ኢሳይያስ 38 – NASV & KJV

New Amharic Standard Version

ኢሳይያስ 38:1-22

የሕዝቅያስ መታመም

1በዚያ ጊዜ ሕዝቅያስ ታመመ፤ ሞት አፋፍ ደረሰ፤ የአሞጽ ልጅ ነቢዩ ኢሳይያስም ወደ እርሱ መጥቶ፣ “እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ ‘ከሕመምህ አትድንም፤ ትሞታለህና ቤትህን አሰናዳ’ ” አለው።

2ሕዝቅያስም ፊቱን ወደ ግድግዳ አዙሮ፣ እንዲህ ሲል ወደ እግዚአብሔር ጸለየ፤ 3እግዚአብሔር ሆይ፤ በፊትህ በታማኝነትና በፍጹም ልብ ደስ የሚያሰኝህንም በማድረግ እንዴት እንደ ኖርሁ አቤቱ ዐስብ።” ሕዝቅያስም አምርሮ አለቀሰ።

4የእግዚአብሔርም ቃል ወደ ኢሳይያስ እንዲህ ሲል መጣ፤ 5“ሂድና ለሕዝቅያስ እንዲህ ብለህ ንገረው፤ ‘የአባትህ የዳዊት አምላክ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ “ጸሎትህን ሰምቻለሁ፤ እንባህንም አይቻለሁ፤ በዕድሜህም ላይ ዐሥራ አምስት ዓመት እጨምርልሃለሁ። 6አንተንና ይህችን ከተማ ከአሦር ንጉሥ እጅ እታደጋለሁ፤ ለከተማዋም እከላከልላታለሁ።”

7“ ‘እግዚአብሔር የገባልህን ቃል እንደሚፈጽምልህ፣ የእግዚአብሔር ምልክት ይህ ነው፤ 8በአካዝ የሰዓት መቍጠሪያ ደረጃ ላይ፣ የወረደውን የፀሓይ ጥላ በዐሥር ደረጃ ወደ ኋላ እንዲመለስ አደርጋለሁ።’ ” ስለዚህ ወርዶ የነበረው የፀሓይ ጥላ ያንኑ ያህል ወደ ኋላ ተመለሰ።

9የይሁዳ ንጉሥ ሕዝቅያስ ከሕመሙ ከተፈወሰ በኋላ የጻፈው ጽሕፈት፤

10እኔ፣ “በዕድሜዬ እኩሌታ፣

በሲኦል ደጆች ማለፍ አለብኝን?

የቀረውንስ ዘመኔን ልነጠቅ ይገባልን?” አልሁ።

11እንዲህም አልሁ፤ “ዳግም እግዚአብሔርን

እግዚአብሔርን በሕያዋን ምድር አላይም፤

ከእንግዲህም የሰውን ዘር አላይም፤

በዚህ ዓለም ከሚኖሩትም ጋር አልሆንም።

12ቤቴ እንደ እረኛ ድንኳን ተነቀለ፤

ከእኔም ተወሰደ፤

ሕይወቴን እንደ ሸማኔ ጠቀለልሁ፤

ከመጠቅለያ ቈርጦኛል፤

ከጧት እስከ ማታ ልትጨርሰኝ ፈጠንህ።

13እስከ ማለዳ በትዕግሥት ጠበቅሁ፤

እርሱ ግን እንደ አንበሳ ዐጥንቶቼን ሁሉ ሰባበረ፤

ከጧት እስከ ማታም ልትጨርሰኝ ፈጠንህ።

14እንደ ጨረባ፣ እንደ ሽመላም ተንጫጫሁ፤

እንደ ርግብ አልጐመጐምሁ፤

ዐይኖቼ ወደ ሰማይ በመመልከት ደከሙ፤

ጌታ ሆይ፤ ተጨንቄአለሁና ታደገኝ!”

15እንግዲህ ምን እላለሁ?

