አስቴር 3 – NASV & CCBT

New Amharic Standard Version

አስቴር 3:1-15

ሐማ አይሁድን ለማጥፋት የሸረበው ሤራ

1ከዚህም ነገር በኋላ ንጉሥ ጠረክሲስ የአጋጋዊውን የሐመዳቱን ልጅ ሐማን ከፍ ከፍ አደረገው፤ ከሌሎቹም መኳንንት ሁሉ ከፍተኛውን ሥልጣን በመስጠት አከበረው። 2ንጉሡ ስለ እርሱ ይህ እንዲደረግለት አዝዞ ስለ ነበር፣ በንጉሡ በር ያሉት የመንግሥቱ ሹማምት ሁሉ ለሐማ ተንበርክከው እጅ በመንሣት አክብሮታቸውን ይገልጡለት ነበር። መርዶክዮስ ግን ወድቆ አልሰገደለትም፤ አክብሮትም አላሳየውም።

3ታዲያ በንጉሡ በር ያሉት የንጉሡ አገልጋዮች መርዶክዮስን፣ “የንጉሡን ትእዛዝ ለምን ትተላለፋለህ?” ሲሉ ጠየቁት። 4ይህንም በየቀኑ ይነግሩት ነበር፤ እርሱ ግን አልተቀበላቸውም። አይሁዳዊ መሆኑን ነግሯቸው ስለ ነበር፣ የመርዶክዮስ ባሕርይ እስከ መቼ ሊቀጥል እንደሚችል ለማየት ሲሉ ይህንኑ ለሐማ ነገሩት።

5ሐማም መርዶክዮስ ወድቆ እንዳልሰገደለትና እንዳላከበረው ሲያይ እጅግ ተቈጣ። 6ይልቁንም መርዶክዮስ ከእነማን ወገን መሆኑን በተረዳ ጊዜ፣ መርዶክዮስን ብቻ መግደል እንደ ኢምንት ቈጠረው፤ ስለዚህ ሐማ በመላው የጠረክሲስ መንግሥት ውስጥ የሚገኙትንና የመርዶክዮስ ወገን የሆኑትን አይሁድ ሁሉ ለማጥፋት ዘዴ ፈለገ።

7ንጉሥ ጠረክሲስ በነገሠ በዐሥራ ሁለተኛው ዓመት ኒሳን በተባለው በመጀመሪያው ወር፣ ቀኑንና ወሩን ለመለየት ፉር የተባለ ዕጣ ሐማ ባለበት ጣሉ፤ ዕጣውም አዳር በተባለው በዐሥራ ሁለተኛው ወር ላይ ወደቀ።

8ከዚያም ሐማ ንጉሥ ጠረክሲስን እንዲህ አለው፤ “በአሕዛብ መካከል በመንግሥትህ አውራጃዎች ሁሉ ተሠራጭቶና ተበታትኖ የሚኖር አንድ ሕዝብ አለ፤ ይህም ሕዝብ ከሌሎች ሕዝቦች ሁሉ የተለየ ልማድ ያለውና የንጉሡንም ሕግ የማይታዘዝ ነው፤ ታዲያ ይህን ሕዝብ ዝም ማለቱ ለንጉሡ አይበጅም። 9ነገሩ ንጉሡን ደስ የሚያሰኘው ከሆነ፣ እነርሱን ለማጥፋት ዐዋጅ ይውጣ፤ እኔም ይህን ተግባር ለሚፈጽሙ ሰዎች የሚውል ዐሥር ሺሕ መክሊት ብር ወደ መንግሥት ግምጃ ቤት አስገባለሁ።”

10ስለዚህ ንጉሡ የቀለበት ማኅተሙን ከጣቱ አውልቆ የአይሁድ ጠላት ለሆነው ለአጋጋዊው ለሐማዳቱ ልጅ ለሐማ ሰጠው። 11ንጉሡም ሐማን፣ “ገንዘቡን እዚያው ያዘው፤ ሕዝቡንም እንዳሻህ አድርገው” አለው።

