ቈላስይስ 1 – NASV & CCBT

New Amharic Standard Version

ቈላስይስ 1:1-29

1በእግዚአብሔር ፈቃድ የክርስቶስ ኢየሱስ ሐዋርያ ከሆነው ከጳውሎስና ከወንድማችን ከጢሞቴዎስ፤

2በቈላስይስ ለሚኖሩ፣ በክርስቶስ ለሆኑ ቅዱሳንና ታማኝ1፥2 ወይም የሚያምኑ ወንድሞች፤

ከእግዚአብሔር ከአባታችን1፥2 አንዳንድ የጥንት ቅጆች ከአባትና ከጌታ ከኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና ሰላም ለእናንተ ይሁን።

ምስጋናና ጸሎት

3ስለ እናንተ በምንጸልይበት ጊዜ የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን አባት እግዚአብሔርን ሁልጊዜ እናመሰግናለን፤ 4ምክንያቱም በክርስቶስ ኢየሱስ ስላላችሁ እምነትና ለቅዱሳን ሁሉ ስላላችሁ ፍቅር ሰምተናል፤ 5ይህም የሆነው በሰማይ ተዘጋጅቶ ከተቀመጠላችሁ ተስፋ የተነሣ ነው፤ ስለዚህ ተስፋ በወንጌል የእውነት ቃል አስቀድማችሁ ሰማችሁ፤ 6ይህም ወደ እናንተ ደርሷል። ይህንም ወንጌል ከሰማችሁበትና የእግዚአብሔርን ጸጋ በእውነት ከተረዳችሁበት ቀን ጀምሮ በዓለም ዙሪያ እየሠራ እንዳለ ሁሉ በእናንተም ዘንድ ፍሬ እያፈራና እያደገ ነው። 7ይህንም ስለ እኛ1፥7 አንዳንድ የጥንት ቅጆች እናንተ ይላሉ። የክርስቶስ ታማኝ አገልጋይ የሆነው፣ አብሮንም በአገልግሎት የተጠመደው ተወዳጁ ኤጳፍራ አስተማራችሁ፤ 8ደግሞም በመንፈስ ስላላችሁ ፍቅር ነገረን።

9ከዚህ የተነሣ እኛ ደግሞ ይህን ከሰማንበት ቀን ጀምሮ እግዚአብሔር የፈቃዱን ዕውቀት በመንፈሳዊ ጥበብና መረዳት ሁሉ ይሞላችሁ ዘንድ ስለ እናንተ መጸለይና መለመን አላቋረጥንም፤ 10የምንጸልየውም ለጌታ እንደሚገባ እንድትኖሩና በሁሉም ደስ እንድታሰኙት ነው፤ ይኸውም በመልካም ሥራ ሁሉ ፍሬ እያፈራችሁ እግዚአብሔርን በማወቅ እያደጋችሁ፣ 11ታላቅ ጽናትና ትዕግሥት ይኖራችሁ ዘንድ፣ እንደ ክቡር ጕልበቱ መጠን በኀይል ሁሉ እየበረታችሁ፣ ደስ እየተሰኛችሁ፣ 12በቅዱሳን ርስት በብርሃን ተካፋዮች ለመሆን ያበቃንን1፥12 ወይም ያበቃችሁን አብን እንድታመሰግኑ ነው። 13እርሱ ከጨለማ አገዛዝ ታደገን፤ ወደሚወድደው ልጁ መንግሥትም አሻገረን፤ 14በእርሱም መዋጀትን በደሙ1፥14 አንዳንድ ቅጆች በደሙ የሚለው ቃል የላቸውም። አግኝተናል፤ ይህም የኀጢአት ይቅርታ ነው።

ክርስቶስ ከሁሉ በላይ

15እርሱ የማይታየው አምላክ አምሳል ነው፤ ከፍጥረት ሁሉ በፊት1፥15 ወይም በላይ በኵር ነው፤ 16ሁሉ ነገር በእርሱ ተፈጥሯል፤ በሰማይና በምድር ያሉ፣ የሚታዩና የማይታዩ፣ ዙፋናት ቢሆኑ ወይም ኀይላት፣ ገዦች ቢሆኑ ወይም ባለሥልጣናት፣ ሁሉም ነገር በእርሱና ለእርሱ ተፈጥሯል። 17እርሱ ከሁሉ በፊት ነው፤ ሁሉም ነገር በአንድ ላይ ተያይዞ የጸናው በእርሱ ነው። 18እርሱ አካሉ የሆነችው የቤተ ክርስቲያን ራስ ነው፤ በሁሉ ነገር የበላይነት ይኖረው ዘንድ እርሱ የመጀመሪያ፣ ከሙታን መካከልም በኵር ነው። 19እግዚአብሔርም ሙላቱ ሁሉ በእርሱ ይሆን ዘንድ ወድዷልና፤ 20በመስቀሉ ላይ በፈሰሰው ደሙ ሰላምን በማድረግ በምድርም ሆነ በሰማይ ያለውን ነገር ሁሉ በእርሱ በኩል ከራሱ ጋር አስታረቀ።

21ከክፉ ባሕርያችሁ የተነሣ1፥21 ወይም በክፉ ባሕርያችሁ እንደሚታየው ቀድሞ ከእግዚአብሔር የተለያችሁ በዐሳባችሁም ጠላቶች ነበራችሁ። 22አሁን ግን ነውርና ነቀፋ የሌለባችሁ ቅዱሳን አድርጎ በእርሱ ፊት ሊያቀርባችሁ፣ በክርስቶስ ሥጋ በሞቱ በኩል አስታረቃችሁ፤ 23ይህም የሚሆነው በእምነታችሁ ተመሥርታችሁና ተደላድላችሁ በመቆም ከሰማችሁት የወንጌል ተስፋ ሳትናወጡ ጸንታችሁ ብትኖሩ ነው። እናንተ የሰማችሁትና ከሰማይ በታች ላለ ፍጥረት ሁሉ የተሰበከውም ወንጌል ይኸው ነው፤ እኔም ጳውሎስ ለዚህ ወንጌል አገልጋይ ሆንሁ።

