ነህምያ 5 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ነህምያ 5:1-19

ነህምያ ድኾችን ረዳ

1በዚህ ጊዜ ወንዶቹና ሚስቶቻቸው አይሁድ ወንድሞቻቸውን በመቃወም ብርቱ ጩኸት አሰሙ፤ 2አንዳንዶቹ፣ “እኛም ሆን ወንዶችና ሴቶች ልጆቻችን በቍጥር ብዙ ነን፤ ታዲያ ለመብላትም ሆነ በሕይወት ለመቈየት እህል ማግኘት አለብን” አሉ።

3ሌሎቹ፣ “በራቡ ወቅት እህል ለማግኘት ስንል ዕርሻችንን፣ የወይን ተክል ቦታችንንና ቤታችንን እስከ ማስያዝ ደርሰናል” አሉ።

4ሌሎቹ ደግሞ እንዲህ አሉ፤ “የዕርሻችንንና የወይን ተክል ቦታችንን ግብር ለንጉሡ ለመክፈል ገንዘብ እስከ መበደር ደርሰናል። 5ምንም እንኳ ከአገራችን ሰዎች ጋር በሥጋና በደም አንድ ብንሆንም፣ እንደ እነርሱ ልጆች ሁሉ የእኛም ወንዶች ልጆች ጥሩዎች ቢሆኑም፣ ወንዶችና ሴቶች ልጆቻችንን ባሮች እንዲሆኑ ሰጥተናል፤ አንዳንድ ሴቶች ልጆቻችን አሁንም በባርነት ላይ ናቸው፤ ዕርሻችንና የወይን ተክል ቦታችን የሌሎች በመሆናቸው እኛ ደካሞች ሆነናል።” 6እኔም ጩኸታቸውንና እነዚህን አቤቱታዎች በሰማሁ ጊዜ፣ እጅግ ተቈጣሁ፤ 7ከዚያም ነገሩን በሐሳቤ ካወጣሁ ካወረድሁ በኋላ፣ መኳንንቱንና ሹማምቱን ገሠጽኋቸው፤ “ከገዛ አገራችሁ ሰዎች ላይ እንዴት ዐራጣ ትበላላችሁ” አልኋቸውም። ስለዚህ ከእነርሱ ጋር ለመነጋገር ታላቅ ስብሰባ ጠራሁ፤ 8“ለአሕዛብ ተሽጠው የነበሩትን አይሁድ ወንድሞቻችንን በተቻለን ሁሉ ተቤዥተናቸዋል፤ አሁንም እናንተ ወንድሞቻችሁን ትሸጣላችሁ፤ ይህም መልሰን እንድንቤዣቸው ለማድረግ ብቻ ነው!” አልኋቸው፤ እነርሱም የሚመልሱት አልነበራቸውምና ዝም አሉ።

9ስለዚህ በመቀጠል እንዲህ አልሁ፤ “ይህ የምታደርጉት ነገር ትክክል አይደለም፤ የጠላቶቻችንን የአሕዛብን ስድብ ለማስወገድ የአምላካችንን መንገድ በፍርሀት መከተል አይገባችሁምን? 10እኔ፣ ወንድሞቼና ሰዎቼም እንደዚሁ ለሕዝቡ ገንዘብና እህል አበድረናል፤ ዐራጣው ግን ያብቃ። 11ዕርሻቸውን፣ የወይንና የወይራ ዘይት ተክል ቦታቸውንና ቤታቸውን በቶሎ መልሱላቸው፤ እንዲሁም የምታስከፍሏቸውን የገንዘቡን፣ የእህሉን፣ የአዲሱን ወይንና ዘይት አንድ መቶኛ ዐራጣ መልሱላቸው”። 12እነርሱም፣ “እንመልሳለን፤ ምንም ዐይነት ትርፍ አንጠይቃቸውም፤ እንዳልኸን እናደርጋለን” አሉ። ካህናቱን ጠራኋቸው፤ መኳንንቱንና ሹማምቱም የገቡትን ቃል እንዲፈጽሙ አማልኋቸው። 13እንዲሁም የልብሴን ዘርፍ አራግፌ፣ “ይህን የተስፋ ቃል የማይፈጽመውን ማናቸውንም ሰው አምላክ ቤቱንና ንብረቱን እንደዚህ ያራግፈው፤ እንደዚህ ያለውም ሰው ይርገፍ፤ ባዶም ይሁን” አልሁ። በዚህም ጉባኤው ሁሉ፣ “አሜን” በማለት እግዚአብሔርን አመሰገነ፤ ሕዝቡም የገቡትን ቃል ፈጸሙ።

