አሞጽ 5 – NASV & CCB

New Amharic Standard Version

አሞጽ 5:1-27

የእስራኤል ሕዝብ ለንስሓ መጠራት

1የእስራኤል ቤት ሆይ፤ ስለ እናንተ የምደረድረውን ይህን የሙሾ ቃል ስሙ፤

2“ድንግሊቱ እስራኤል ወደቀች፤

ከእንግዲህም አትነሣም፤

በገዛ ምድሯ ተጣለች፤

የሚያነሣትም የለም።”

3ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“አንድ ሺሕ ብርቱዎችን ለእስራኤል የምታዘምት ከተማ፣

አንድ መቶ ብቻ ይቀሯታል፤

አንድ መቶ ብርቱዎችን የምታዘምተውም፣

ዐሥር ብቻ ይቀሯታል።”

4እግዚአብሔር ለእስራኤል ቤት እንዲህ ይላል፤

“እኔን ፈልጉ፤ በሕይወትም ትኖራላችሁ።”

5ቤቴልን አትፈልጉ፤

ወደ ጌልገላ አትሂዱ፤

ወደ ቤርሳቤህም አትሻገሩ፤

ጌልገላ በርግጥ ትማረካለች፤

ቤቴልም እንዳልነበረች5፥5 ሐዘን ትሆናለችና።

6እግዚአብሔርን ፈልጉ፤

በሕይወትም ትኖራላችሁ፤

አለዚያ እንደ እሳት የዮሴፍን ቤት ያወድማል፤

እሳቱም ቤቴልን ይበላል፤ የሚያጠፋውም የለም።

7እናንት ፍትሕን ወደ መራርነት የምትለውጡ፣

ጽድቅንም ወደ ምድር የምትጥሉ ወዮላችሁ!

8ሰባቱን ከዋክብትና ኦሪዮንን የሠራ፣

ጨለማውን ወደ ንጋት ብርሃን የሚለውጥ፣

ቀኑን አጨልሞ ሌሊት የሚያደርግ፣

የባሕሩንም ውሃ ጠርቶ፣

በገጸ ምድር ላይ የሚያፈስስ፣

ስሙ እግዚአብሔር ነው፤

9እርሱ በብርቱው ላይ ድንገተኛ ጥፋትን፣

በተመሸገውም ከተማ ላይ ውድመትን ያመጣል።

10እናንተ በፍርድ አደባባይ

የሚገሥጻችሁን ትጠላላችሁ፤ እውነት የሚናገረውንም ትንቃላችሁ።

11እናንተ ድኻውን ትረግጣላችሁ፤

እህል እንዲሰጣችሁም ታስገድዱታላችሁ፤

ስለዚህ በተጠረበ ድንጋይ ቤት ብትሠሩም፣

በውስጡ ግን አትኖሩም፤

ባማሩ የወይን ተክል ቦታዎች ወይን ብትተክሉም፣

የወይን ጠጁን ግን አትጠጡም፤

12ኀጢአታችሁ ምንኛ ታላቅ እንደ ሆነ፣

በደላችሁም የቱን ያህል እንደ በዛ እኔ ዐውቃለሁና።

ጻድቁን ትጨቍናላችሁ፤

ጕቦም ትቀበላላችሁ፤

በፍርድ አደባባይም ከድኻው ፍትሕ ትነጥቃላችሁ።

13ስለዚህ አስተዋይ ሰው በእንዲህ ያለ ጊዜ ዝም ይላል፤

ቀኖቹ ክፉዎች ናቸውና።

14በሕይወት ትኖሩ ዘንድ፣

መልካሙን እንጂ ክፉውን አትፈልጉ፤

ከዚያ በኋላ እንደ ተናገራችሁት፣

የሰራዊት አምላክ እግዚአብሔር ከእናንተ ጋር ይሆናል።

15ክፉውን ጥሉ፤ መልካሙንም ውደዱ፤

በፍርድ አደባባይም ፍትሕን አታጓድሉ፤

ምናልባትም የሰራዊት አምላክ እግዚአብሔር

ለዮሴፍ ትሩፍ ይራራ ይሆናል።

16ስለዚህ ጌታ የሰራዊት አምላክ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“በየመንገዱ ሁሉ ወየው ተብሎ ይለቀሳል፤

በአደባባዩም የሥቃይ ጩኸት ይሆናል፤

ገበሬዎች ለልቅሶ፣

አልቃሾችም ለዋይታ ይጠራሉ።

17በየወይኑ ዕርሻ ሁሉ ወየው ተብሎ ይለቀሳል፤

እኔ በመካከላችሁ ዐልፋለሁና፤”

ይላል እግዚአብሔር

የእግዚአብሔር ቀን

18የእግዚአብሔርን ቀን ለምትሹ፣

ለእናንተ ወዮላችሁ!

የእግዚአብሔርን ቀን ለምን ትሻላችሁ?

ያ ቀን ጨለማ ነው እንጂ ብርሃን አይደለም።

19ይህ ቀን አንድ ሰው ከአንበሳ ሲሸሽ፣

ድብ እንደሚያጋጥመው፣

ወደ ቤቱም ገብቶ፣ እጁን በግድግዳው

ላይ ሲያሳርፍ፣

እባብ እንደሚነድፈው ነው።

20የእግዚአብሔር ቀን ብርሃን ሳይሆን ጨለማ፣

የብርሃን ጸዳል የሌለው ድቅድቅ ጨለማ አይደለምን?

