ሰቈቃወ 2 – NASV & JCB

New Amharic Standard Version

ሰቈቃወ 2:1-22

א አሌፍ

2 ይህ ምዕራፍ ጥቅሶቹ ተከታታይ ፊደላት ባሉት የዕብራይስጥ ሆህያት የሚጀምር፣ የመጀመሪያው ወይም የመጨረሻው መሥመር ትርጕም የሚሰጥ ቃል ወይም ዐረፍተ ነገር ያለው ግጥም ነው። 1ጌታ የጽዮንን ሴት ልጅ፣

በቍጣው ደመና እንዴት ጋረዳት!2፥1 ወይም እግዚአብሔር በቍጣው የጽዮንን ሴት ልጅ እንዴት አዋረዳት!

ከሰማይ ወደ ምድር፣

የእስራኤልን ክብር ወርውሮ ጣለው፤

በቍጣው ቀን፣

የእግሩን መቀመጫ አላስታወሰም።

ב ቤት

2የያዕቆብን መኖሪያ ሁሉ፣

ጌታ ያለ ርኅራኄ ዋጣቸው፤

የይሁዳን ሴት ልጅ ምሽጎች፣

በቍጣው አፈረሳቸው፤

መንግሥቷንና መሳፍንቷን፣

በማዋረድ ወደ ምድር ጣላቸው።

ג ጊሜል

3በጽኑ ቍጣው፣

የእስራኤልን ቀንድ ሁሉ2፥3 ወይም ብርታትን ሁሉ፤ ወይም ንጉሥ ሁሉ፤ ቀንድ በዚህ ቦታ ብርታትን ያመለክታል። ሰበረ፤

ጠላት በተቃረበ ጊዜ፣

ቀኝ እጁን ወደ ኋላ መለሰ፤

በዙሪያው ያለውን ሁሉ እንደሚበላ እሳት፣

በያዕቆብ ላይ የእሳት ነበልባል ነደደ።

ד ዳሌት

4እንደ ጠላት ቀስቱን ገተረ፤

ቀኝ እጁ ተዘጋጅታለች፤

ለዐይን ደስ የሚያሰኙትን ሁሉ፤

እንደ ጠላት ዐረዳቸው፤

በጽዮን ሴት ልጅ ድንኳን ላይ፣

ቍጣውን እንደ እሳት አፈሰሰ።

ה ሄ

5ጌታ እንደ ጠላት ሆነ፤

እስራኤልንም ዋጠ፤

ቤተ መንግሥቶቿን ሁሉ ዋጠ፤

ምሽጎቿን አፈራረሰ፤

በይሁዳ ሴት ልጅ፣

ልቅሶንና ሰቈቃን አበዛ።

ו ዋው

6ማደሪያውን እንደ አትክልት ስፍራ ባዶ አደረገ፤

መሰብሰቢያ ስፍራውን አፈረሰ፤

እግዚአብሔር ጽዮንን፣

ዓመት በዓላቶቿንና ሰንበታቷን እንድትረሳ አደረጋት፤

በጽኑ ቍጣው፣

ንጉሡንና ካህኑን እጅግ ናቀ።

ז ዛይን

7ጌታ መሠዊያውን ናቀ፤

መቅደሱንም ተወ፤

የቤተ መንግሥቶቿን ቅጥሮች፣

ለጠላት አሳልፎ ሰጠ፤

በዓመት በዓል ቀን እንደሚደረገው

በእግዚአብሔር ቤት በኀይል ጮኹ።

ח ኼት

8በጽዮን ሴት ልጅ ዙሪያ ያለውን ቅጥር፣

እግዚአብሔር ለማፍረስ ወሰነ፤

የመለኪያ ገመድ ዘረጋ፤

ከማጥፋትም እጆቹን አልሰበሰበም፤

ምሽጎችና ቅጥሮች እንዲያለቅሱ አደረገ፤

በአንድነትም ጠፉ።

ט ቴት

9በሮቿ ወደ ምድር ሰመጡ፤

የብረት መወርወሪያዎቻቸውን ሰባበረ፤ አጠፋቸውም፤

ንጉሧና መሳፍንቷ በአሕዛብ መካከል ተማርከው ተሰድደዋል፤

ሕጉ ከእንግዲህ አይኖርም፤

ነቢያቷም ከእንግዲህ፣

ከእግዚአብሔር ራእይ አያገኙም።

י ዮድ

10የጽዮን ሴት ልጅ ሽማግሌዎች፣

በምድር ላይ በዝምታ ተቀምጠዋል፤

በራሳቸው ላይ ትቢያ ነሰነሱ፤

ማቅም ለበሱ፤

የኢየሩሳሌም ወጣት ሴቶች፣

ራሳቸውን ወደ ምድር ዝቅ አደረጉ።

כ ካፍ

11ዐይኔ በልቅሶ ደከመ፤

ነፍሴ በውስጤ ተሠቃየች፤

ልቤም በሐዘን ፈሰሰች፣

በከተማዪቱ መንገዶች ላይ፣

ሕዝቤ ተደምስሰዋልና፤

ልጆችና ሕፃናት ደክመዋልና።

ל ላሜድ

12በከተማዪቱ መንገዶች ላይ፣

እንደ ቈሰሉ ሰዎች ሲደክሙ፣

በእናታቸው ክንድ ላይ፣

ነፍሳቸው በመውጣት ላይ ሳለች፣

“እንጀራና የወይን ጠጅ የት አለ?”

