ራእይ 7 – NASV & CCBT

New Amharic Standard Version

ራእይ 7:1-17

መቶ አርባ አራት ሺሑ መታተማቸው

1ከዚህ በኋላ አራት መላእክት በአራቱ የምድር ማእዘኖች ቆመው አየሁ፤ እነርሱም ነፋስ በምድር ወይም በባሕር፣ ወይም በማንኛውም ዛፍ ላይ እንዳይነፍስ አራቱን የምድር ነፋሶች ያዙ። 2ከዚያም የሕያው አምላክ ማኅተም ያለው ሌላ መልአክ ከምሥራቅ ሲመጣ አየሁ፤ እርሱም ምድርንና ባሕርን ለመጕዳት ሥልጣን የተሰጣቸውን አራቱን መላእክት በታላቅ ድምፅ እንዲህ አላቸው፤ 3“በአምላካችን አገልጋዮች ግንባር ላይ ማኅተም እስከምናደርግባቸው ድረስ ምድርን ወይም ባሕርን፣ ወይም ዛፎችን አትጕዱ።” 4የታተሙትንም ቍጥር ሰማሁ፤ እነርሱም ከእስራኤል ነገዶች ሁሉ መቶ አርባ አራት ሺሕ ነበሩ፤

5ከይሁዳ ነገድ ዐሥራ ሁለት ሺሕ፣

ከሮቤል ነገድ ዐሥራ ሁለት ሺሕ፣

ከጋድ ነገድ ዐሥራ ሁለት ሺሕ፣

6ከአሴር ነገድ ዐሥራ ሁለት ሺሕ፣

ከንፍታሌም ነገድ ዐሥራ ሁለት ሺሕ፣

ከምናሴ ነገድ ዐሥራ ሁለት ሺሕ፣

7ከስምዖን ነገድ ዐሥራ ሁለት ሺሕ፣

ከሌዊ ነገድ ዐሥራ ሁለት ሺሕ፣

ከይሳኮር ነገድ ዐሥራ ሁለት ሺሕ፣

8ከዛብሎን ነገድ ዐሥራ ሁለት ሺሕ፣

ከዮሴፍ ነገድ ዐሥራ ሁለት ሺሕ፣

ከብንያም ነገድ ዐሥራ ሁለት ሺሕ ታተሙ።

ነጭ ልብስ የለበሱ እጅግ ብዙ ሕዝብ

9ከዚህም በኋላ አየሁ፤ እነሆ፤ በዙፋኑና በበጉ ፊት ማንም ሊቈጥራቸው የማይችል ከሕዝብ፣ ከነገድ፣ ከወገን፣ ከቋንቋም ሁሉ እጅግ ብዙ ሕዝብ ቆመው ነበር፤ እነርሱም ነጭ ልብስ ለብሰው፣ የዘንባባ ዝንጣፊ በእጃቸው ይዘው ነበር። 10በታላቅ ድምፅም እንዲህ ብለው ጮኹ፤

“ማዳን በዙፋኑ ላይ የተቀመጠው፣

የአምላካችንና የበጉ ነው።”

11መላእክቱም ሁሉ በዙፋኑና በሽማግሌዎቹ፣ በአራቱም ሕያዋን ፍጡራን ዙሪያ ቆመው ነበር፤ በዙፋኑ ፊት በግንባራቸው ተደፍተው ለእግዚአብሔር ሰገዱ፤ 12እንዲህም ይሉ ነበር፤

“አሜን፤

ውዳሴና ክብር፣

ጥበብ፣ ምስጋናና፣ ሞገስ፣

ኀይልና ብርታትም፣

ከዘላለም እስከ ዘላለም ድረስ ለአምላካችን ይሁን፤

አሜን።”

13ከዚያም ከሽማግሌዎቹ አንዱ፣ “እነዚህ ነጭ ልብስ የለበሱት እነማን ናቸው? ከወዴትስ መጡ?” አለኝ።

14እኔም፣ “ጌታ ሆይ፤ አንተ ታውቃለህ” አልሁት።

እርሱም እንዲህ አለኝ፤ “እነዚህ ከታላቁ መከራ የመጡ ናቸው፤ ልብሳቸውንም በበጉ ደም ዐጥበው አንጽተዋል። 15ስለዚህ፣

“በእግዚአብሔር ዙፋን ፊት ሆነው፣

ቀንና ሌሊት በመቅደሱ ያገለግሉታል፤

በዙፋኑም ላይ የተቀመጠው ድንኳኑን

በላያቸው ይዘረጋል፤

16ከእንግዲህ ወዲህ አይራቡም፤

ከዚህም በኋላ አይጠሙም፤

ፀሓይ አይመታቸውም፤

ሐሩሩም ሁሉ አያቃጥላቸውም፤

17ምክንያቱም በዙፋኑ መካከል ያለው

በግ እረኛቸው ይሆናል፤

ወደ ሕይወት ውሃ ምንጭም ይመራቸዋል፤

እግዚአብሔር እንባን ሁሉ ከዐይናቸው ያብሳል።”

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

啟示錄 7:1-17

為上帝的僕人蓋印

1這些事情之後,我看見四位天使分別站在地的四個角落控制著四面的風,使風不再吹向地面、海洋和樹木。 2我又看見一位天使從東方日出之地上來,手裡拿著永活上帝的印。他對那領受權柄能傷害地和海的四位天使大聲說: 3「我們還沒在上帝的奴僕額上蓋印之前,你們不可傷害地、海和樹木。」 4我聽見以色列各支派中蓋了印的共有十四萬四千人: 5猶大支派有一萬二千,呂便支派有一萬二千,迦得支派有一萬二千, 6亞設支派有一萬二千,拿弗他利支派有一萬二千,瑪拿西支派有一萬二千, 7西緬支派有一萬二千,利未支派有一萬二千,以薩迦支派有一萬二千, 8西布倫支派有一萬二千,約瑟支派有一萬二千,便雅憫支派有一萬二千。

劫後餘生的上帝子民

9後來我又看見一大群人,多得不可勝數。他們來自各國家、各部落、各民族、各語言族群,身穿白袍,手拿棕樹枝,站在寶座和羔羊面前, 10大聲呼喊說:「救恩來自我們坐在寶座上的上帝,也來自羔羊!」 11眾天使都站在寶座、眾長老和四個活物的周圍,在寶座前俯伏敬拜上帝,說: 12「阿們!願頌讚、榮耀、智慧、感謝、尊貴、權柄、能力都歸給我們的上帝,直到永永遠遠。阿們!」

13長老中有一位問我:「這些身穿白袍的人是誰?他們從哪裡來?」

14我回答說:「先生,你知道答案。」

他便說:「這些都是經過大災難的人,他們用羔羊的血將衣裳洗得純淨潔白。 15因此,他們在寶座前,在聖殿中不分晝夜地事奉上帝。坐在寶座上的那位要庇護他們。 16他們不會再受饑餓和乾渴的折磨,也不會再受太陽和酷熱的煎熬, 17因為在寶座中央的羔羊要作他們的牧人,引導他們到生命之泉那裡,上帝要擦乾他們所有的眼淚。」