ኢሳይያስ 24 – NASV & JCB

New Amharic Standard Version

ኢሳይያስ 24:1-23

እግዚአብሔር ምድርን ፈጽሞ ያጠፋታል

1እነሆ፤ እግዚአብሔር ምድርን ባድማ ያደርጋታል፤

ፈጽሞ ያጠፋታል፤

የፍርስራሽ ክምር ያደርጋታል፤

ነዋሪዎቿንም ይበትናል።

2ነገሩ ሁሉ አንድ ዐይነት ይሆናል፤

በሕዝቡ ላይ የሚሆነው በካህኑ፣

በአገልጋዩ ላይ የሚሆነው በጌታው፣

በአገልጋይዋ ላይ የሚሆነው በእመቤቷ፣

በገዥው ላይ የሚሆነው በሻጩ፣

በተበዳሪው ላይ የሚሆነው በአበዳሪው፣

በብድር ከፋይ ላይ የሚሆነው በብድር ሰጪው ይሆናል።

3ምድር ፈጽሞ ባድማ ትሆናለች፤

ጨርሶም ትበዘበዛለች፤

እግዚአብሔር ይህን ቃል ተናግሯልና።

4ምድር ትደርቃለች፤ ትረግፋለች፤

ዓለም ትዝላለች፤ ትረግፋለች፤

የምድርም መሳፍንት ይዝላሉ።

5ምድር በሕዝቧ ትረክሳለች፤

ሕግን ጥሰዋል፤

ሥርዐትን ተላልፈዋል፤

ዘላለማዊውንም ኪዳን አፍርሰዋል።

6ስለዚህ ርግማን ምድርን ትበላለች፤

ሕዝቦቿም ስለ በደላቸው ይቀጣሉ፤

ስለዚህ የምድር ነዋሪዎች ተቃጥለዋል፤

በጣም ጥቂት የሆኑት ቀርተዋል።

7አዲሱ የወይን ጠጅ ዐለቀ፤ የወይኑም ተክል ደረቀ፤

ደስተኞችም ሁሉ አቃሰቱ።

8የከበሮ ደስታ ጸጥ አለ፤

የጨፋሪዎች ጩኸት አበቃ፤

ደስ የሚያሰኘውም በገና እረጭ አለ።

9ከእንግዲህ እየዘፈኑ የወይን ጠጅ አይጠጡም፤

መጠጡም ለሚጠጡት ይመርራል።

10የፈራረሰችው ከተማ ባድማ ሆነች፤

የየቤቱም መግቢያ ተዘጋ።

11በየአደባባዩ የወይን ጠጅ ያለህ እያሉ ይጮኻሉ፤

ደስታው ሁሉ ወደ ሐዘን ይለወጣል፤

ሐሤቱም ሁሉ ከምድር ገጽ ጠፍቷል።

12ከተማዪቱ ፈጽማ ፈርሳለች፤

በሮቿም ደቅቀው ወድቀዋል።

13የወይራ ዛፍ ሲመታ፣

የወይንም ዘለላ ሲቈረጥ ቃርሚያ እንደሚቀር ሁሉ፣

በምድሪቱ ላይ፣

በሕዝቦችም ላይ እንዲሁ ይሆናል።

14ድምፃቸውን ከፍ ያደርጋሉ፤ በደስታም ይጮኻሉ፤

ከምዕራብም የእግዚአብሔርን ክብር ያስተጋባሉ።

15ስለዚህ በምሥራቅ ለእግዚአብሔር ክብር ስጡ፤

ከባሕር ደሴቶችም፣

የእስራኤልን አምላክ፣ የእግዚአብሔርን ስም ከፍ ከፍ አድርጉ።

16“ለጻድቁ ክብር ይሁን” የሚል ዝማሬ፣

ከምድር ዳርቻ ሰማን፤

እኔ ግን፣ “ከሳሁ፤ መነመንሁ፤

ወዮልኝ!