14ከዚህም በላይ በይሁዳ ምድር አገረ ገዥ ሆኜ ከተሾምሁበት፣ ከአርጤክስስ ሃያኛ ዓመት ጀምሮ እስከ ሠላሳ ሁለተኛው ዘመነ መንግሥቱ ድረስ፣ ለዐሥራ ሁለት ዓመት እኔም ሆንሁ ወንድሞቼ ለአንድ አገረ ገዥ የተመደበውን ምግብ ተቀብለን አልበላንም። 15ከእኔ በፊት የነበሩት የቀድሞዎቹ አገረ ገዦች ግን ከምግቡና ከወይኑ ሌላ፣ በሕዝቡ ላይ ከባድ ሸክም በመጫን አርባ ሰቅል5፥15 0.5 ኪሎ ግራም ያህል ነው። ብር ይወስዱ ነበር፤ ረዳቶቻቸውም እንዲሁ ይጭኑባቸው ነበር። እኔ ግን እግዚአብሔርን ከመፍራቴ የተነሣ እንዲህ ያለውን አላደረግሁም። 16ከዚህ ይልቅ ራሴን ለዚህ ቅጥር ሥራ ሰጠሁ። ሰዎቼም ሁሉ ለሥራው እዚያው ይሰበሰቡ ነበር፤ ምንም መሬት አልነበረንም5፥16 ብዙ የዕብራይስጥ ቅጆች ከዚህ ጋር ይስማማሉ፤ አንዳንድ የዕብራይስጥ ቅጆች፣ የሰብዓ ሊቃናት፣ የቩልጌትና የሱረሰት ቅጆች ግን አልነበረኝም ይላሉ።

17ከዚህም በላይ በዙሪያችን ካሉት፣ ወደ እኛ ከሚመጡት አሕዛብ ሌላ አንድ መቶ አምሳ አይሁድና ሹማምት ከማእዴ ይካፈሉ ነበር። 18በየዕለቱም አንድ በሬ፣ ስድስት ምርጥ በጎችና የተወሰኑ ዶሮዎች፣ በየዐሥሩም ቀን ብዛት ያለው ልዩ ልዩ የወይን ጠጅ ይዘጋጅልኝ ነበር። ይህም ሁሉ ሆኖ ለአንድ አገረ ገዥ የተመደበውን ምግብ ከቶ ጠይቄ አላውቅም፤ በሕዝቡ ላይ የተጣለው ሸክም ከባድ ነበርና።

19አምላኬ ሆይ፤ ለዚህ ሕዝብ ያደረግሁትን ሁሉ በበጎነት ዐስብልኝ።

Thai New Contemporary Bible

เนหะมีย์ 5:1-19

เนหะมีย์ช่วยเหลือผู้ยากไร้

1ครั้งนั้นมีพวกผู้ชายพร้อมกับภรรยามาโวยวายเรื่องพี่น้องชาวยิวของตน 2บางคนกล่าวว่า “พวกเรารวมทั้งบุตรชายบุตรสาวของเรามีจำนวนมาก พวกเราต้องขวนขวายหาอาหารเพื่อเราจะมีข้าวกินประทังชีวิต”

3บางคนก็กล่าวว่า “เราต้องจำนองบ้าน ที่นา และสวนองุ่น เพื่อแลกเมล็ดข้าวในช่วงกันดารอาหาร”

4ในขณะที่บางคนกล่าวว่า “เราต้องกู้ยืมเงินเพื่อเสียภาษีที่นาและสวนองุ่นให้กษัตริย์ 5ถึงแม้ว่าเราจะเป็นเลือดเนื้อเชื้อไขเดียวกันกับเพื่อนร่วมชาติคนอื่นๆ และถึงแม้ลูกชายของเราก็ดีพอๆ กับลูกของพวกเขา แต่เราต้องให้ลูกชายลูกสาวของเราเป็นทาส ลูกสาวบางคนของเรากลายเป็นทาสโดยที่เราไม่มีทางไถ่ตัวคืนมา เพราะเรือกสวนไร่นาของเราตกเป็นของคนอื่นแล้ว”

6ข้าพเจ้าโกรธมากที่ได้ยินเช่นนี้ 7เมื่อใคร่ครวญเรื่องนี้แล้ว ข้าพเจ้าก็ต่อว่าเหล่าขุนนางและข้าราชการว่า “พวกท่านขูดรีดพี่น้องร่วมชาติ!” ข้าพเจ้าจึงเรียกประชุมใหญ่เพื่อจัดการกับคนพวกนี้ 8ข้าพเจ้าพูดกับพวกเขาว่า “เราต้องทำทุกวิถีทางเพื่อไถ่พี่น้องชาวยิวของเราที่ถูกขายให้คนต่างชาติกลับคืนมาให้ได้ แต่นี่พวกท่านกลับขายพี่น้องของตัวเองเพียงเพื่อให้พวกเขาถูกขายกลับมาให้พวกเรา!” คนเหล่านั้นก็นิ่งเงียบพูดอะไรไม่ออก

