ሮሜ 5 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ሮሜ 5:1-21

ሰላምና ደስታ

1እንግዲህ በእምነት ስለ ጸደቅን፣ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል ከእግዚአብሔር ጋር ሰላም አለን5፥1 ወይም ሰላም ይኑረን ወይም እናድርግ2በእርሱም በኩል አሁን ወደ ቆምንበት ጸጋ በእምነት መግባት ችለናል፤ የእግዚአብሔርንም ክብር ተስፋ በማድረግ ሐሤት እናደርጋለን።5፥2 ወይም ሰላም ይኑረን ወይም እናድርግ፣ 3በዚህ ብቻ ሳይሆን በመከራችንም ሐሤት እናደርጋለን፤5፥3 ወይም ሰላም ይኑረን ወይም እናድርግ፣ ምክንያቱም መከራ ትዕግሥትን እንደሚያስገኝ እናውቃለን። 4ትዕግሥት ጽናትን፣ ጽናት የተፈተነ ባሕርይን፣ የተፈተነ ባሕርይ ተስፋን፤ 5ይህም ተስፋ ለዕፍረት አይዳርገንም፤ እግዚአብሔር በሰጠን በመንፈስ ቅዱስ ፍቅሩን በልባችን አፍስሷልና። 6ገና ደካሞች ሳለን፣ ልክ ጊዜው ሲደርስ፣ ክርስቶስ ስለ ኀጢአተኞች ሞቷልና። 7ለጻድቅ የሚሞት ሰው ማግኘት እጅጉን ያዳግታል፤ ለደግ ሰው ሲል ሊሞት የሚደፍር ምናልባት ይገኝ ይሆናል። 8ነገር ግን ገና ኀጢአተኞች ሳለን ክርስቶስ ስለ እኛ ሞተ፤ ይህም እግዚአብሔር ለእኛ ያለውን የራሱን ፍቅር ያሳያል።

9አሁን በደሙ ከጸደቅን፣ ይልቁንማ በእርሱ በኩል ከእግዚአብሔር ቍጣ እንዴት አንድንም! 10የእግዚአብሔር ጠላቶች ሳለን በልጁ ሞት ከእርሱ ጋር ከታረቅን፣ ዕርቅን ካገኘን በኋላ፣ በሕይወቱማ መዳናችን እንዴት የላቀ አይሆንም! 11ይህ ብቻ አይደለም። ነገር ግን አሁን ዕርቅን ባገኘንበት በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል በእግዚአብሔር ደግሞ ሐሤት እናደርጋለን።

ሞት በአዳም፣ ሕይወት በክርስቶስ

12ስለዚህ ኀጢአት በአንድ ሰው በኩል ወደ ዓለም እንደ ገባ ሁሉ፣ ሞትም በኀጢአት በኩል ገብቷል፤ በዚሁ መንገድ ሞት ወደ ሰዎች ሁሉ መጣ፤ ምክንያቱም ሁሉም ኀጢአትን ሠርተዋል፤ 13ሕግ ከመሰጠቱ በፊት ኀጢአት በዓለም ላይ ነበር፤ ነገር ግን ሕግ በሌለበት ኀጢአት አይቈጠርም። 14ይሁን እንጂ ከአዳም ጀምሮ እስከ ሙሴ ድረስ ባሉት፣ እንደ አዳም ሕግን በመጣስ ኀጢአት ባልሠሩት ላይ እንኳ ሞት ነገሠ፤ አዳም ይመጣ ዘንድ ላለው አምሳሉ ነበረ።

15ነገር ግን ስጦታው እንደ በደሉ መጠን አይደለም፤ በአንድ ሰው መተላለፍ ብዙዎቹ ከሞቱ፣ የእግዚአብሔር ጸጋና በአንዱ ሰው፣ ይኸውም በኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ የመጣው ስጦታ ለብዙዎች እንዴት አብልጦ ይትረፈረፍ! 16ደግሞም የእግዚአብሔር ስጦታ እንደ አንዱ ሰው የኀጢአት ውጤት አይደለም፤ ምክንያቱም ፍርዱ የአንድን ሰው ኀጢአት ተከትሎ ኵነኔን አመጣ፤ ስጦታው ግን አያሌ መተላለፍን ተከትሎ ጽድቅን አመጣ። 17በአንድ ሰው መተላለፍ ምክንያት ሞት በዚህ ሰው በኩል የነገሠ ከሆነ፣ የእግዚአብሔርን የተትረፈረፈ ጸጋና የጽድቅ ስጦታ የተቀበሉት፣ በአንዱ ሰው በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል እንዴት አብልጠው በሕይወት አይነግሡ!