21“ዓመት በዓላችሁን ተጸይፌአለሁ፤

ጠልቼውማለሁ፤ ጉባኤዎቻችሁ ደስ አያሰኙኝም።

22የሚቃጠል መሥዋዕትና የእህል ቍርባን ብታቀርቡልኝም፣

እኔ አልቀበለውም፤

ከሠቡ እንስሶቻችሁ የኅብረት መሥዋዕት5፥22 የሰላም መሥዋዕት በመባል የሚታወቀው ነው። ብታቀርቡልኝም፣

እኔ አልመለከተውም።

23የዝማሬህን ጩኸት ከእኔ አርቅ፤

የበገናህንም ዜማ አልሰማም።

24ነገር ግን ፍትሕ እንደ ወንዝ፣

ጽድቅም እንደማይደርቅ ምንጭ ይፍሰስ።

25“የእስራኤል ቤት ሆይ፤ አርባ ዓመት በምድረ በዳ፣

መሥዋዕትንና ቍርባንን አቅርባችሁልኝ ነበርን?

26ለራሳችሁ የሠራችሁትን፣

የንጉሣችሁን ቤተ ጣዖት፣

የጣዖቶቻችሁን ዐምድ፣

የአምላካችሁን5፥26 ወይም ንጉሣችሁን ሱኮትን ከፍ ከፍ አደረጋችሁት እንዲሁም ጣዖታችሁን ቀይዋን የከዋክብት አማልክታችሁን፣ ሰብዓ ሊቃናት የሞሌክን ቤተ ጣዖት እንዲሁም የአምላካችሁን የሬፋንን ከዋክብት ከፍ አደረጋችሁ ይላሉ። ኮከብ አንሥታችሁ ተሸከማችሁ።

27ስለዚህ ከደማስቆ ወዲያ እንድትሰደዱ አደርጋችኋለሁ፤”

ይላል ስሙ የሰራዊት አምላክ የሆነ እግዚአብሔር

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

阿摩司书 5:1-27

劝以色列人悔改

1以色列家啊,

听我为你们唱哀歌:

2“处女以色列跌倒了,

再也站不起来;

她被遗弃在自己的土地上,

无人扶她起来。”

3因为主耶和华说:

以色列家的城邑中,

出兵一千的,只有百人生还;

出兵一百的,只有十人生还。”

4耶和华对以色列家说:

“你们要寻求我,才能存活。

5不要去伯特利求问,

不要进入吉甲

也不要前往别示巴

因为吉甲人必被掳去,

伯特利也必化为乌有。”

6你们要寻求耶和华,才能存活。

否则,祂要在约瑟5:6 约瑟家”此处指约瑟的子孙以法莲和玛拿西两个支派,圣经中有时用约瑟家代指北国以色列。如烈火爆发,

吞噬伯特利,无人能扑灭。

7你们这些使正义变为苦艾、将公义丢弃在地的人啊,

8那位造昴星和参星,

使幽暗变为黎明,

使白昼变为黑夜,

召来海水浇在大地上的——

祂的名字是耶和华。

9祂使毁灭如闪电临到强者,

摧毁他们的坚城。

10你们憎恨在城门口主持公道的人,

厌恶正直的人。

11你们践踏穷人,

对他们横征暴敛。

因此,你们用凿过的石头建房,

却不得居住在里面;

你们种植佳美的葡萄园,

却喝不到葡萄酒。

12我知道你们的过犯众多、罪恶无数。

你们迫害义人,收受贿赂,

在城门口冤枉穷人。

13这是邪恶的时代,

所以明智者静默不言。

14你们要弃恶从善,才能存活。

这样,万军之上帝耶和华必与你们同在,

正如你们所说的。

15你们要恨恶邪恶,喜爱良善,

在城门口伸张正义,

也许万军之上帝耶和华会恩待约瑟的余民。

16因此,主——万军之上帝耶和华说:

“哀号之声要响遍各广场,

哭喊之声将充满大街小巷。

农夫被叫来哭泣,

哭丧者被召来哀号。

17每个葡萄园都传出哀恸的声音,

因为我要从你们中间经过,惩罚你们。

这是耶和华说的。”

18盼望耶和华的日子到来的人有祸了!

你们为什么盼望耶和华的日子呢?

那日将带来黑暗,而非光明。

19你们的光景将好像人逃避狮子,

却遇上了熊,

逃回家里,手扶墙壁,

又被蛇咬。

20耶和华的日子将充满黑暗,毫无光明,

一片漆黑,

毫无亮光。

21“我憎恶、鄙弃你们的节期,

厌恶你们的圣会。

22即使你们献上燔祭和素祭,

我也不悦纳;

即使你们用肥美的牲畜献上平安祭,

我也不屑一顾。

23撤去你们嘈杂的歌声吧,

我不想听到你们的琴音。

24惟愿公正如江河滔滔不尽,

公义如溪流绵绵不绝。

25以色列家啊,

在旷野的四十年间,

你们向我献过祭物和供品吗?

26你们抬着为自己造的神像——

你们的王撒固和星神迦温

27所以,我要使你们被掳到大马士革以外的地方。”

这是耶和华说的,祂的名字是万军之上帝。