እያሉ እናቶቻቸውን ይጠይቃሉ።

מ ሜም

13የኢየሩሳሌም ሴት ልጅ ሆይ፤ ስላንቺ ምን ማለት እችላለሁ?

ከምንስ ጋር አወዳድርሻለሁ? ድንግሊቱ የጽዮን ልጅ ሆይ፤

አጽናናሽ ዘንድ፣

በምን ልመስልሽ እችላለሁ?

ቍስልሽ እንደ ባሕር ጥልቅ ነው፤

ማንስ ሊፈውስሽ ይችላል?

נ ኑን

14የነቢያቶችሽ ራእይ፣

ሐሰትና ከንቱ ነው፤

ምርኮኛነትሽን ለማስቀረት፣

ኀጢአትሽን አይገልጡም።

የሚሰጡሽም የትንቢት ቃል፣

የሚያሳስትና ከመንገድ የሚያወጣ ነው።

ס ሳሜክ

15በአጠገብሽ የሚያልፉ ሁሉ፣

እጃቸውን ያጨበጭቡብሻል፤

“የውበት መደምደሚያ፣ የምድር ሁሉ ደስታ፣

የተባለች ከተማ ይህች ናትን?”

እያሉ ራሳቸውን በመነቅነቅ፣

በኢየሩሳሌም ሴት ልጅ ላይ ያሾፋሉ።

ע ዐዪን

16ጠላቶችሽ ሁሉ በአንድ ላይ፣

አፋቸውን በኀይል ከፈቱ፤

ጥርሳቸውን እያፏጩ አሾፉ፤

እንዲህም አሉ፤ “ውጠናታል፤

የናፈቅነው ጊዜ ይህ ነበር፤

ኖረንም ልናየው በቃን።”

פ ፌ

17እግዚአብሔር ያሰበውን አደረገ፤

ከረዥም ጊዜ በፊት የተናገረውን፣

ቃሉን ፈጸመ፤

ያለ ርኅራኄ አፈረሰሽ፤

ጠላት በሥቃይሽ ላይ እንዲደሰት፣

የጠላትሽንም ቀንድ2፥17 ቀንድ በዚህ ቦታ ብርታትን ያመለክታል ከፍ ከፍ አደረገ።

צ ጻዲ

18የሕዝቡ ልብ፣ ወደ ጌታ ጮኸ።

የጽዮን ሴት ልጅ ቅጥር ሆይ፤

ቀንና ሌሊት፣

እንባሽ እንደ ወንዝ ይፍሰስ፤

ለራስሽ ዕረፍትን አትስጪ፣

ዐይኖችሽ ከማንባት አያቋርጡ።

ק ቆፍ

19የሌሊቱ ሰዓት ሲጀምር፣

ተነሺ በሌሊት ጩኺ፤

በጌታ ፊት፣

ልብሽን እንደ ውሃ አፍስሺ፤

በየመንገዱ ዳር ላይ፣ በራብ ስለወደቁት፣

ስለ ልጆችሽ ሕይወት፣ እጆችሽን ወደ እርሱ አንሺ።

ר ሬሽ

20አቤቱ እግዚአብሔር ሆይ እይ፤ ተመልከትም፤

በማን ላይ እንዲህ አድርገህ ታውቃለህ?

በውኑ እናቶች ሕፃኖቻቸውን፣

ተንከባክበው ያሳደጓቸውን ልጆች ይብሉን?

ካህኑና ነቢዩስ፣

በእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ውስጥ ይገደሉን?

ש ሲን እና ሺን

21በየመንገዱ ዐቧራ ላይ፣

ወጣትና ሽማግሌ በአንድነት ወደቁ፤

ወይዛዝርቴና ጐበዛዝቴ፣

በሰይፍ ተገደሉ፤

በቍጣህ ቀን ገደልሃቸው፤

ያለ ርኅራኄም ዐረድሃቸው።

ת ታው

22“በበዓል ቀን ለግብዣ እንደምትጠራ፣

ሽብርን ከየአቅጣጫው በእኔ ላይ ጠራህ፤

በእግዚአብሔር የቍጣ ቀን፣

ማንም አላመለጠም ወይም አልተረፈም፤

የተንከባከብኋቸውንና ያሳደግኋቸውን፣

ጠላቴ አጠፋብኝ።”

