ሰቈቃወ 2 – NASV & BPH

New Amharic Standard Version

ሰቈቃወ 2:1-22

א አሌፍ

2 ይህ ምዕራፍ ጥቅሶቹ ተከታታይ ፊደላት ባሉት የዕብራይስጥ ሆህያት የሚጀምር፣ የመጀመሪያው ወይም የመጨረሻው መሥመር ትርጕም የሚሰጥ ቃል ወይም ዐረፍተ ነገር ያለው ግጥም ነው። 1ጌታ የጽዮንን ሴት ልጅ፣

በቍጣው ደመና እንዴት ጋረዳት!2፥1 ወይም እግዚአብሔር በቍጣው የጽዮንን ሴት ልጅ እንዴት አዋረዳት!

ከሰማይ ወደ ምድር፣

የእስራኤልን ክብር ወርውሮ ጣለው፤

በቍጣው ቀን፣

የእግሩን መቀመጫ አላስታወሰም።

ב ቤት

2የያዕቆብን መኖሪያ ሁሉ፣

ጌታ ያለ ርኅራኄ ዋጣቸው፤

የይሁዳን ሴት ልጅ ምሽጎች፣

በቍጣው አፈረሳቸው፤

መንግሥቷንና መሳፍንቷን፣

በማዋረድ ወደ ምድር ጣላቸው።

ג ጊሜል

3በጽኑ ቍጣው፣

የእስራኤልን ቀንድ ሁሉ2፥3 ወይም ብርታትን ሁሉ፤ ወይም ንጉሥ ሁሉ፤ ቀንድ በዚህ ቦታ ብርታትን ያመለክታል። ሰበረ፤

ጠላት በተቃረበ ጊዜ፣

ቀኝ እጁን ወደ ኋላ መለሰ፤

በዙሪያው ያለውን ሁሉ እንደሚበላ እሳት፣

በያዕቆብ ላይ የእሳት ነበልባል ነደደ።

ד ዳሌት

4እንደ ጠላት ቀስቱን ገተረ፤

ቀኝ እጁ ተዘጋጅታለች፤

ለዐይን ደስ የሚያሰኙትን ሁሉ፤

እንደ ጠላት ዐረዳቸው፤

በጽዮን ሴት ልጅ ድንኳን ላይ፣

ቍጣውን እንደ እሳት አፈሰሰ።

ה ሄ

5ጌታ እንደ ጠላት ሆነ፤

እስራኤልንም ዋጠ፤

ቤተ መንግሥቶቿን ሁሉ ዋጠ፤

ምሽጎቿን አፈራረሰ፤

በይሁዳ ሴት ልጅ፣

ልቅሶንና ሰቈቃን አበዛ።

ו ዋው

6ማደሪያውን እንደ አትክልት ስፍራ ባዶ አደረገ፤

መሰብሰቢያ ስፍራውን አፈረሰ፤

እግዚአብሔር ጽዮንን፣

ዓመት በዓላቶቿንና ሰንበታቷን እንድትረሳ አደረጋት፤

በጽኑ ቍጣው፣

ንጉሡንና ካህኑን እጅግ ናቀ።

ז ዛይን

7ጌታ መሠዊያውን ናቀ፤

መቅደሱንም ተወ፤

የቤተ መንግሥቶቿን ቅጥሮች፣

ለጠላት አሳልፎ ሰጠ፤

በዓመት በዓል ቀን እንደሚደረገው

በእግዚአብሔር ቤት በኀይል ጮኹ።

ח ኼት

8በጽዮን ሴት ልጅ ዙሪያ ያለውን ቅጥር፣

እግዚአብሔር ለማፍረስ ወሰነ፤

የመለኪያ ገመድ ዘረጋ፤

ከማጥፋትም እጆቹን አልሰበሰበም፤

ምሽጎችና ቅጥሮች እንዲያለቅሱ አደረገ፤

በአንድነትም ጠፉ።

ט ቴት

9በሮቿ ወደ ምድር ሰመጡ፤

የብረት መወርወሪያዎቻቸውን ሰባበረ፤ አጠፋቸውም፤

ንጉሧና መሳፍንቷ በአሕዛብ መካከል ተማርከው ተሰድደዋል፤

ሕጉ ከእንግዲህ አይኖርም፤

ነቢያቷም ከእንግዲህ፣

ከእግዚአብሔር ራእይ አያገኙም።

י ዮድ

10የጽዮን ሴት ልጅ ሽማግሌዎች፣

በምድር ላይ በዝምታ ተቀምጠዋል፤

