አሞጽ 9 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

አሞጽ 9:1-15

እስራኤል ትጠፋለች

1ጌታን በመሠዊያው አጠገብ ቆሞ አየሁት፤ እርሱም እንዲህ አለ፤

“መድረኮቹ እንዲናወጡ፣

ጕልላቶቹን ምታ፤

በሕዝቡም ሁሉ ራስ ላይ ሰባብራቸው፤

የቀሩትን በሰይፍ እገድላቸዋለሁ፤

ከእነርሱ አንድም ሰው አይሸሽም፤

ቢሸሽም የሚያመልጥ የለም።

2መቃብር9፥2 ዕብራይስጡ ሲዖል ይለዋል። በጥልቀት ቈፍረው ቢወርዱም፣

እጄ ከዚያ ታወጣቸዋለች፤

ወደ ሰማይ ቢወጡም፣

ከዚያ አወርዳቸዋለሁ።

3በቀርሜሎስ ጫፍ ላይ ቢሸሸጉም፣

ዐድኜ፣ ፈልጌ ከዚያ አወርዳቸዋለሁ፤

እይዛቸዋለሁም።

በጥልቅ ባሕር ውስጥ ከእኔ ቢሸሸጉም፣

በዚያ እባቡ እንዲነድፋቸው አዝዘዋለሁ፤

4በጠላቶቻቸው ተነድተው ለምርኮ ቢወሰዱም፣

በዚያ እንዲገድላቸው ሰይፍን አዝዛለሁ፤

“ለመልካም ሳይሆን ለክፉ፣

ዐይኔን በእነርሱ ላይ አደርጋለሁ።”

5ጌታ፣ እግዚአብሔር ጸባኦት፣

ምድርን ይዳስሳል፤

እርሷም ትቀልጣለች፤

በውስጧ የሚኖሩ ሁሉ ያለቅሳሉ፤

የምድር ሁለመና እንደ አባይ ወንዝ ይነሣል፤

እንደ ግብፅ ወንዝም ይወርዳል።

6መኖሪያውን9፥6 ዕብራይስጡ ለዚህ ሐረግ የሰጠው ትርጕም ምን እንደ ሆነ አይታወቅም። በሰማይ የሚሠራ፣

መሠረቱንም9፥6 ዕብራይስጡ ለዚህ ሐረግ የሰጠው ትርጕም ምን እንደ ሆነ አይታወቅም። በምድር የሚያደርግ፣

የባሕርን ውሃ የሚጠራ፣

በምድርም ገጽ ላይ የሚያፈስስ፣

እርሱ ስሙ እግዚአብሔር ነው።

7“እናንት እስራኤላውያን፣

ለእኔ እንደ ኢትዮጵያውያን አይደላችሁምን?”

ይላል እግዚአብሔር

“እስራኤልን ከግብፅ፣

ፍልስጥኤማውያንን ከከፍቶር9፥7 በላይኛው አባይ አካባቢ ያለ ሕዝብ ነው።

ሶርያውያንንም ከቂር አላወጣሁምን?

8“እነሆ፤ የጌታ እግዚአብሔር ዐይኖች፣

በኀጢአተኛ መንግሥት ላይ ናቸው፤

ከምድር ገጽ፣ ፈጽሜ አጠፋዋለሁ፤

የያዕቆብን ቤት ግን፣ ሙሉ በሙሉ

አልደመስስም፤”