Japanese Contemporary Bible

哀歌 2:1-22

2

神の怒りの理由

1主の怒りの雲がエルサレムを覆いました。

イスラエルで最も美しい町は、ちりの中に伏し、

主の命令によって天から投げ落とされました。

御怒りの燃え上がる日になると、

神はご自分の宮にさえ、

一かけらのあわれみもかけませんでした。

2主は容赦なく、イスラエル中の家を倒し、

怒りにまかせて、すべての要塞と城壁を壊しました。

この国を、支配者もろとも地にたたきつけたのです。

3イスラエルの力は、主の憤りの前に、

あえなく消滅します。

主は敵が攻めて来た時、擁護から手を引きました。

神は猛り狂う火のように、

イスラエルを焼き尽くします。

4神はご自分の民に向けて、

まるで敵でもあるかのように弓を引きます。

主の御力は彼らに向かい、

えり抜きの若者たちを虐殺し、

憤りの火を注ぎます。

5主は、敵のようになって、

イスラエルを地上から抹殺し、

その要塞と宮殿を破壊しました。

こうして、悲しみと涙が

エルサレムの受ける分となったのです。

6主は、庭先の木の枝と葉で作ったあばら屋のように、

ご自分の神殿を手荒く壊しました。

もう例祭と安息日を守ることができません。

王も、祭司も、主の激しい怒りの前に倒れます。

7主はご自分の祭壇から顔を背けました。

形ばかりの礼拝に失望したからです。

主は宮殿を敵の手に渡しました。

彼らは、例祭の日にイスラエル人がしたように、

神殿で飲み騒ぎました。

8主はエルサレムを滅ぼそうと決め、

「破壊」という物差しでこの都を測ったのです。

それで、とりでも城壁も音を立ててくずれました。

9エルサレムの門はもう役に立ちません。

主の手にかかって、錠もかんぬきも壊されたからです。

王も首長も奴隷となり、引かれて行きました。

そこには神殿もなく、

生活の指針となる律法もなく、

預言者の幻もありません。

10エルサレムの長老たちは、荒布をまとって地に座り、

黙り込んでいます。

彼らは悲しみ、失望して、頭にちりをかぶります。

おとめたちも、恥ずかしがって頭を垂れます。

11私は涙のかれるまで泣きました。

同胞の身に起こったことを見て、

悲しみのあまり胸が張り裂け、

身を切られる思いでした。

幼い子どもや、生まれたばかりの赤ん坊が、

道ばたで衰弱し、息絶えていくのです。

12子どもたちは「何か食べたい」と訴えるように、

乳の出ない母の胸に顔を埋めます。

小さないのちは、

戦場で傷ついた兵士のように消えていきます。

13今までこんな悲惨なことがあったでしょうか。

エルサレムよ。

あなたの苦悩を何にたとえたらよいでしょう。

どのようにして慰めたらよいのでしょう。

その傷は海よりも深く、だれにもいやせません。

14預言者たちは、多くのまやかしを預言しました。

あなたの罪を指摘して、

何とかしてあなたが奴隷にならないようにしようと、

努力することもありませんでした。

うそを並べ立て、

万事うまくいくと言ったのです。

15道行く人たちはみな、あざけって頭を振り、

「これが『世界で最も美しい都』とも、

『全地の喜び』とも呼ばれていた町なのか」

とさげすみます。

16敵はあなたをあざ笑い、

ののしって言います。

「とうとう、この都を滅ぼしたぞ。

待ちに待った時がついにきた。

この目で、都が倒れるのを見た。」

17しかし、このようにしたのは主です。

主は、警告どおりのことをしたのです。

ずっと前から決めていた

エルサレムを破壊するという約束を実現させたのです。

容赦なくエルサレムを滅ぼし、

敵がこの町のことで喜び、

自分たちの力を自慢するように仕向けたのです。

18その時、人々は主の前で泣きました。

エルサレムの城壁よ、昼も夜も、

存分に泣きなさい。

涙が川となって落ちるまでに。

19夜を徹して、神に叫びなさい。

主に向かって両手を上げ、

心を水のように注ぎ出しなさい。

飢えて道にしゃがみ込んでいる子どもたちのために、

ひたすら祈りなさい。

20主よ、思い直してください。

このような仕打ちをしている相手は、

神の民ではありませんか。

母親が、ひざの上であやしたわが子を

食べていいのでしょうか。

祭司や預言者が、神殿で殺されてよいのでしょうか。

21老人も幼い者も、男も女も、

敵の剣にかかって路上に倒れています。

主よ。あなたが怒って無慈悲に殺したのです。

22あなたが、この恐ろしい破壊を招き寄せたのです。

あなたの怒りの日、逃げ延びた者や生き残った者は、

一人もいません。

幼い子どもたちはみな敵の手に落ち、

冷たくなって路上に横たわっています。