቃል፤ አበባውም ይረግፋል፤

የእግዚአብሔር እስትንፋስ ነፍሶበታልና፤

ሕዝቡ በርግጥ ሣር ነው።

8ሣሩ ይደርቃል፤ አበባውም ይረግፋል፤

የአምላካችን ቃል ግን ለዘላለም ጸንቶ ይኖራል።”

9አንተ ለጽዮን የምሥራችን የምትነግር፤

ከፍ ወዳለው ተራራ ውጣ፤

አንተ ለኢየሩሳሌም ብሥራት የምትነግር፣40፥9 ወይም፣ ጽዮን ሆይ፤ የምሥራቹን የምታበሥሪ፣ ወደ ረዥም ተራራ ላይ ውጪ ወይም የምሥራቹን የምታበሥሪ ኢየሩሳሌም ሆይ

ድምፅህን ከፍ አድርገህ ጩኽ።

ከፍ አድርገው፤ አትፍራ፤

ለይሁዳም ከተሞች፣

“እነሆ፤ አምላካችሁ!” በል።

10እነሆ፤ጌታ እግዚአብሔር በኀይል

ይመጣል፤

ክንዱ ስለ እርሱ ይገዛል።

እነሆ፤ ዋጋው ከእርሱ ጋር ነው፤

የሚከፍለውም ብድራት አብሮት አለ።

11መንጋውን እንደ እረኛ ያሰማራል፤

ጠቦቶቹን በክንዱ ይሰበስባል፤

በዕቅፉም ይይዛቸዋል፤

የሚያጠቡትንም በጥንቃቄ ይመራል።

12ውሆችን በዕፍኙ የሰፈረ፣

ሰማያትን በስንዝሩ የለካ፣

የምድርን ዐፈር በመስፈሪያ ሰብስቦ የያዘ፣

ተራሮችን በሚዛን፣

ኰረብቶችንም በመድሎት የመዘነ ማነው?

13የእግዚአብሔርን መንፈስ የተረዳ፣

አማካሪውስ ሆኖ ያስተማረው ማነው?

14ዕውቀት ለማግኘት እግዚአብሔር ማንን አማከረ?

ትክክለኛውንስ መንገድ ማን አስተማረው?

ዕውቀትን ያስተማረው፣

የማስተዋልንም መንገድ ያሳየው ማን ነበር?

15እነሆ፤ አሕዛብ በገንቦ ውስጥ እንዳለች ጠብታ ናቸው፤

በሚዛን ላይ እንዳለ ትቢያ ይቈጠራሉ፤

ደሴቶችንም እንደ ደቃቅ ዐፈር ይመዝናቸዋል።

16ሊባኖስ ለመሠዊያ እሳት አትበቃም፤

የእንስሶቿም ቍጥር ለሚቃጠል መሥዋዕት ያንሳል።

17አሕዛብ ሁሉ በፊቱ እንደ ኢምንት ናቸው፤

ከምንም የማይቈጠሩ መና ናቸው።

18እንግዲህ፣ እግዚአብሔርን ከማን ጋር ታወዳድሩታላችሁ?

ከየትኛውስ ምስል ጋር ታነጻጽሩታላችሁ?

19የተቀረጸውንማ ምስል ባለ እጅ ይቀርጸዋል፤

ወርቅ አንጥረኛም በወርቅ ይለብጠዋል፤

የብር ሰንሰለትም ያበጅለታል።

20እንዲህ ያለውን መባ ማቅረብ የማይችል ምስኪን ድኻ፣

የማይነቅዝ ዕንጨት ይመርጣል፤

የማይወድቅ ምስልን ለማቆምም፣

ታዋቂ ባለሙያ ይፈልጋል።

21አላወቃችሁምን?

አልሰማችሁምን?

ከጥንት አልተነገራችሁምን?

ምድር ከተመሠረተች ጀምሮ አላስተዋላችሁምን?

22እርሱ ከምድር ክበብ በላይ በዙፋን ላይ ይቀመጣል፤

ሕዝቦቿም እንደ አንበጣ ናቸው።

ሰማያትን እንደ ድባብ ይዘረጋቸዋል፤

እንደ መኖሪያ ድንኳንም ይተክላቸዋል።

23አለቆችን ኢምንት፣

የዚህን ዓለም ገዦች እንዳልነበሩ ያደርጋቸዋል።

24ተተክለው ምንም ያህል ሳይቈዩ፣

ተዘርተው ምንም ያህል ሳይሰነብቱ፣

ገና ሥር መስደድ ሳይጀምሩ

አነፈሰባቸው፤ እነርሱም ደረቁ፤

ዐውሎ ነፋስም እንደ ገለባ ጠራርጎ ወሰዳቸው።

25ቅዱሱ፣ “ከማን ጋር ታወዳድሩኛላችሁ?

የሚስተካከለኝስ ማን አለ?” ይላል።

26ዐይናችሁን አንሡ፤ ወደ ሰማይ ተመልከቱ፤

እነዚህን ሁሉ የፈጠረ ማን ነው?

የከዋክብትን ሰራዊት አንድ በአንድ የሚያወጣቸው፣

በየስማቸው የሚጠራቸው እርሱ ነው።

ከኀይሉ ታላቅነትና ከችሎታው ብርታት የተነሣ፣

አንዳቸውም አይጠፉም።

27ያዕቆብ ሆይ፤ ለምን እንዲህ ትላለህ?

እስራኤል ሆይ፤ ለምን እንዲህ ትናገራለህ?

