አስቴር 7 – NASV & BPH

New Amharic Standard Version

አስቴር 7:1-10

ሐማ ተሰቀለ

1ስለዚህ ንጉሡና ሐማ ከንግሥት አስቴር ጋር ለመጋበዝ ሄዱ፤ 2በሁለተኛውም ቀን የወይን ጠጅ እየጠጡ ሳለ፣ ንጉሡ እንደ ገና፣ “ንግሥት አስቴር ሆይ፤ የምትለምኚው ምንድን ነው? ይሰጥሻል፤ የምትጠይቂውስ ምንድን ነው? እስከ መንግሥቴ እኩሌታ እንኳ ቢሆን ይደረግልሻል” አላት።

3ከዚያም ንግሥት አስቴር እንዲህ ስትል መለሰች፤ “ንጉሥ ሆይ፤ በፊትህ ሞገስ አግኝቼና ግርማዊነትህን ደስ የሚያሰኝ ከሆነ፣ ሕይወቴን ታደጋት፤ ልመናዬ ይህ ነው፤ ሕዝቤን አትርፍ፤ ጥያቄዬም ይኸው ነው። 4እኔና ሕዝቤ ለጥፋት፣ ለዕርድና ለመደምሰስ ተሸጠናልና። ወንዶችና ሴቶች ባሮች ለመሆን የተሸጥን ቢሆን ኖሮ፣ ዝም ባልሁ ነበር፤ ምክንያቱም እንዲህ ያለው ጭንቀት ንጉሡን ለማስቸገር የሚበቃ አይደለም7፥4 ወይም፣ ዝም ባልሁም ነበር፤ ነገር ግን ባለጋራችን የሚሰጠው ካሣ ንጉሡ ከሚያጣው ነገር ጋር ከቶ አይነጻጸርም።”

5ንጉሥ ጠረክሲስም ንግሥት አስቴርን፣ “ለመሆኑ እርሱ ማን ነው? እንዲህ ያለውን ነገር ለማድረግ እስከዚህ የደፈረውስ ሰው የታለ?” ሲል ጠየቀ።

6አስቴርም፣ “ያ ባላጋራና ጠላት ይህ ክፉው ሐማ ነው” አለች።

ከዚያም ሐማ በንጉሡና በንግሥቲቱ ፊት እጅግ ደነገጠ። 7ንጉሡ ከተቀመጠበት በቍጣ ተነሣ፤ የወይን ጠጁንም ትቶ ወደ ቤተ መንግሥቱ የአትክልት ቦታ ሄደ። ሐማ ግን ንጉሡ ሊያጠፋው ቈርጦ መነሣቱን ስላወቀ፣ ንግሥት አስቴር ሕይወቱን እንድታተርፍለት ለመማጠን በዚያው ቀረ።

8ንጉሡ ከቤተ መንግሥቱ የአትክልት ቦታ ወደ ግብዣው አዳራሽ ሲመለስ አስቴር ደገፍ ባለችበት ድንክ ዐልጋ ላይ ሐማ ተደፍቶ ነበር።

ንጉሡም፣ “ይባስ ብሎ አብራኝ ያለችውን ንግሥት በገዛ ቤቴ ሊደፍራት ያስባልን?” ሲል ተናገረ።

ይህ ቃል ከንጉሡ አፍ ገና እንደ ወጣ፣ የሐማን ፊት ሸፈኑት። 9ከዚያም ንጉሡን በቅርብ ከሚያገለግሉት ጃንደረቦች አንዱ የሆነው ሐርቦና፣ “እነሆ ቁመቱ አምሳ ክንድ7፥9 23 ሜትር ያህል ነው። የሆነ ግንድ በሐማ ቤት አጠገብ ተተክሏል፤ ይህን ያዘጋጀው ንጉሡን ለማዳን በጎ ነገር ለተናገረው ለመርዶክዮስ ነው” አለ።

ንጉሡም፣ “በዚሁ ላይ ስቀሉት” አለ። 10ስለዚህ ለመርዶክዮስ ባዘጋጀው ግንድ ላይ ሐማን ሰቀሉት፤ ከዚያም የንጉሡ ቍጣ በረደ።

Bibelen på hverdagsdansk

Esters Bog 7:1-10

Hamans endeligt

1Om aftenen sad kongen og Haman endnu en gang til fest hos dronning Ester. 2Mens de drak af vinen, spurgte kongen igen: „Hvad har du på hjerte, dronning Ester? Fortæl mig nu, hvad du ønsker. Jeg giver dig det, om det så er det halve kongerige!”

3Da svarede dronning Ester: „Hvis jeg har fundet nåde for Deres øjne, herre konge, beder jeg om, at De vil skåne mit eget og mine landsmænds liv. 4Det er blevet besluttet, at jeg og mit folk skal udryddes fuldstændigt. Hvis vi var blevet solgt som slaver, ville jeg ikke have ulejliget kongen af den grund, men total udryddelse er en anden sag.”

5„Hvad mener du?” spurgte kong Xerxes. „Hvem er det, der har besluttet at udrydde jer?”

6„Det er en fjende af jøderne, den onde Haman der!” svarede Ester.

Haman blev ligbleg og rystede af skræk. 7Kongen sprang op i vrede og gik ud i parken, mens Haman blev tilbage for at bønfalde dronning Ester om nåde, for han vidste, hvad kongens vrede betød. 8I sin fortvivlelse knælede Haman ned over divanen, som Ester lå på, netop som kongen vendte tilbage fra haven.

„Hvad i alverden!” råbte kongen. „Overfalder han dronningen for øjnene af mig i mit eget palads?” Straks sprang tjenerne til, overmandede Haman og tildækkede hans ansigt.

9Den tjener, der hed Harbona, sagde til kongen: „Herre, Haman har netop opstillet en høj galge, som var tænkt til Mordokaj, kongens redningsmand. Den står parat i Hamans gård.”

„Så hæng ham selv i den!” beordrede kongen. 10Så hængte de Haman i den galge, han havde tænkt til Mordokaj, og kongens vrede lagde sig.