ቲቶ 1 – NASV & CRO

New Amharic Standard Version

ቲቶ 1:1-16

1የእግዚአብሔርን ምርጦች እምነትና ወደ እውነተኛ መንፈሳዊነት የሚመራውን የእውነት ዕውቀት ለማሳደግ የእግዚአብሔር ባሪያና የኢየሱስ ክርስቶስ ሐዋርያ የሆነው ጳውሎስ፤ 2እምነቱና ዕውቀቱ የተመሠረቱትም የማይዋሸው አምላክ ከዘመናት በፊት በገባው የዘላለም ሕይወት ተስፋ ላይ ነው። 3እርሱ በወሰነውም ጊዜ በአዳኛችን በእግዚአብሔር ትእዛዝ ለእኔ ዐደራ በተሰጠ ስብከት በኩል ቃሉን ይፋ አደረገ።

4የጋራችን በሆነው እውነተኛ እምነት ልጄ ለሆነው ለቲቶ፤

ከእግዚአብሔር አብ፣ ከአዳኛችንም ከክርስቶስ ኢየሱስ ጸጋና ሰላም ይሁን።

ቲቶ በቀርጤስ የነበረው ኀላፊነት

5አንተን በቀርጤስ የተውሁህ ገና ያልተስተካከለውን ነገር እንድታስተካክልና ባዘዝሁህ መሠረት በየከተማው ሽማግሌዎችን እንድትሾም ነው። 6ሽማግሌ ነቀፋ የሌለበት፣ የአንዲት ሚስት ባል፣ ልጆቹም አማኞችና በመዳራት ወይም ባለመታዘዝ ስማቸው የማይነሣ ይሁን። 7ኤጲስቆጶስ የእግዚአብሔር ሥራ ባለ ዐደራ እንደ መሆኑ የማይነቀፍ ሊሆን ይገባል፤ ይኸውም ትምክሕተኛ፣ ግልፍተኛ፣ ሰካራም፣ ጨቅጫቃና ተገቢ ባልሆነ መንገድ ለጥቅም የሚሮጥ ሊሆን አይገባም። 8ከዚህ ይልቅ እንግዳ ተቀባይ፣ በጎ የሆነውን ነገር የሚወድድ፣ ራሱን የሚገዛ፣ ቅን፣ ቅዱስና ጠንቃቃ ሊሆን ይገባል። 9ሌሎችን ትክክል በሆነው ትምህርት እንዲያበረታታና ይህንኑ ትምህርት የሚቃወሙትን ይወቅሥ ዘንድ እንደ ተማረው በታመነ ቃል የሚጸና መሆን አለበት።

10ዐመፀኞች፣ ለፍላፊዎችና አታላዮች የሆኑ ብዙ ሰዎች አሉና፤ በተለይም እነዚህ ከተገረዙት ወገን ናቸው። 11እነዚህን ዝም ማሰኘት ተገቢ ነው፤ ምክንያቱም ትክክል ባልሆነ መንገድ ጥቅም ለማግኘት ሲሉ ማስተማር የማይገባቸውን ነገር በማስተማር ቤተ ሰብን ሁሉ በመበከል ላይ ናቸው። 12ከራሳቸው ነቢያት አንዱ ስለ እነርሱ ሲናገር፣ “የቀርጤስ ሰዎች ዘወትር ውሸታሞች፣ ክፉ አውሬዎችና ሰነፍ ሆዳሞች ናቸው” ብሏል። 13ይህ ምስክርነት እውነት ነው፤ ስለዚህ አጥብቀህ ገሥጻቸው፤ ይኸውም ትክክለኛ እምነት እንዲኖራቸውና 14የአይሁድን ተረት ወይም ከእውነት የራቁትን ሰዎች ትእዛዝ እንዳያዳምጡ ነው። 15ለንጹሓን ሁሉም ነገር ንጹሕ ነው፤ ለርኩሳንና ለማያምኑ ግን ንጹሕ የሆነ ምንም ነገር የለም፤ እንዲያውም አእምሯቸውና ኅሊናቸው የረከሰ ነው። 16እግዚአብሔርን እናውቃለን ይላሉ፤ ዳሩ ግን በተግባራቸው ይክዱታል፤ አስጸያፊዎች፣ የማይታዘዙና ለበጎ ሥራ የማይበቁ ናቸው።

Knijga O Kristu

Titu 1:1-16

Pavlovi pozdravi

1Ovo je pismo od Pavla, Božjega sluge i apostola Isusa Krista. Poslan sam učvršćivati vjeru Božjih izabranika i poučiti ih istini da mogu pobožno živjeti. 2Ta im istina daje nadu vječnog života koji im je Bog obećao prije postanka svijeta—a Bog ne može lagati. 3U pravo vrijeme objavio je svoju Riječ propovijedanjem, koje je meni povjereno po zapovijedi Boga, našega Spasitelja.

4Pišem Titu, mojemu pravom sinu po zajedničkoj vjeri.

Neka ti Bog Otac i naš Spasitelj Isus Krist udijele milost i mir.

Titov rad na Kreti

5Ostavio sam te na Kreti da dovršiš naše djelo i da po gradovima postaviš starješine kao što sam te uputio. 6Starješina mora biti besprijekoran, vjeran svojoj ženi,1:6 Ili: jedne žene muž. a djeca mu moraju biti vjernici. Nikomu ne smiju davati povoda da ih optuži za razuzdanost ili nepokornost. 7Nadglednik mora živjeti besprijekorno jer je Božji upravitelj. Ne smije biti samoživ, svadljiv, pijanac, nasilnik ni sklon prljavom dobitku. 8Mora biti gostoljubiv, dobrostiv, razborit, pravedan, svet i uzdržljiv. 9Mora se čvrsto držati vjerodostojne riječi učenja, mora hrabriti druge i uvjeravati protivnike u zdravo učenje.

10Mnogo je nepokornih, taštih govornika prijevarnih umova, osobito među Židovima1:10 U grčkome obrezanih., 11i takve treba natjerati da ušute. Već su cijele obitelji unesrećili poučavajući radi prljavog dobitka ono što ne bi smjeli. 12Jedan od njih, njihov vlastiti prorok, za njih je rekao: “Svi su ti Krećani lašci, opake zvijeri, lijene izjelice.” 13To je istina. Zato strogo kori kršćane da budu zdravi u vjeri, 14da ne prihvaćaju židovske bajke i zapovijedi ljudi koji okreću leđa istini.

15Čistim ljudima sve je čisto, a okaljanima i nevjernima ništa nije čisto; njima su i razum i savjest okaljani. 16Tvrde da poznaju Boga, ali ga svojim djelima niječu. Odurna su to i buntovna stvorenja, neposobna za bilo kakvo dobro djelo.