በራሳቸው ላይ ትቢያ ነሰነሱ፤

ማቅም ለበሱ፤

የኢየሩሳሌም ወጣት ሴቶች፣

ራሳቸውን ወደ ምድር ዝቅ አደረጉ።

כ ካፍ

11ዐይኔ በልቅሶ ደከመ፤

ነፍሴ በውስጤ ተሠቃየች፤

ልቤም በሐዘን ፈሰሰች፣

በከተማዪቱ መንገዶች ላይ፣

ሕዝቤ ተደምስሰዋልና፤

ልጆችና ሕፃናት ደክመዋልና።

ל ላሜድ

12በከተማዪቱ መንገዶች ላይ፣

እንደ ቈሰሉ ሰዎች ሲደክሙ፣

በእናታቸው ክንድ ላይ፣

ነፍሳቸው በመውጣት ላይ ሳለች፣

“እንጀራና የወይን ጠጅ የት አለ?”

እያሉ እናቶቻቸውን ይጠይቃሉ።

מ ሜም

13የኢየሩሳሌም ሴት ልጅ ሆይ፤ ስላንቺ ምን ማለት እችላለሁ?

ከምንስ ጋር አወዳድርሻለሁ? ድንግሊቱ የጽዮን ልጅ ሆይ፤

አጽናናሽ ዘንድ፣

በምን ልመስልሽ እችላለሁ?

ቍስልሽ እንደ ባሕር ጥልቅ ነው፤

ማንስ ሊፈውስሽ ይችላል?

נ ኑን

14የነቢያቶችሽ ራእይ፣

ሐሰትና ከንቱ ነው፤

ምርኮኛነትሽን ለማስቀረት፣

ኀጢአትሽን አይገልጡም።

የሚሰጡሽም የትንቢት ቃል፣

የሚያሳስትና ከመንገድ የሚያወጣ ነው።

ס ሳሜክ

15በአጠገብሽ የሚያልፉ ሁሉ፣

እጃቸውን ያጨበጭቡብሻል፤

“የውበት መደምደሚያ፣ የምድር ሁሉ ደስታ፣

የተባለች ከተማ ይህች ናትን?”

እያሉ ራሳቸውን በመነቅነቅ፣

በኢየሩሳሌም ሴት ልጅ ላይ ያሾፋሉ።

ע ዐዪን

16ጠላቶችሽ ሁሉ በአንድ ላይ፣

አፋቸውን በኀይል ከፈቱ፤

ጥርሳቸውን እያፏጩ አሾፉ፤

እንዲህም አሉ፤ “ውጠናታል፤

የናፈቅነው ጊዜ ይህ ነበር፤

ኖረንም ልናየው በቃን።”

פ ፌ

17እግዚአብሔር ያሰበውን አደረገ፤

ከረዥም ጊዜ በፊት የተናገረውን፣

ቃሉን ፈጸመ፤

ያለ ርኅራኄ አፈረሰሽ፤

ጠላት በሥቃይሽ ላይ እንዲደሰት፣

የጠላትሽንም ቀንድ2፥17 ቀንድ በዚህ ቦታ ብርታትን ያመለክታል ከፍ ከፍ አደረገ።

צ ጻዲ

18የሕዝቡ ልብ፣ ወደ ጌታ ጮኸ።

የጽዮን ሴት ልጅ ቅጥር ሆይ፤

ቀንና ሌሊት፣

እንባሽ እንደ ወንዝ ይፍሰስ፤

ለራስሽ ዕረፍትን አትስጪ፣

ዐይኖችሽ ከማንባት አያቋርጡ።

ק ቆፍ

19የሌሊቱ ሰዓት ሲጀምር፣

ተነሺ በሌሊት ጩኺ፤

በጌታ ፊት፣

ልብሽን እንደ ውሃ አፍስሺ፤

በየመንገዱ ዳር ላይ፣ በራብ ስለወደቁት፣

ስለ ልጆችሽ ሕይወት፣ እጆችሽን ወደ እርሱ አንሺ።

ר ሬሽ

20አቤቱ እግዚአብሔር ሆይ እይ፤ ተመልከትም፤

በማን ላይ እንዲህ አድርገህ ታውቃለህ?

በውኑ እናቶች ሕፃኖቻቸውን፣

ተንከባክበው ያሳደጓቸውን ልጆች ይብሉን?

ካህኑና ነቢዩስ፣

በእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ውስጥ ይገደሉን?