ጳውሎስ ስለ ቤተ ክርስቲያን ያሳየው ትጋት

24ስለ እናንተ በተቀበልሁት መከራ አሁንም ደስ ይለኛል፤ ክርስቶስ ስለ አካሉ ስለ ቤተ ክርስቲያን ከተቀበለው መከራ የጐደለውን በሥጋዬ አሟላለሁ። 25የእግዚአብሔርን ቃል በሙላት እንዳቀርብላችሁ ከእግዚአብሔር በተሰጠኝ ዐደራ የቤተ ክርስቲያን አገልጋይ ሆኛለሁ፤ 26ይህም ቃል ከዘመናትና ከትውልዶች ተሰውሮ ምስጢር ሆኖ ቈይቶ ነበር፤ አሁን ግን ለቅዱሳኑ ተገልጧል። 27ለእነርሱም እግዚአብሔር የዚህ ምስጢር ክብር ባለጠግነት በአሕዛብ መካከል ምን ያህል እንደ ሆነ ለማሳወቅ መረጠ፤ እርሱም የክብር ተስፋ የሆነው በእናንተ ውስጥ ያለው ክርስቶስ ነው።

28እኛም እያንዳንዱን ሰው በክርስቶስ ፍጹም አድርገን ማቅረብ እንችል ዘንድ፣ ሰውን ሁሉ በጥበብ ሁሉ እየመከርንና እያስተማርን እርሱን እንሰብካለን። 29እኔም በብርታት በውስጤ በሚሠራው በእርሱ ኀይል ሁሉ እየታገልሁ ለዚህ ዐላማ እጥራለሁ።

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

歌羅西書 1:1-29

1我是奉上帝旨意作基督耶穌使徒的保羅2提摩太弟兄寫信給歌羅西的聖徒,就是忠於基督的弟兄姊妹。

願我們的父上帝賜給你們恩典和平安!

感恩與禱告

3-4我們聽說了你們對基督耶穌的信心和對眾聖徒的愛心,為你們禱告的時候,常常感謝我們主耶穌基督的父上帝。 5你們能有這樣的信心和愛心是因為那給你們存在天上的盼望,就是你們從前從福音真道中聽到的盼望。 6這福音不但傳到了你們那裡,也傳到了世界各地,並且開花結果,信主的人數不斷增長,正如你們當初聽了福音,因為明白真理而認識上帝的恩典後的情形。 7這福音是你們從我們親愛的同工以巴弗那裡得知的。他代表我們1·7 我們」有古卷作「你們」。作基督的忠僕, 8並把聖靈賜給你們的愛心告訴了我們。

9因此,從聽到你們的消息那天起,我們便不斷地為你們禱告,求上帝使你們在一切屬靈的智慧和悟性上完全明白祂的旨意, 10以便你們行事為人對得起主,凡事蒙祂喜悅,在一切良善的事上結出果實,對上帝的認識不斷增加。 11願上帝以祂榮耀的權能使你們剛強,無論遇到什麼事都能長久忍耐, 12歡喜地感謝天父,因祂使你們有資格跟眾聖徒在光明中同享基業。 13祂把我們從黑暗的權勢下拯救出來,帶進祂愛子的國度裡。 14我們藉著祂的愛子蒙救贖,罪過得到赦免。

基督超越一切

15基督是那不能看見之上帝的真像,超越1·15 超越」或譯「先存於」,希臘文是「長子」,常用來指地位上的優越或時間上的優先。一切受造之物。 16因為萬物都是藉著祂創造的,天上的、地上的、有形的、無形的、作王的、統治的、執政的、掌權的,一切都是藉著祂也是為了祂而創造的。 17祂存在於萬物之前,萬物都靠祂而維繫。 18祂是教會的頭,教會是祂的身體;祂是源頭,是首先從死裡復活的,這樣祂可以在一切事上居首位。 19因為上帝樂意讓一切的豐盛住在祂裡面, 20又藉著祂在十字架上所流的血成就了和平,使天地萬物藉著祂與上帝和好。

21你們從前與上帝隔絕,行事邪惡,心思意念與祂為敵; 22但現在上帝藉著基督肉身的死使你們與祂和好了,讓你們在祂面前成為聖潔無瑕、無可指責的人。 23只是你們必須恆心持守所信的道,根基穩固,堅定不移,不要失去你們聽到福音後所得到的盼望。這福音傳給了天下萬民。我保羅也作了這福音的使者。

保羅為教會受苦

24現在我因能夠為你們受苦而歡喜,並且我是為基督的身體——教會的緣故,在自己身上補滿基督未受的苦難。 25我受上帝的委派成為教會的僕人,要把上帝的道完整地傳給你們。 26這道是歷世歷代一直隱藏的奧祕,現在已經向祂的眾聖徒顯明了。 27上帝要他們知道這奧祕在外族人中有何等豐富的榮耀,這奧祕就是基督在你們裡面,使你們有榮耀的盼望。 28我們傳揚基督,用各樣的智慧勸誡、教導眾人,使他們在基督裡長大成熟,好把他們帶到上帝面前。 29為此,我按著祂在我身上運行的大能盡心竭力,不辭勞苦。