ኢሳይያስ 12 – NASV & NUB

New Amharic Standard Version

ኢሳይያስ 12:1-6

የውዳሴ መዝሙር

1በዚያን ቀን እንዲህ ትላለህ፤

እግዚአብሔር ሆይ፤

ቀድሞ ተቈጥተኸኝ ነበር፤

አሁን ግን ከቍጣህ ተመለስህ፤

ደግሞም አጽናንተኸኛልና አወድስሃለሁ።

2እነሆ፣ እግዚአብሔር ድነቴ ነው፤

እታመናለሁ፣ ደግሞም አልፈራም፤

12፥2 እግዚአብሔር በሚለው ስም ፈንታ ተተክቶ የገባ ነው። ጌታ እግዚአብሔር ብርታቴና ዝማሬዬ ነው፤

ድነቴም ሆኗል።”

3ከድነቴ ምንጮች

ውሃ በደስታ ትቀዳላችሁ።

4በዚያን ቀን እንዲህ ትላላችሁ፤

እግዚአብሔርን አመስግኑ፤ ስሙንም ጥሩ፤

ያደረገውንም በአሕዛብ መካከል አስታውቁ፤

ስሙ ከፍ ከፍ ማለቱንም ዐውጁ።

5ለእግዚአብሔር ዘምሩ፤ ታላቅ ሥራ ሠርቷልና፤

ይህም ለዓለም ሁሉ ይታወቅ።

6የጽዮን ሕዝብ ሆይ፤ እልል በሉ፤

በደስታም ዘምሩ፤

በመካከላችሁ ያለው የእስራኤል ቅዱስ ታላቅ ነውና።”

Swedish Contemporary Bible

Jesaja 12:1-6

Lovsång till Herren

1Den dagen ska du säga:

”Jag prisar dig, Herren!

Du var vred på mig,

men din vrede är över,

och nu har du tröstat mig.

2Ja, Gud är min räddning,

jag är trygg och inte rädd,

för Herren är min starkhet och min sång.

Han har blivit min räddning.

3Med glädje ska ni ösa vatten

ur räddningens källor.”

4Den dagen ska ni säga:

”Prisa Herren,

åkalla honom!

Gör hans gärningar kända bland folken,

förkunna hans upphöjda namn.

5Sjung till Herrens ära,

för det härliga han har gjort,

låt det bli känt över hela jorden.

6Ropa och sjung av glädje,

ni som bor på Sion,

för stor är han som bor mitt ibland er,

Israels Helige.”