ከዳተኞች አሳልፈው ሰጡ፤

ከዳተኞች በክሕደታቸው አሳልፈው ሰጡ” አልሁ።

17በምድር የምትኖር ሕዝብ ሆይ፤

ሽብር፣ ጕድጓድና ወጥመድ ይጠብቁሃል።

18ከሽብር ድምፅ የሚሸሽ፣

ወደ ጕድጓድ ይገባል፤

ከጕድጓድ የወጣም፣

በወጥመድ ይያዛል።

የሰማይ መስኮቶች ተከፍተዋልና፤

የምድርም መሠረት ተናወጠ።

19ምድር ተከፈለች፤

ምድር ተሰነጠቀች፤

ምድር ፈጽማ ተናወጠች።

20ምድር እንደ ሰካራም ዞረባት፤

ነፋስ እንደሚወዘውዘውም ጐጆ ሆነች፣

የዐመፅዋ ሸክም ከባድ ስለሆነ ትወድቃለች፤

እንደ ገናም አትነሣም።

21በዚያ ቀን እግዚአብሔር

በላይ በሰማያት ያሉትን ኀይሎች፣

በታችም በምድር ያሉትን ነገሥታት ይቀጣቸዋል።

22በጕድጓድ ውስጥ እንዳሉ እስረኞች፣

በአንድ ላይ ይታጐራሉ፤

በእስር ቤት ይዘጋባቸዋል24፥22 ወይም፣ ይላቀቃሉ

ከብዙ ቀንም በኋላ ለፍርድ ይቀርባሉ።

23የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር

በጽዮን ተራራና በኢየሩሳሌም፣

በሽማግሌዎቹም ፊት በክብሩ ይነግሣል፤

ጨረቃ ትሸማቀቃለች፤ ፀሓይም ታፍራለች።

Japanese Contemporary Bible

イザヤ書 24:1-23

24

ユダが荒地となる

1主は地をくつがえし、

広大な荒れ地にしようとしています。

全国民を地上のあちこちに追い散らします。

2祭司も一般の民も、召使も主人も、

女奴隷も女主人も、売り手も買い手も、

貸す者も借りる者も、銀行家も債務者も、

一人として免れることはできません。

3地は完全にすたれ、

いっさいのものが略奪されます。

主がそれを語りました。

4-5国は民の罪のために苦しみ、地はやせ衰え、

作物はしおれ、空は雨を降らせません。

国は犯罪によって汚れました。

住民が神のおきてに背き、

神の永遠の命令を破ったからです。

6そのため神ののろいが下り、

人々は心がすさみ、日照りで死に絶えます。

生き残る者は数えるほどしかいません。

7人生の喜びは去り、

ぶどうは収穫期になっても実らず、

ぶどう酒は底をつきます。

陽気だった人も顔をくもらせ、

うなだれます。

8竪琴やタンバリンの陽気な音は二度と聞かれません。

楽しかった時代は終わりました。

9ぶどう酒を飲みながら歌う喜びはなくなり、

強い酒を飲んでも、口の中が苦くなるばかりです。

10町は無法地帯も同然で、

どの家も店も戸締まりを厳重にし、

略奪されないようにと神経をとがらせます。

11暴徒は群れをなし、

「酒をくれ」とわめきます。

喜びは失われ、楽しみは忘れ去られました。

12町は荒れ放題、

城門は無残な姿をさらすばかりです。

13国中どこでも、わずかな生存者しかいません。

14しかし、残った者は大喜びで歌います。

西に住む者が神の偉大さをたたえれば、

15-16東に住む者も、喜んで声を合わせます。

地の果てから主をほめ歌い、

正義の神の誉れをたたえる声に耳をすましなさい。

ああ、それなのに、

私の心は憂いのために重く沈んでいます。

悪は依然としてはびこり、

裏切り行為が至るところで見られます。

17全世界の人々よ。

あなたがたが恐怖の地獄へ引かれて行く運命に

変わりはありません。

18恐ろしくなって逃げようとすると、

穴に落ち込みます。

やっとの思いで穴からはい出せば、

今度は罠にかかります。

天から滅びが降ってくるので、

足の下で大地は揺れ動きます。

19地はずたずたに裂け、

何もかも原形をとどめないほどになり、

足の踏み場もなくなります。

20世界中が酔った者のようにふらつき、

嵐に会ったテントのように揺れ動きます。

あまりの罪の大きさに耐えきれず、

世界は倒れて、二度と起き上がれません。

21その日、主は天上の堕落した天使を罰し、

地上の国々の高慢な支配者に罰を加えます。

22彼らは囚人のように駆り集められ、

刑の執行の時まで地下牢に閉じ込められます。

23ついに天の軍勢の主はシオンの御座に上り、

イスラエルの長老たちの見ている前で、

エルサレムを中心に世を治めます。

その栄光は、太陽の輝きも月のうるわしさも、

色あせてしまうほどです。