18ከእንግዲህ በአንድ ሰው መተላለፍ የተነሣ ኵነኔ በሁሉ ሰው ላይ እንደ መጣ፣ እንዲሁም በአንዱ የጽድቅ ሥራ ለሰው ሁሉ ሕይወትን የሚሰጥ ጽድቅ ተገኘ። 19በአንዱ ሰው አለመታዘዝ ብዙዎች ኀጢአተኞች እንደ ሆኑ፣ በአንዱ ሰው መታዘዝ ደግሞ ብዙዎች ጻድቃን ይሆናሉ።

20ሕግ በመምጣቱ መተላለፍ በዛ፤ ነገር ግን ኀጢአት በበዛበት ጸጋ አብልጦ የተትረፈረፈ ሆነ፤ 21ይህም የሆነው ኀጢአት በሞት እንደ ነገሠ ሁሉ፣ በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል ደግሞ የዘላለም ሕይወት ይገኝ ዘንድ ጸጋ በጽድቅ እንዲነግሥ ነው።

Thai New Contemporary Bible

โรม 5:1-21

สันติสุขและความชื่นชมยินดี

1เหตุฉะนั้นเมื่อเราได้ถูกนับเป็นผู้ชอบธรรมโดยความเชื่อแล้ว เราจึง5:1 หรือให้เรามีสันติสุขกับพระเจ้าโดยทางองค์พระเยซูคริสต์เจ้าของเรา 2โดยทางพระองค์เราจึงได้เข้าในร่มพระคุณที่เรายืนอยู่นี้ด้วยความเชื่อ และเรา5:2 หรือให้เราจึงชื่นชมยินดีในความหวังที่จะได้มีส่วนในพระเกียรติสิริของพระเจ้า 3ไม่เพียงเท่านั้นแต่เรา5:3 หรือให้เรายังชื่นชมยินดีในความทุกข์ยากของเราด้วย เพราะเรารู้ว่าความทุกข์ยากนั้นก่อให้เกิดความบากบั่น 4ความบากบั่นทำให้เรามีอุปนิสัยที่พิสูจน์แล้วว่าใช้การได้ และอุปนิสัยเช่นนั้นทำให้มีความหวัง 5และความหวังไม่ทำให้เราผิดหวัง เพราะพระเจ้าทรงเทความรักของพระองค์เข้ามาในจิตใจของเราโดยพระวิญญาณบริสุทธิ์ผู้ซึ่งพระเจ้าได้ประทานแก่เรา

6เมื่อเรายังไร้กำลัง พระคริสต์ได้สิ้นพระชนม์เพื่อคนบาปในเวลาอันเหมาะ 7น้อยนักที่จะมีใครตายเพื่อคนชอบธรรม แม้ว่าอาจจะมีบางคนกล้าที่จะตายเพื่อคนดีก็ได้ 8แต่พระเจ้าทรงสำแดงความรักของพระองค์เองแก่เราทั้งหลาย คือขณะที่เรายังเป็นคนบาปอยู่นั้น พระคริสต์ได้สิ้นพระชนม์เพื่อเรา

9ในเมื่อบัดนี้เราได้ถูกนับเป็นผู้ชอบธรรมแล้วโดยพระโลหิตของพระองค์ ยิ่งไปกว่านั้นเราจะรอดพ้นจากพระพิโรธของพระเจ้าโดยพระองค์อย่างแน่นอน! 10เพราะถ้าเรายังได้คืนดีกับพระเจ้าโดยการสิ้นพระชนม์ของพระบุตรของพระองค์ในขณะที่เราเป็นศัตรูกับพระองค์ ยิ่งไปกว่านั้นเมื่อเราได้คืนดีกับพระองค์แล้ว เราก็จะได้รับความรอดโดยพระชนม์ชีพของพระองค์อย่างแน่นอน! 11ไม่เพียงเท่านี้แต่เรายังชื่นชมยินดีในพระเจ้าโดยทางองค์พระเยซูคริสต์เจ้าของเราด้วย บัดนี้พระองค์ทรงทำให้เราคืนดีกับพระเจ้าแล้ว