ይላል እግዚአብሔር

9“እነሆ፤ ትእዛዝ እሰጣለሁ፤

እህል በወንፊት እንደሚነፋ፣

የእስራኤልን ቤት፣

በሕዝብ ሁሉ መካከል እንዲሁ አደርጋለሁ፤

ነገር ግን አንዲት ቅንጣት በምድር ላይ አትወድቅም።

10በሕዝቤ መካከል ያሉ፣

‘ክፉ ነገር አያገኘንም ወይም አይደርስብንም’ የሚሉ፣

ኀጢአተኞች ሁሉ፣

በሰይፍ ይሞታሉ።

የእስራኤል መመለስ

11“በዚያ ቀን፣

“የወደቀውን የዳዊትን ድንኳን አነሣለሁ፤

የተሰበረውን እጠግናለሁ፤

የፈረሰውን ዐድሳለሁ፤

ቀድሞ እንደ ነበረም አድርጌ እሠራዋለሁ፤

12ስለዚህ የኤዶምን ትሩፍ፣

በስሜ9፥12 ዕብራይስጡ እንደ ሰብዓ ሊቃናቱ ትርጕም የሕዝቡ ትሩፋንና ስሜን የሚሸከሙ ሁሉ፣ እኔን ይፈልጋሉ የተጠሩትንም ሕዝቦች ሁሉ ይወርሳሉ፤”

ይላል ይህን የሚያደርግ እግዚአብሔር

13እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“እነሆ፤ ዐጫጁ ዐጭዶ ሳይጨርስ፣

ዐራሹ በላዩ የሚደርስበት፣

ችግኝ ተካዩም ገና ተክሎ ሳይጨርስ፣

ወይን ጨማቂው የሚደርስበት ጊዜ ይመጣል፤

አዲስ የወይን ጠጅ ከተራሮች ይንጠባጠባል፤

ከኰረብቶችም ሁሉ ይፈስሳል።

14የተሰደደውን9፥14 ወይም ዕጣ ፈንታቸውን አድሳለሁ ሕዝቤን እስራኤልን እመልሳለሁ።

“እነርሱም የፈራረሱትን ከተሞች መልሰው ሠርተው በውስጣቸው ይኖራሉ።

የወይን ተክል ተክለው፣ ጠጁን ይጠጣሉ፤

አትክልት ተክለው ፍሬውን ይበላሉ።

15እስራኤልን በገዛ ምድራቸው እተክላቸዋለሁ፤

ከሰጠኋቸውም ምድር፣

ዳግመኛ አይነቀሉም፤”

ይላል አምላክህ እግዚአብሔር

Thai New Contemporary Bible

อาโมส 9:1-15

อิสราเอลจะถูกทำลาย

1ข้าพเจ้าเห็นองค์พระผู้เป็นเจ้าประทับยืนอยู่ข้างแท่นบูชา และพระองค์ตรัสว่า

“จงฟาดยอดเสา

เพื่อให้ธรณีประตูสั่นสะเทือน

ให้พังทับประชาชนทั้งปวง

ผู้ที่เหลือรอดเราจะประหารด้วยดาบ

จะไม่มีใครหนีรอดไปได้สักคนเดียว

จะไม่มีใครหนีไปได้เลย

2แม้พวกเขาจะขุดลึกลงไปถึงก้นหลุมฝังศพ

มือของเราก็จะควานลงไปดึงขึ้นมา

แม้พวกเขาปีนขึ้นถึงฟ้าสวรรค์

เราก็จะนำพวกเขาลงมา

3แม้พวกเขาซ่อนตัวบนยอดเขาคารเมล

เราก็จะตามล่าจับพวกเขาลงมาจากที่นั่น

แม้พวกเขาหนีไปซ่อนที่ก้นทะเล

เราก็จะสั่งงูพิษให้กัดพวกเขา

4แม้พวกเขาถูกศัตรูกวาดต้อนไปเป็นเชลย

เราก็จะสั่งให้ดาบประหารพวกเขาที่นั่น

เราจะจับตาดูพวกเขาอย่างมุ่งร้าย

ไม่ใช่ด้วยหวังดี”

5องค์พระผู้เป็นเจ้า พระยาห์เวห์ผู้ทรงฤทธิ์

ผู้ทรงแตะโลกแล้ว มันก็หลอมละลาย

และชาวโลกทั้งปวงก็ไว้ทุกข์

ทั่วทั้งดินแดนเอ่อท้นขึ้นเหมือนแม่น้ำไนล์

แล้วก็จมลงเหมือนแม่น้ำอียิปต์

6พระองค์ผู้ทรงสร้างที่ประทับอันสูงส่ง9:6 ในภาษาฮีบรูวลีนี้มีความหมายไม่ชัดเจนไว้ในฟ้าสวรรค์

และวางฐานราก9:6 ในภาษาฮีบรูคำนี้มีความหมายไม่ชัดเจนของมันไว้ที่แผ่นดินโลก

ผู้ทรงเรียกน้ำทะเลขึ้นมา

และเทมันรดผิวโลก

ทรงพระนามว่าพระยาห์เวห์

7“อิสราเอลเอ๋ย สำหรับเราแล้ว

เจ้าก็ไม่ได้แตกต่างอะไรจากชาวคูช9:7 คือผู้คนจากตอนบนของลุ่มแม่น้ำไนล์ไม่ใช่หรือ?”