12ከዚያም በመጀመሪያው ወር ዐሥራ ሦስተኛው ቀን የንጉሡ ጸሓፊዎች ተጠሩ። እነርሱም የሐማን ትእዛዝ በሙሉ በየአውራጃው ፊደልና በየሕዝቡ ቋንቋ፣ ለንጉሡ እንደራሴዎች፣ ለልዩ ልዩ አውራጃ ገዦችና ለልዩ ልዩ ሕዝቦች መኳንንት ጻፉ። ይህም የተጻፈው በራሱ በንጉሡ ጠረክሲስ ስም ሲሆን፣ የታተመውም በራሱ ማኅተም ነበር። 13አዳር በተባለው በዐሥራ ሁለተኛው ወር፣ በዐሥራ ሦስተኛው ቀን ወጣት፣ ሽማግሌ፣ ሴትና ሕፃን ሳይባል አይሁድ ሁሉ በዚያኑ ዕለት እንዲጠፉ፣ እንዲገደሉና እንዲደመሰሱ፣ ሀብታቸውም እንዲዘረፍ ደብዳቤ ለንጉሡ አውራጃዎች ሁሉ በመልእክተኞች እጅ ተላከ። 14ለእያንዳንዱም አውራጃ ሕዝብ እንዲታወቅ፣ እነርሱም ለዚያ ቀን ዝግጁ እንዲሆኑ፣ የዋናው ዐዋጅ ቅጅ ሕግ እንዲወጣና ወደ እያንዳንዱም አውራጃ እንዲላክ ተደረገ።

15መልእክተኞቹ በንጉሡ ትእዛዝ ተቻኵለው ወጡ፤ ዐዋጁም በሱሳ ግንብ ተላለፈ። ንጉሡና ሐማ ለመጠጣት ተቀመጡ፤ የሱሳ ከተማ ግን ግራ ተጋብታ ነበር።

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

以斯帖記 3:1-15

哈曼圖謀滅絕猶太人

1後來,亞哈隨魯王擢升亞甲哈米大他的兒子哈曼,使他的權位高過他所有的同僚。 2王命令所有在宮門供職的臣僕都要向哈曼跪拜,但末底改不肯跪拜。 3在宮門供職的臣僕問末底改:「你為何違抗王的命令?」 4他們天天勸他,他卻不聽。他們便把這件事告訴哈曼,想看看末底改這樣做是否能站得住,因為末底改已告訴他們自己是猶太人。 5哈曼末底改不肯向他跪拜,就怒氣填胸。 6他得知末底改猶太人後,便不屑於只害末底改一人,而是要剷除亞哈隨魯王國內所有的猶太人,即末底改的同胞。

7亞哈隨魯王十二年一月,即尼散月,有人在哈曼面前抽普珥,也就是抽籤,來決定哪月哪日下手,結果抽中十二月,即亞達月。

8哈曼亞哈隨魯王說:「有一個民族散居在王境內各省的眾民族中,他們的律例與各族的律例不同,他們不遵守王的律例,所以容忍他們對王不利。 9王若願意,就請降旨消滅他們。我願捐三百四十五噸銀子交給管理國事的人,納入王的庫房。」 10於是,王摘下手上的戒指,交給猶太人的仇敵——亞甲哈米大他的兒子哈曼11對他說:「這些銀子歸你,這個民族也交給你,隨你處置。」

12一月十三日,王的書記被召來,他們以亞哈隨魯王的名義,照哈曼的吩咐,用各省的文字和各族的語言寫諭旨,用王的戒指蓋印,送交各總督、各省省長和各族首領。 13諭旨由信差送到王的各省,限令在一天之內,即十二月,也就是亞達月十三日,把猶太人的男女老少全部剷除、殺光、滅盡,並奪取他們的財物。 14諭旨的抄本作為法令頒佈到各省,通知各族為那天做好準備。 15信差奉王的命令急忙上路,諭旨也在書珊城裡頒佈了。王和哈曼坐下飲酒,書珊城一片慌亂。