ความตายมาทางอาดัม ชีวิตมาทางพระคริสต์

12ฉะนั้นเช่นเดียวกับที่บาปเข้ามาในโลกเพราะมนุษย์คนเดียวและบาปนำความตายมา และโดยทางนี้เองความตายจึงมาถึงมวลมนุษย์เพราะทุกคนได้ทำบาป 13เพราะก่อนมีบทบัญญัติบาปก็อยู่ในโลกแล้ว แต่เมื่อยังไม่มีบทบัญญัติก็ไม่ถือว่าบาป 14อย่างไรก็ตามความตายก็ครอบครองมาตั้งแต่สมัยของอาดัมจนถึงสมัยของโมเสส แม้แต่คนที่ไม่ได้ทำบาปโดยละเมิดพระบัญชาเหมือนอาดัมผู้เป็นแบบของพระองค์ซึ่งจะเสด็จมาภายหลัง

15แต่ของประทานนั้นต่างจากการล่วงละเมิด เพราะถ้าคนเป็นอันมากตายเพราะการล่วงละเมิดของมนุษย์เพียงคนเดียว ยิ่งกว่านั้นสักเท่าใดพระคุณของพระเจ้าและของประทานโดยพระคุณของพระเยซูคริสต์เพียงผู้เดียวนั้นย่อมล้นไหลไปสู่คนเป็นอันมาก! 16และของประทานจากพระเจ้าก็ต่างจากผลของบาปของมนุษย์คนเดียว กล่าวคือการพิพากษาเกิดขึ้นหลังจากการทำบาปเพียงครั้งเดียวและนำไปสู่การลงโทษ แต่ของประทานเกิดขึ้นหลังจากการล่วงละเมิดหลายๆ ครั้งและนำไปสู่การนับเป็นผู้ชอบธรรม 17เพราะถ้าโดยการล่วงละเมิดของมนุษย์คนเดียวเป็นเหตุให้ความตายได้ครอบครองผ่านทางมนุษย์คนเดียวผู้นั้น ยิ่งกว่า

นั้นสักเท่าใดบรรดาผู้ที่ได้รับพระคุณและของประทานแห่งความชอบธรรมซึ่งพระเจ้าทรงจัดเตรียมไว้อย่างมากล้นย่อมครอบครองในชีวิตผ่านทางมนุษย์คนเดียวคือพระเยซูคริสต์

18ฉะนั้นการล่วงละเมิดเพียงครั้งเดียวส่งผลให้คนทั้งปวงถูกลงโทษฉันใด การกระทำอันชอบธรรมเพียงครั้งเดียวก็ส่งผลให้คนทั้งปวงถูกนับเป็นผู้ชอบธรรมฉันนั้น ซึ่งการนับเป็นผู้ชอบธรรมนี้นำชีวิตมาให้คนทั้งปวงเหล่านั้น 19เพราะการไม่เชื่อฟังของมนุษย์คนเดียวทำให้คนเป็นอันมากเป็นคนบาปฉันใด การเชื่อฟังของมนุษย์คนเดียวก็ทำให้คนเป็นอันมากเป็นผู้ชอบธรรมฉันนั้น

20บทบัญญัติถูกเพิ่มเข้ามาเพื่อที่การล่วงละเมิดจะมีมากขึ้น แต่ที่ใดมีบาปมากขึ้น พระคุณก็มีมากขึ้นยิ่งกว่านั้น 21เพื่อว่าบาปได้ครอบครองในความตายฉันใด พระคุณจะได้ครอบครองผ่านทางความชอบธรรมเพื่อชีวิตนิรันดร์จะมาทางพระเยซูคริสต์องค์พระผู้เป็นเจ้าของเราฉันนั้น