እርሱ ተናግሮኛል፤ ራሱ ደግሞ ይህን አድርጓል፤

ስለ ነፍሴ ጭንቀት፣

ዕድሜዬን ሁሉ በትሕትና እሄዳለሁ።

16ጌታ ሆይ፤ ሰዎች በእነዚህ ነገሮች ይኖራሉ፤

መንፈሴም እንዲሁ በእነዚህ ሕይወትን ያገኛል፤

ፈወስኸኝ፤

በሕይወትም አኖርኸኝ።

17እነሆ፤ በሥቃይ የተጨነቅሁት፣

ለጥቅሜ ሆነ፤

ከጥፋት ጕድጓድ፣

በፍቅርህ ጠበቅኸኝ፤

ኀጢአቴንም ሁሉ፣

ወደ ኋላህ ጣልህ።

18ሲኦል አያመሰግንህም፤

ሞት አያወድስህም፤

ወደ ጕድጓድ የሚወርዱ፣

የአንተን ታማኝነት ተስፋ አያደርጉም።

19እኔ ዛሬ እንደማደርገው፣

ሕያዋን እነርሱ ያመሰግኑሃል።

ስለ አንተ ታማኝነትም፣

አባቶች ለልጆቻቸው ይነግራሉ።

20እግዚአብሔር ያድነኛል፤

ስለዚህ በዕድሜ ዘመናችን ሁሉ፣

በእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ፣

አውታር ባለው መሣሪያ እንዘምራለን።

21ኢሳይያስም፣ “የበለስ ጥፍጥፍ ወስዳችሁ በዕባጩ ላይ አድርጉለት፤ እርሱም ይፈወሳል” ብሎ ነበር።

22ሕዝቅያስም፣ “ወደ እግዚአብሔር ቤተ መቅደስ እወጣ ዘንድ ምልክቱ ምንድን ነው?” ብሎ ነበር።

King James Version

Isaiah 38:1-22

1In those days was Hezekiah sick unto death. And Isaiah the prophet the son of Amoz came unto him, and said unto him, Thus saith the LORD, Set thine house in order: for thou shalt die, and not live.38.1 Set…: Heb. Give charge concerning thy house 2Then Hezekiah turned his face toward the wall, and prayed unto the LORD, 3And said, Remember now, O LORD, I beseech thee, how I have walked before thee in truth and with a perfect heart, and have done that which is good in thy sight. And Hezekiah wept sore.38.3 sore: Heb. with great weeping

4¶ Then came the word of the LORD to Isaiah, saying, 5Go, and say to Hezekiah, Thus saith the LORD, the God of David thy father, I have heard thy prayer, I have seen thy tears: behold, I will add unto thy days fifteen years. 6And I will deliver thee and this city out of the hand of the king of Assyria: and I will defend this city. 7And this shall be a sign unto thee from the LORD, that the LORD will do this thing that he hath spoken; 8Behold, I will bring again the shadow of the degrees, which is gone down in the sun dial of Ahaz, ten degrees backward. So the sun returned ten degrees, by which degrees it was gone down.38.8 sun dial: Heb. degrees by, or, with the sun

9¶ The writing of Hezekiah king of Judah, when he had been sick, and was recovered of his sickness: 10I said in the cutting off of my days, I shall go to the gates of the grave: I am deprived of the residue of my years. 11I said, I shall not see the LORD, even the LORD, in the land of the living: I shall behold man no more with the inhabitants of the world. 12Mine age is departed, and is removed from me as a shepherd’s tent: I have cut off like a weaver my life: he will cut me off with pining sickness: from day even to night wilt thou make an end of me.38.12 with…: or, from the thrum 13I reckoned till morning, that, as a lion, so will he break all my bones: from day even to night wilt thou make an end of me. 14Like a crane or a swallow, so did I chatter: I did mourn as a dove: mine eyes fail with looking upward: O LORD, I am oppressed; undertake for me.38.14 undertake…: or, ease me 15What shall I say? he hath both spoken unto me, and himself hath done it: I shall go softly all my years in the bitterness of my soul. 16O Lord, by these things men live, and in all these things is the life of my spirit: so wilt thou recover me, and make me to live. 17Behold, for peace I had great bitterness: but thou hast in love to my soul delivered it from the pit of corruption: for thou hast cast all my sins behind thy back.38.17 for peace…: or, on my peace came great bitterness38.17 thou hast in…: Heb. thou hast loved my soul from the pit 18For the grave cannot praise thee, death can not celebrate thee: they that go down into the pit cannot hope for thy truth. 19The living, the living, he shall praise thee, as I do this day: the father to the children shall make known thy truth. 20The LORD was ready to save me: therefore we will sing my songs to the stringed instruments all the days of our life in the house of the LORD. 21For Isaiah had said, Let them take a lump of figs, and lay it for a plaister upon the boil, and he shall recover. 22Hezekiah also had said, What is the sign that I shall go up to the house of the LORD?