องค์พระผู้เป็นเจ้าประกาศดังนั้น

“เราไม่ได้นำอิสราเอลออกมาจากอียิปต์

นำชาวฟีลิสเตียออกจากคัฟโทร์9:7 คือเกาะครีต

และนำชาวอารัมออกจากคีร์หรอกหรือ?”

8“แน่นอน พระยาห์เวห์องค์เจ้าชีวิต

ทรงจับตาดูอาณาจักรอันบาปหนา

เราจะทำลายมัน

จากพื้นโลก

ถึงกระนั้นเราจะไม่ทำลายพงศ์พันธุ์ยาโคบ

ลงอย่างสิ้นเชิง”

องค์พระผู้เป็นเจ้าประกาศดังนั้น

9“เพราะเราจะออกคำสั่ง

และเราจะเขย่าพงศ์พันธุ์อิสราเอล

ท่ามกลางมวลประชาชาติ

เหมือนเขย่ากระด้งฝัดข้าว

แต่จะไม่มีสักเมล็ดเดียวตกถึงพื้น

10บรรดาคนบาปในหมู่ประชากรของเรา

จะตายด้วยคมดาบ

คือคนทั้งปวงที่พูดว่า

‘ภัยพิบัติจะไม่มาเล่นงานเราหรือมาถึงเรา’

อิสราเอลคืนสู่สภาพดี

11“ในวันนั้นเราจะตั้งเต็นท์ของดาวิด

“ที่ล้มลงแล้วขึ้นมาใหม่

เราจะซ่อมแซมสถานที่ที่พังทลายลง

และปฏิสังขรณ์ซากปรักหักพัง

และสร้างมันขึ้นเหมือนอย่างแต่ก่อน

12เพื่อพวกเขาจะครอบครองชนหยิบมือที่เหลืออยู่ของเอโดม

และครอบครองประชาชาติทั้งปวงที่ได้ชื่อตามนามของเรา9:12 ฉบับLXX. ว่าเพื่อคนหยิบมือที่เหลืออยู่ / และทุกชาติที่ได้ชื่อตามนามของเราจะได้แสวงหาองค์พระผู้เป็นเจ้า

องค์พระผู้เป็นเจ้าผู้จะทรงกระทำสิ่งเหล่านี้

ประกาศดังนั้น

13องค์พระผู้เป็นเจ้าประกาศว่า

“วันเวลาจะมาถึงเมื่อคนที่ไถจะตามทันคนที่เกี่ยว

และคนย่ำองุ่นจะตามทันคนที่ปลูก

จะมีเหล้าองุ่นใหม่หยดจากภูเขา

และไหลจากเนินเขาทั้งปวง

14เราจะนำอิสราเอลประชากรของเราซึ่งตกเป็นเชลยนั้นกลับคืนมา9:14 หรือเราจะให้อิสราเอลประชากรของเรากลับสู่สภาพดี

พวกเขาจะสร้างเมืองต่างๆ ที่ปรักหักพังขึ้นใหม่ แล้วเข้าอยู่อาศัย

พวกเขาจะทำสวนองุ่นและดื่มเหล้าองุ่น

พวกเขาจะทำสวนและกินผลผลิต

15เราจะปลูกอิสราเอลไว้ในดินแดนของพวกเขาเอง

พวกเขาจะไม่ถูกถอนรากถอนโคน

ออกจากดินแดนที่เรามอบให้พวกเขาอีกเลย”

องค์พระผู้เป็นเจ้าพระเจ้าของเจ้าตรัสดังนั้น