9ข้าพเจ้าจึงพูดต่อไปว่า “สิ่งที่พวกท่านทำอยู่นี้ไม่ถูกต้อง ท่านควรจะดำเนินชีวิตด้วยความยำเกรงพระเจ้าของพวกเราไม่ใช่หรือ? จะได้ไม่เป็นที่ตำหนิติเตียนของศัตรูต่างชาติ 10ข้าพเจ้ากับพี่น้อง และคนของข้าพเจ้าก็ให้คนยืมเงิน ยืมข้าว จงเลิกการให้ยืมแบบเก็บดอกเบี้ยอย่างนี้เถิด! 11จงคืนที่นา สวนองุ่น สวนมะกอก และบ้านเรือนให้เขาทันที ทั้งดอกเบี้ยที่ท่านเก็บไม่ว่าจะเป็นเงิน ข้าว เหล้าองุ่นใหม่ หรือน้ำมัน”

12พวกเขาตอบว่า “เราจะคืนให้และจะไม่เรียกร้องสิ่งใดจากพวกเขาอีก เราจะทำตามที่ท่านบอก”

ข้าพเจ้าจึงเรียกบรรดาปุโรหิตมา และให้ขุนนางและข้าราชการเหล่านี้สาบานว่าจะทำตามที่สัญญาไว้ 13แล้วข้าพเจ้ายังสะบัดชายเสื้อคลุมของข้าพเจ้าและลั่นวาจาว่า “ใครไม่รักษาคำสัญญานี้ ขอให้พระเจ้าสลัดบ้านและทรัพย์สินของเขาออกไปอย่างนี้ ให้เขาถูกสลัดออกไปจนหมดเนื้อหมดตัว!”

แล้วประชากรทั้งหมดขานรับว่า “อาเมน” และสรรเสริญองค์พระผู้เป็นเจ้า คนทั้งหลายก็ทำตามที่สัญญาไว้

14ยิ่งไปกว่านั้นตลอดสิบสองปีที่ข้าพเจ้าเป็นผู้ว่าการยูดาห์ นับตั้งแต่ปีที่ยี่สิบถึงปีที่สามสิบสองแห่งรัชกาลกษัตริย์อารทาเซอร์ซีส ตัวข้าพเจ้าหรือพี่น้องไม่ได้รับส่วนแบ่งอาหารของผู้ว่าการเลย 15ผู้ว่าการคนอื่นๆ ก่อนหน้าข้าพเจ้าได้เบียดเบียนประชาชนโดยเรียกร้องเอาเงินหนัก 40 เชเขล5:15 1 เชเขล คือเงินหนักประมาณ 11.5 กรัม มีค่าเท่ากับค่าแรงสองเดือนนอกเหนือจากอาหารและเหล้าองุ่น ลูกน้องของเขาก็วางอำนาจเหนือประชาชน แต่ข้าพเจ้ายำเกรงพระเจ้าจึงไม่ประพฤติตัวเช่นนั้น 16ข้าพเจ้ากลับทุ่มเทให้กับงานสร้างกำแพง คนทั้งหมดของข้าพเจ้าก็มาชุมนุมกันอยู่ที่นั่นเพื่อทำงาน เรา5:16 สำเนาต้นฉบับภาษาฮีบรูบางฉบับ และฉบับ LXX. และ Syr. ว่าข้าพเจ้าไม่ได้คิดหาจับจองที่ดิน

17ยิ่งกว่านั้นมีคนยิวและเจ้าหน้าที่รวม 150 คนร่วมโต๊ะกับข้าพเจ้าเป็นประจำ นอกเหนือจากคน ชาติต่างๆ โดยรอบซึ่งมาหาพวกเรา 18แต่ละวันต้องจัดเตรียมวัวผู้หนึ่งตัว แกะอ้วนหกตัว และเป็ดไก่จำนวนหนึ่งให้ข้าพเจ้า และทุกสิบวันมีเหล้าองุ่นทุกชนิดในปริมาณมาก แต่ข้าพเจ้าก็ไม่เคยเรียกร้องส่วนแบ่งอาหารของผู้ว่าการจากประชาชน เพราะพวกเขาเองก็เดือดร้อนอยู่แล้ว

19ข้าแต่พระเจ้าของข้าพระองค์ ขอทรงระลึกถึงข้าพระองค์ด้วยความโปรดปรานในสิ่งทั้งปวงที่ข้าพระองค์ได้ทำเพื่อประชากรเหล่านี้