ש ሲን እና ሺን

21በየመንገዱ ዐቧራ ላይ፣

ወጣትና ሽማግሌ በአንድነት ወደቁ፤

ወይዛዝርቴና ጐበዛዝቴ፣

በሰይፍ ተገደሉ፤

በቍጣህ ቀን ገደልሃቸው፤

ያለ ርኅራኄም ዐረድሃቸው።

ת ታው

22“በበዓል ቀን ለግብዣ እንደምትጠራ፣

ሽብርን ከየአቅጣጫው በእኔ ላይ ጠራህ፤

በእግዚአብሔር የቍጣ ቀን፣

ማንም አላመለጠም ወይም አልተረፈም፤

የተንከባከብኋቸውንና ያሳደግኋቸውን፣

ጠላቴ አጠፋብኝ።”

Bibelen på hverdagsdansk

Klagesangene 2:1-22

Guds dom over Jerusalem

1Ak, som en sort og truende tordensky lå Herrens vrede over Jerusalem.

Israels himmelske herlighed ligger knust i støvet.

End ikke Herrens eget tempel blev forskånet for hans vrede.

2Befolkningen i Juda blev nådesløst jaget fra hus og hjem.

Herren nedbrød i sin vrede hver eneste befæstet by.

Han ødelagde hele kongeriget til skam for dets ledere.

3Den samlede israelitiske hær blev løbet over ende.

Herren trak sin beskyttende hånd væk, da fjenden angreb.

Hans vrede hærgede landet som en fortærende ild.

4Eliten blandt landets ungdom blev dræbt.

Herren blev vores fjende og gjorde det af med os.

Han udgød sin vrede over Jerusalems indbyggere.

5Fjenderne viste sig at være sendt af Herren.

De ødelagde alle paladser og fæstninger i landet

og skabte sorg og smerte overalt i Juda.

6Grundlaget for at holde sabbat og højtid forsvandt,

da Herren nedrev sit tempel, som var det et skur.

Han forstødte i vrede både konger og præster.

7Han forkastede sit alter, forlod sit tempel,

lod fjenderne nedbryde palads og bymur.

De jublede i templet som på en højtidsdag.

8Intet i Jerusalem undgik ødelæggelsens svøbe.

Herren havde besluttet, at bymuren skulle falde.

Alle fæstningsværker og tårne blev lagt i ruiner.

9Jerusalems portslåer blev smadret og portene splintret.

Kongen og landets ledere blev ført bort til et fremmed land.

Toraen bliver glemt og profetisk åbenbaring er forbi.

10Klædt i sæk og med aske på hovedet

sidder de tilbageblevne ledere tavse på jorden.

De unge kvinder går nedbøjede omkring.

11Lidelsen er ikke til at bære, mine tårer er brugt op.

Mit hjerte er knust ved at se mit folks smerte.

Børn og spædbørn dør af sult midt på gaden.

12„Mad! Vand!” klager de små og besvimer.

De falder om som sårede soldater i byens gader.

Langsomt dør de i armene på deres mødre.

13Nøden og pinen i byen er ufattelig.

Åh, Jerusalem, din trøstesløse sorg er uden sidestykke.

Det er umuligt at lindre din grænseløse smerte.

14Ordene I hørte fra jeres såkaldte profeter, var falske.

Hvis de havde påtalt jeres synd i stedet for at lyve,

havde I måske kunnet undgå denne frygtelige skæbne.

15På vejen uden for byen går folk nu forbi og råber hånligt:

„Er det den by, man kaldte verdens skønneste?

Den skulle ellers have bragt glæde til hele jorden.”

16Raseriet står malet i deres ansigter, mens de håner dig:

„Endelig kom Jerusalem ned med nakken!

Det har vi set frem til meget længe.”

17Så fik Herren til sidst gjort alvor af sin trussel.

Han gennemførte uden skånsel den straf, han havde lovet.

Han gav fjenderne sejr og lod dem tage æren for det.

18Tårerne skal strømme som en flod dag og nat.

Græd øjnene ud af hovedet, Jerusalem, råb til Herren.

Lad selv dine nedbrudte mure hulke af gråd.

19Udgyd dine tårer for Herren natten igennem.

Løft hænderne og bønfald ham om at redde dine indbyggere,

som er ved at dø af sult i dine gader.

20„Vær nådig, Herre,” råber Jerusalem. „Stands denne frygtelige straf.

Skal mødre virkelig spise deres egne børn, som sad på deres skød?

Skal præster og profeter myrdes i dit hellige tempel?

21Yngre så vel som ældre ligger døde i gadens snavs.

Både unge mænd og piger blev hugget ned af sværdet.

Herre, du slog dem i din vrede og uden barmhjertighed.

22Ødelæggeren skabte rædsel overalt, så alle måtte smage din vrede.

Du inviterede mine fjender til at komme, som var det en festdag.

Fjenden dræbte alle mine kære, som var født og opvokset hos mig.”