“መንገዴ ከእግዚአብሔር ተሰውራለች፤

ፍርዴም በአምላኬ ቸል ተብላለች” ለምን ትላለህ?

28አታውቅምን?

አልሰማህምን?

እግዚአብሔር የዘላለም አምላክ፣

የምድር ዳርቻ ፈጣሪ ነው።

አይደክምም፤ አይታክትም፤

ማስተዋሉም በማንም አይመረመርም።

29ለደከመው ብርታት ይሰጣል፤

ለዛለው ጕልበት ይጨምራል።

30ወጣቶች እንኳ ይደክማሉ፤ ይታክታሉም፤

ጐበዛዝትም ተሰናክለው ይወድቃሉ።

31እግዚአብሔርን ተስፋ የሚያደርጉ ግን፣

ኀይላቸውን ያድሳሉ፤

እንደ ንስር በክንፍ ይወጣሉ፤

ይሮጣሉ፤ አይታክቱም፤

ይሄዳሉ፤ አይደክሙም።

King James Version

Isaiah 40:1-31

1Comfort ye, comfort ye my people, saith your God. 2Speak ye comfortably to Jerusalem, and cry unto her, that her warfare is accomplished, that her iniquity is pardoned: for she hath received of the LORD’s hand double for all her sins.40.2 comfortably: Heb. to the heart40.2 warfare: or, appointed time

3¶ The voice of him that crieth in the wilderness, Prepare ye the way of the LORD, make straight in the desert a highway for our God. 4Every valley shall be exalted, and every mountain and hill shall be made low: and the crooked shall be made straight, and the rough places plain:40.4 straight: or, a straight place40.4 plain: or, a plain place 5And the glory of the LORD shall be revealed, and all flesh shall see it together: for the mouth of the LORD hath spoken it. 6The voice said, Cry. And he said, What shall I cry? All flesh is grass, and all the goodliness thereof is as the flower of the field: 7The grass withereth, the flower fadeth: because the spirit of the LORD bloweth upon it: surely the people is grass. 8The grass withereth, the flower fadeth: but the word of our God shall stand for ever.

9¶ O Zion, that bringest good tidings, get thee up into the high mountain; O Jerusalem, that bringest good tidings, lift up thy voice with strength; lift it up, be not afraid; say unto the cities of Judah, Behold your God!40.9 O Zion…: or, O thou that tellest good tidings to Zion40.9 O Jerusalem…: or, O thou that tellest good tidings to Jerusalem 10Behold, the Lord GOD will come with strong hand, and his arm shall rule for him: behold, his reward is with him, and his work before him.40.10 with strong…: or, against the strong40.10 his work: or, recompence for his work 11He shall feed his flock like a shepherd: he shall gather the lambs with his arm, and carry them in his bosom, and shall gently lead those that are with young.40.11 that…: or, that give suck

12¶ Who hath measured the waters in the hollow of his hand, and meted out heaven with the span, and comprehended the dust of the earth in a measure, and weighed the mountains in scales, and the hills in a balance?40.12 a measure: Heb. a tierce 13Who hath directed the Spirit of the LORD, or being his counsellor hath taught him?40.13 his…: Heb. man of his counsel 14With whom took he counsel, and who instructed him, and taught him in the path of judgment, and taught him knowledge, and shewed to him the way of understanding?40.14 instructed…: Heb. made him understand40.14 understanding: Heb. understandings? 15Behold, the nations are as a drop of a bucket, and are counted as the small dust of the balance: behold, he taketh up the isles as a very little thing. 16And Lebanon is not sufficient to burn, nor the beasts thereof sufficient for a burnt offering. 17All nations before him are as nothing; and they are counted to him less than nothing, and vanity.

18¶ To whom then will ye liken God? or what likeness will ye compare unto him? 19The workman melteth a graven image, and the goldsmith spreadeth it over with gold, and casteth silver chains. 20He that is so impoverished that he hath no oblation chooseth a tree that will not rot; he seeketh unto him a cunning workman to prepare a graven image, that shall not be moved.40.20 is so…: Heb. is poor of oblation 21Have ye not known? have ye not heard? hath it not been told you from the beginning? have ye not understood from the foundations of the earth? 22It is he that sitteth upon the circle of the earth, and the inhabitants thereof are as grasshoppers; that stretcheth out the heavens as a curtain, and spreadeth them out as a tent to dwell in:40.22 It is…: or, Him that 23That bringeth the princes to nothing; he maketh the judges of the earth as vanity. 24Yea, they shall not be planted; yea, they shall not be sown: yea, their stock shall not take root in the earth: and he shall also blow upon them, and they shall wither, and the whirlwind shall take them away as stubble. 25To whom then will ye liken me, or shall I be equal? saith the Holy One. 26Lift up your eyes on high, and behold who hath created these things, that bringeth out their host by number: he calleth them all by names by the greatness of his might, for that he is strong in power; not one faileth.

27Why sayest thou, O Jacob, and speakest, O Israel, My way is hid from the LORD, and my judgment is passed over from my God?

28¶ Hast thou not known? hast thou not heard, that the everlasting God, the LORD, the Creator of the ends of the earth, fainteth not, neither is weary? there is no searching of his understanding. 29He giveth power to the faint; and to them that have no might he increaseth strength. 30Even the youths shall faint and be weary, and the young men shall utterly fall: 31But they that wait upon the LORD shall renew their strength; they shall mount up with wings as eagles; they shall run, and not be weary; and they shall walk, and not faint.40.31 renew: Heb. change